newsare.net
የእስራኤል ኃይሎች በእስራኤል ቁጥጥር ስር በሚገኘው ዌስት ባንክ ሸማቂዎችን ለመያዝ ባደረጉት አሰሳ ወቅት ዘጠኝ ፍልስጤማውያንን ገድለው ሌሎች በርካቶችን ማየእስራኤል ወታደሮች በዌስት ባንክ ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውን ፍልስጤማውያን ተናገሩ
የእስራኤል ኃይሎች በእስራኤል ቁጥጥር ስር በሚገኘው ዌስት ባንክ ሸማቂዎችን ለመያዝ ባደረጉት አሰሳ ወቅት ዘጠኝ ፍልስጤማውያንን ገድለው ሌሎች በርካቶችን ማቁሰላቸውን የፍልስጤም ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። የዛሬው ብጥብጥ ለወራት ከቀጠለው ግጭት ከሁሉ የከፋው ነው ተብሏል። እንደ ፍልስጤም የጤና ጥበቃ ሚንስትር ተጨማሪ ገለጣ ግጭቱ የተካሄደው የሸማቂ ኃይሎች ጠንካራ ይዞታ በሆነው እና ላለፈው አንድ ዓመት የእስራኤል ጦር ወታደራዊ እንቅስቃሴ በቀጠለባት ዌስት ባንኳ ጄኒን የስደተኞች ካምፕ ባካሄዱት ብርቱ አሰሳ ወቅት ነው። እስራኤል ‘የሸማቂዎችን መረብ ለመበጣጠስ የታለመ ነው’ በሚል በየምሽቱ በዌስት ባንክ ወታደራዊ አሰሳ ስታደርግ ቆይታለች። ፍልስጤማውያን በበኩላቸው እርምጃውን የወደፊት ግዛታቸው ለማድረግ በሚያቅዷት እና እስራኤል ላለፉት ሃምሳ አምስት ዓመታት በኃይል በያዘችው ምድር የሚደረግ መስፋፋት አድርገው ያዩታል። Read more