Ethiopia



ሶማሊያ «በቀጣዩ የአፍሪካ ህብረት ተልእኮ ማን እንደሚሳተፍ የምወስነው እኔ ነኝ» አለች

የሶማሊያ መንግሥት እአአ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ በሀገሯ ሥራ እንዲጀምር ለታቀደው የአፍሪካ ኅብረት አረጋጊ ተልእኮ (አውሶም) ወታደር የሚያዋጡ ሀገሮ
የአሜሪካ ድምፅ

ሶማሊያ «በቀጣዩ የአፍሪካ ህብረት ተልእኮ ማን እንደሚሳተፍ የምወስነው እኔ ነኝ» አለች

የሶማሊያ መንግሥት እአአ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ በሀገሯ ሥራ እንዲጀምር ለታቀደው የአፍሪካ ኅብረት አረጋጊ ተልእኮ (አውሶም) ወታደር የሚያዋጡ ሀገሮችን እንደሚመርጥ አረጋግጧል። የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ ሶማሊያ የተልእኮውን አቅጣጫ «ትኩረቱን በግልጽ ሉዓላዊነት ላይ» ባደረገ መንገድ ትመራዋለች ብሏል፡፡ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የደረሰችው ስምምነት  ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ነው ስትል ሶማሊያ ትከራከራለች። «ከሶማሊያ ሰሜናዊ ክልል ጋር የተደረገውን ስምምነት ጨምሮ፣ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜያት የወሰደቻቸው የተናጠል እርምጃዎች ሉዓላዊነታችንን የሚጥስ እና ለሰላም ማስከበር አስፈላጊ የሆነውን አመኔታ የሚሸረሽር ነው።» ሲል መግለጫው አመልክቷል። መግለጫው የወጣው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ሶማሊያ ውስጥ ጦር ባላቸው አራት ሀገራት፣ ማለትም ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ቡሩንዲ እና ጅቡቲ ያደረጉትን ጉብኝት ካጠናቀቁ በኋላ ነው። መሀሙድ ሶማሊያ ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች ቢኖራትም ኢትዮጵያን አልጎበኙም፡፡ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተያየቱን እንዲሰጥ ከቪኦኤ ለቀረበለት ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም። ኢትዮጵያ  የአውሶም አካል ሆና ለመሳተፍ ፈቃደኛ መሆኗን አመላክታለች። ባለፈው ነሀሴ ኢትዮጵያ ወደ አዲሱ የአውሶም (AUSSOM) ተልዕኮ የሚደረገው ሽግግር “አካባቢው ላይ አደጋ ደቅኗል” ስትል አስጠንቅቃለች። ኢትዮጵያ አዲሱን ተልዕኮ የማዘጋጀት ኃላፊነት የተጣለባቸው አካላት "የቀጠናውን ሀገራት እና ሠራዊት ያዋጡ ሀገራትን ተገቢ ስጋት ከግምት ማስገባት አለባቸው” በማለት አሳስባለች፡፡ ሽግግሩ እየተዘጋጀ ባለበት በዚህ ወቅት ክልሉ “ወደ ማይታወቅ አደጋ እየገባ ነው” ስትልም ኢትዮጵያ ያላትን ስጋት አመልክታለች። “ኢትዮጵያ የጥላቻ መግለጫዎችን እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የከፈለውን መስዋእትነት ችላ መባሉን በዝምታ እንድታልፈው እየተጠበቀ ነው” ስትልም ኢትዮጵያ በመግለጫዋ አክላለች፡፡

«የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ሩሲያ ውስጥ መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ አለ» የመከላከያ ሚንስትር ሎይድ ኦስትን

የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስትን “የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ሩሲያ ውስጥ መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ አለ” ሲሉ ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩ ት
የአሜሪካ ድምፅ

«የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ሩሲያ ውስጥ መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ አለ» የመከላከያ ሚንስትር ሎይድ ኦስትን

የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስትር ሎይድ ኦስትን “የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ሩሲያ ውስጥ መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ አለ” ሲሉ ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩ ትላንት ረቡዕ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል “ቀሪው ነገር” እዚያ ምን እንደሚሠሩ ማየቱ ነው ብለዋል። ኦስትን ይህን ያሉት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ ሁለት የሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ ክፍሎች ሩሲያ ውስጥ ለዩክሬኑ ጦርነት ሊውል የሚችል ሥልጠና እየወሰዱ መሆኑን መንግሥታቸው መረጃ እንዳለው ከተናገሩ አንድ ቀን በኋላ ነው፡፡ ሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያ «የተጠናከረ ግንኙነት» አላቸው ያሉት ኦስትን ሰሜን ኮሪያ ለሩሲያ የጦር መሣሪያ እንደሰጠች ጠቁመዋል፡፡ «ግንባር ከፈጠሩ፣ አላማቸው በዚህ ጦርነት ሩሲያን ወክለው ለመሳተፍ ከሆነ፣ ያ በጣም፣ በጣም አሳሳቢ ጉዳይ ነው፣ በአውሮፓ ብቻ ሳይሆን በህንድ እና ፓሲፊክ ውቅያኖስ አካባቢ (ኢንዶ-ፓሲፊክ) ባሉ ጉዳዮችም ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል» ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ኦስትን ሩሲያ እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ ዩክሬንን ሙሉ በሙሉ በመውረር በከፈተችው ጦርነት ሰለባ ስለሆኑ ሩሲያውያን ገልፀው፣ የሰሜን ኮሪያ እዚህ ውስጥ መጨመር የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን “ብዙ ሰዎች ከሚያስቡት በላይ የበለጠ ችግር ውስጥ ሊሆኑ እንደሚችሉ አመላካች ነው” ብለዋል። ዜሌነስኪ «ሰሜን ኮሪያ በአውሮፓ ጦርነት ውስጥ ጣልቃ መግባት ከቻለች፣ በዚህ አገዛዝ ላይ የሚደረገው ጫና በእርግጠኝነት በቂ አይደለም ማለት ነው» በማለት ዩክሬን ከዓለም ጠንካራና ተጨባጭ ምላሽ ትጠብቃለች” ብለዋል፡፡

VOA60 Africa - Uganda: Fuel truck explosion near Kampala kills at least 10 people

A fuel truck that ran out of control and exploded into flames near the capital, Kampala, killed at least 10 people, police said Tuesday. Last week a fuel tanker exploded in northern Nigeria, killing more than 170 people.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - Uganda: Fuel truck explosion near Kampala kills at least 10 people

A fuel truck that ran out of control and exploded into flames near the capital, Kampala, killed at least 10 people, police said Tuesday. Last week a fuel tanker exploded in northern Nigeria, killing more than 170 people.

VOA60 America - Blinken visits Saudi Arabia amid push for Middle East ceasefire

U.S. Secretary of State Antony Blinken arrived in Saudi Arabia from Israel on Wednesday. Blinken said in Israel that Israel’s killing of Hamas leader Yahya Sinwar presents a “real opportunity” to free the remaining hostages being held by Hamas in Gaza a
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - Blinken visits Saudi Arabia amid push for Middle East ceasefire

U.S. Secretary of State Antony Blinken arrived in Saudi Arabia from Israel on Wednesday. Blinken said in Israel that Israel’s killing of Hamas leader Yahya Sinwar presents a “real opportunity” to free the remaining hostages being held by Hamas in Gaza and end the Israel-Hamas war.

VOA60 World - Israeli jets struck multiple buildings in the Lebanese coastal city of Tyre

Israeli jets struck multiple buildings in the coastal city of Tyre on Wednesday, sending large clouds of black smoke into the air. The state-run National News Agency reported that an Israeli airstrike on the nearby town of Maarakeh killed three people.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Israeli jets struck multiple buildings in the Lebanese coastal city of Tyre

Israeli jets struck multiple buildings in the coastal city of Tyre on Wednesday, sending large clouds of black smoke into the air. The state-run National News Agency reported that an Israeli airstrike on the nearby town of Maarakeh killed three people.

ብሊንከን የሃማስ መሪ ከተገደሉ በኋላ ታጋቾቹን ለማስለቀቅ «እውነተኛ ዕድል ይኖራል» አሉ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ እስራኤል የሃማሱን መሪ ያህያ ሲንዋርን መግደሏ አሁንም ጋዛ ውስጥ በታጣቂው ቡድን እጅ ያሉትን ቀ
የአሜሪካ ድምፅ

ብሊንከን የሃማስ መሪ ከተገደሉ በኋላ ታጋቾቹን ለማስለቀቅ «እውነተኛ ዕድል ይኖራል» አሉ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን፣ እስራኤል የሃማሱን መሪ ያህያ ሲንዋርን መግደሏ አሁንም ጋዛ ውስጥ በታጣቂው ቡድን እጅ ያሉትን ቀሪዎቹን ታጋቾች የሚያስለቅቅ ስምምነት ላይ ለመድረስ  እውነተኛ እድል ማምጣቱን ተናገሩ። ብሊንክን ይህን የተናገሩት፣ ዛሬ ረቡዕ ከቴል አቪቭ ወደ ሳኡዲ አረብያ ከመብረራቸው በፊት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው። «እስራኤል ሃማስ ላይ በምታካሂደው ጦርነት  ወታደራዊ ዓቅሙን ማዳከም ጨምሮ ብዙ ስኬት አግኝታለች» ያሉት ብሊንከን  «የቀረው ታጋቾቹን ማስለቀቅ እና ጦርነቱን ማጠናቀቅ ነው» ብለዋል።  ጦርነቱ ሃማስን ከጋዛ በሚያስወጣ እና የእስራኤል ወታደሮችም እዚያ እንዳይቆዩ በሚያደርግ መንገድ መጠናቀቅ እንዳለበትም ብሊንክን አሳስበዋል። ከጦርነቱ በኋላ ለጋዛ የሚኖረው እቅድ አስተዳደር፣ ደህንነት፣ መልሶ ግንባታ፣ እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ፍልስጤማውያንን ለመርዳት ማድረግ የሚችለውን ጨምሮ በሚቀጥሉት ቀናት ከአረብ አገሮች ጋራ የሚወያዩበት ርዕስ እንደሚሆን ብሊንከን ተናግረዋል፡፡ ብሊንከን ነገ ሐሙስ ወደካታር ይሄዱ እና አርብ በለንደን ከአረብ ሀገራት አቻዎቻቸው ጋራ  እንደሚገናኙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ብሊንከን እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ሎይድ ኦስተን እስራኤል ወደጋዛ የሚገባውንን የሰብአዊ ርዳታ መጠን እንድትጨምር፣ አለዚያ  የአሜሪካን ወታደራዊ ርዳታ እንደምታጣ የሚያስጠነቅቅ ደብዳቤ ከላኩ አንድ ሳምንት በኋላ ሁኔታዎች መሻሻል ቢያሳዩም ብዙ እንደሚቀረውና ቀጣይነት እንደሚያስፈልገው የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ትላንት ረቡዕ በሰጡት መግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ አምና የሰጡትን ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ተከትሎ እስራኤል ወዲያውኑ የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦቱ መጠን እንዲጨምር ብታደርግም እንዳልቀጠለ ብሊንከን አውስተዋል። አዲሱ ማስጠንቀቂያ «ባዶ ማስፈራሪያ» ይሆን እንደሆን የተጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ « በሕጉ  መሠረት ለመሥራት ቁርጠኛ ነኝ» ብለዋል፡፡ ብሊንከን ከአንድ ዓመት በፊት ከተቀሰቀሰው የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነት ወዲህ ባደረጉት 11ኛ ጉብኘታቸው ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋራ ትላንት ማክሰኞ ተገናኝተው ተወያይተዋል። የሃማሱ መሪ ሲንዋርን ግድያ ተከትሎ ዩናትይትድ ስቴትስ ወደ አካባቢው ተመልሳ የተኩስ አቁም ጥረቱን እንድትገፋበት መልካም አጋጣሚ የተከፈተላት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ኅይሎች ዛሬ ረቡዕ የሊባኖስ ደቡባዊ የወደብ ከተማ ታይር ላይ የአየር ጥቃት አካሂደዋል፡፡ ጥቃቱን ያደረሱት ነዋሪዎች ከተማዋን ለቅቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ከሰጡ ከሰዓታት በኋላ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ሌሊቱን ቤይሩት ውስጥ ያሉ ከሄዝቦላህ ጋር ግንኙነት ያላቸውን አካባቢዎች ደብድበናል ስትል እስራኤል አስታውቃለች፡፡ ዛሬ ረቡዕ ቤይሩትን የጎበኙት የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አናሌና ቤርቦክ ለሊባኖሱ ጦርነት ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሕክምና የበጎ አድራጎት አገልግሎቶች የሃያ አምስት ዓመታት ጉዞ

ዋና መቀመጫውን ዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው “ፒፕል ቱ ፒፕል” ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብላ በምትገኘው የአርሊንግተን ዋና ከተማ የተመሰረ
የአሜሪካ ድምፅ

በሕክምና የበጎ አድራጎት አገልግሎቶች የሃያ አምስት ዓመታት ጉዞ

ዋና መቀመጫውን ዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው “ፒፕል ቱ ፒፕል” ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብላ በምትገኘው የአርሊንግተን ዋና ከተማ የተመሰረተበትን ሃያ አምስተኛ ዓመት መታሰቢያ በማድረግ ዓመታዊ የሕክምና ሳይንስ ጉባኤው አካሂዷል። አብዛኞቹ አባላቱ ኢትዮጵያውያን የሕክምና ባለሞያዎች ቢሆኑም፤ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ከፍተኛ እውቅና ያላቸው የሕክምና ባለ ሞያዎችም ለዓመታት ተሳትፈውበታል። ከሕክምና አገልግሎቶች እና የህክምና ትምሕርት ተሳትፎዎቹ በተጨማሪም በሌሎች ርዳታ የሚሹ ማኅበራዊ ጉዳዮች አስተዋጽኦ ሲያደርግ የቆየ ድርጅት ነው። ይህንኑ መነሻ በማድረግ ከድርጅቱ አመራር አባላት ጋራ ውይይት አካሂደናል። ውይይቱን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በምዕራብ ወለጋ ግጭት ውስጥ ያልተሳተፉ ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ፣ በመንግሥት ኃይሎች እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ግጭት፣ ሲቪ
የአሜሪካ ድምፅ

በምዕራብ ወለጋ ግጭት ውስጥ ያልተሳተፉ ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ፣ በመንግሥት ኃይሎች እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ግጭት፣ ሲቪሎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ። የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች «ለታጣቂዎቹ ታገለግላላችኹ» ፣ ታጣቂዎቹ ደግሞ «ለመንግሥት ትሠራላችኹ» በሚል ከሁለቱም በኩል ጉዳት እየደረሰባቸው እንደኾነ፣ ለቪኦኤ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ጉዳቱ ደርሶበታል የተባለው፣ የቆንዳላ ወረዳ አስተዳዳር፣ ተገደሉ ስለተባሉ ሲቪሎች መረጃ እንደሌለው አስታውቋል። መንግሥት በሲቪሎች ላይ ጥቃት እንደማያደርስም የወረዳው አስተዳዳሪ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በአካባቢው ይፈፀማል የተባለው ጥቃት ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል። /ዝርዝርሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

ስፔን ከአፍሪካ የሚመጣውን ፍልሰት እንደ መልካም የኢኮኖሚ አጋጣሚ ትመለከታለች

ለቀኝ ዘመም ወግ አጥባቂ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሰጠው ድጋፍ እየጨመረ በመጣበት የአውሮፓ ኅብረት፣ ዓባል ሃገራቱ ፍልሰት እንዲቆም ጥሪ በማድረግ ላይ ናቸው።
የአሜሪካ ድምፅ

ስፔን ከአፍሪካ የሚመጣውን ፍልሰት እንደ መልካም የኢኮኖሚ አጋጣሚ ትመለከታለች

ለቀኝ ዘመም ወግ አጥባቂ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሰጠው ድጋፍ እየጨመረ በመጣበት የአውሮፓ ኅብረት፣ ዓባል ሃገራቱ ፍልሰት እንዲቆም ጥሪ በማድረግ ላይ ናቸው። ስፔን ግን ከዚህ በተቃራኒ በመቆም፣ በአውሮፓ ዕድሜያቸው የገፉ አዛውንቶች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ፣ ኢኮኖሚውን ለማሳደግ ቁጥጥር የሚደረግበት ፍልሰት አስፈላጊ ነው ትላለች። ሄንሪ ሪጅዌል ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የአሜሪካ ምርጫ ወጪ 

ሃገራት በምርጫ ወቅት ከፍተኛ ገንዘብ ያወጣሉ። የአሜሪካ የምርጫ ወጪ ከሌሎች ሃገራት ጋራ ሲነጻጸር ከፍተኛ ነው። ይህንንኑ የተመለከተውን  ገላጭ ዘገባ ከተያ
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ ምርጫ ወጪ 

ሃገራት በምርጫ ወቅት ከፍተኛ ገንዘብ ያወጣሉ። የአሜሪካ የምርጫ ወጪ ከሌሎች ሃገራት ጋራ ሲነጻጸር ከፍተኛ ነው። ይህንንኑ የተመለከተውን  ገላጭ ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የሠራተኛ ማኅበራት ድጋፍ በዩናይትድ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ያለው ከፍተኛ ሚና

በመላዋ ዩናይትድ ስቴትስ ወደ14 ሚሊዮን የሚሆኑት መራጮች መብታቸውን ለማስከበር በተቋቋሙ ማኅበራት የተደራጁ ሠራተኞች ናቸው። ከአጠቃላዩ መራጭ ቁጥር አኳያ
የአሜሪካ ድምፅ

የሠራተኛ ማኅበራት ድጋፍ በዩናይትድ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ያለው ከፍተኛ ሚና

በመላዋ ዩናይትድ ስቴትስ ወደ14 ሚሊዮን የሚሆኑት መራጮች መብታቸውን ለማስከበር በተቋቋሙ ማኅበራት የተደራጁ ሠራተኞች ናቸው። ከአጠቃላዩ መራጭ ቁጥር አኳያ ሲታይ ቁጥራቸው አነስተኛ ቢሆንም ፕሬዚደንታዊ ዕጩ ተፎካካሪዎች ድጋፋቸውን በእጅጉ ይፈልጉታል። የአሜሪካ ድምጿ የምክር ቤታዊ ጉዳዮች ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን በዘንድሮ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ የሠራተኛ ማኅበራት ድምጽ ትልቅ ሚና የሚጫወትባት ከሆነችው ከኔቫዳ ክፍለ ግዛት ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የአይ ኤም ኤፍ እና ዓለም ባንክ ዓመታዊ ጉባኤ

ዓመታዊው የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤም ኤፍ)ና የዓለም ባንክ ጉባኤ በዋሽንግተን ዲሲ ተጀምሯል።  ኢትዮጵያን ጨምሮ የአባል ሃገራቱ የገንዘብ ሚንስት
የአሜሪካ ድምፅ

የአይ ኤም ኤፍ እና ዓለም ባንክ ዓመታዊ ጉባኤ

ዓመታዊው የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤም ኤፍ)ና የዓለም ባንክ ጉባኤ በዋሽንግተን ዲሲ ተጀምሯል።  ኢትዮጵያን ጨምሮ የአባል ሃገራቱ የገንዘብ ሚንስትሮችና የብሄራዊ ባንክ ገዥዎች የሚሳተፉበት ነው። የኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት አማካሪው አቶ ያሬድ ሃይለመስቀል ይህ ጉባኤ የዓለም ኢኮኖሚ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጦርነቶች እየተፈተነ ባለበት ወቅት የሚካሄድ ነው ይላሉ። /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/ 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 11 ፓርቲዎችን በጊዜያዊነት አገደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "በጠቅላላ ጉባኤ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋራ በተያያዘ፣ 11 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በጊዜያ
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 11 ፓርቲዎችን በጊዜያዊነት አገደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "በጠቅላላ ጉባኤ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋራ በተያያዘ፣ 11 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በጊዜያውነት ማገዱን ትላንት ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም. በጻፈው እና በፌስቡክ ገጹ ይፋ ባደረገው ደብዳቤ አስታውቋል። ቦርዱ የእግድ ውሳኔ ካሳለፈባቸው ፓርቲዎች መካከል የኦሮሞ ነጻነት ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የጌዲኦ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የሐረዲ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ፣ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የጋምቤላ ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የጋምቤላ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ኅብረት እና አገው ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ ይገኙበታል።  ፓርቲው እግዱን አስመልክቶ ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋር ምክር ቤት በጻፈው በዚሁ ደብዳቤ፣ ቦርዱ የተለየ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ፣ ፓርቲዎቹ ከማንኛውም ሕጋዊ እንቅስቃሴ ታቅበው እንዲቆዩ ትዕዛዝ አስተላልፏል።  በመሆኑም የተዘረዘሩት ፓርቲዎች የተጣለባቸው የእግድ ውሳኔ እስከሚነሳ ድረስ፣ በማናቸውም የጋራ ምክር ቤቱ የሚያዘጋጃቸው ጉባኤዎች ላይ ሊገኙ፣ ሊመርጡ፣ ሊመረጡ ወይም በተለያዩ ኮሚቴዎች ውስጥ ሊያገለግሉ እንደማይችሉ ቦርዱ ጨምሮ ገልጿል።  እስካሁን ስማቸው ከተጠቀሰው ፓርቲዎች በኩል የወጣ መግለጫም ሆነ የተሰጠ አስተያየት የለም።

ኡጋንዳ  16 ተቃዋሚዎችን በ’ሀገር ክህደት’ ወነጀለች

የኡጋንዳ ወታደራዊ ፍርድ ቤት «በሕግ ወጥ መንገድ ፈንጂ ይዞ በመገኘት እና የሀገር ክህደት በመፈጸም» በተወነጀሉ 16 የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ በትላንት
የአሜሪካ ድምፅ

ኡጋንዳ  16 ተቃዋሚዎችን በ’ሀገር ክህደት’ ወነጀለች

የኡጋንዳ ወታደራዊ ፍርድ ቤት «በሕግ ወጥ መንገድ ፈንጂ ይዞ በመገኘት እና የሀገር ክህደት በመፈጸም» በተወነጀሉ 16 የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ በትላንትናው እለት የጥፋተኝነት ብይን ማሳለፉን አንድ የተከሳሾች ተከላካይ ጠበቃ አስታወቁ። የችሎቱን ውሳኔም ‘አጠያያቂ’ ብለውታል። አቃቤ ሕግ 16’ቱን የተቃዋሚው ይብሔራዊ አንድነት መድረክ ፓርቲ አባላት እና እስከአሁን  አልተያዙም ያላቸውን ሌሎች ግለሰቦች እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በሕዳር 2020 እና በግንቦት 2021 መካከል ባለው ጊዜ በሃገሪቱ ምርጫ እየተካሄደ ሳለ የተባሉትን ወንጀሎች ‘ፈጽመዋል’ ሲል ነው የከሰሳቸው።   ሻሚም ማሌንዴ የተባሉ የተከሳሾች ተከላካይ ጠበቃ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ የዜና ወኪል እንደተናገሩት፤ «ካሁን ቀደም ወንጀሉን አልፈጸምንም” ሲሉ ክሱን ያስተባበሉት ተከሳሾች አሁን ጥፋተኝነታቸውን አምነዋል የተባለበትን ሁኔታ “አጠያያቂ ነው» ብለውታል። ‘ባቢ ዋይን’ በሚል የመድረክ ስም የሚታወቀው  የቀድሞ ድምጻዊ  ሮበርት ኪያጉላኒ የተባለው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል፤ ቡድኑ ጥፋተኛነቱን አምኖ ፕሬዝዳንታዊ ይቅርታ እንዲጠይቅ መገደዱን ተናግሯል። 16ቱ ተከሳሾች አራት ዓመታት በእስር ላይ የቆዩ ሲሆኑ፤ ነገ ረቡዕ ችሎቱ ዘንድ ይቀርባሉ። ጋዜጠኞች ሥነ ስርአቱን እንዳይከታተሉ ታግደዋል። ምሥራቅ አፍሪቃዊቱ አገር ኡጋንዳ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1986 አንስቶ በዩዌሪ ሙሴቬኒ ስትመራ መቆየቷ ይታወቃል።  

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያውያንን በእግር ኳስ አንድ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ካፍ አስታወቀ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ያቀረበችውን ጥያቄ ካፍ እንዲያፀድቀው ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአዲስ አበባ በተካሔደው የካፍ 46ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላ
የአሜሪካ ድምፅ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያውያንን በእግር ኳስ አንድ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ካፍ አስታወቀ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ያቀረበችውን ጥያቄ ካፍ እንዲያፀድቀው ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአዲስ አበባ በተካሔደው የካፍ 46ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ጠየቁ።  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “ኢትዮጵያውያንን በእግር ኳስ አንድ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው” የተናገሩት የካፍ ፕሬዝደንት ፓትሪስ ሞትሴፔ፣ የኢትዮጵያ ጥያቄ በካፍ አሠራር መሰረት ታይቶ ምላሽ እንደሚሰጠው ተናግረዋል፡፡ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በመጪው 2029 ዓ.ም. የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት 13 አገራት መጠየቃቸውንም አስታውቀዋል።  የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ እኢንፋንቲኖ በበኩላቸው፣ በፊፋ የዓለም ዋንጫ የሚሳተፉ የአፍሪካ አገራት ቁጥር ከቀጣዩ ውድድር ጀምሮ በእጥፍ እንደሚጨምር፣ በአዲስ አበባው የካፍ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ገልፀዋል፡፡ /ዝርዝርሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/ 

የኤሌክቶራል ኮሌጅ ሂደት

ኤሌክቶራል ኮሌጅ (Electoral College) የአሜሪካ ዜጎች ፕሬዝዳንታቸውን የሚመርጡበት ሂደት ነው። በስተመጨረሻ አሸናፊውን የሚመስኑት የኤሌክቶራል ኮሌጅ አባላት ናቸ
የአሜሪካ ድምፅ

የኤሌክቶራል ኮሌጅ ሂደት

ኤሌክቶራል ኮሌጅ (Electoral College) የአሜሪካ ዜጎች ፕሬዝዳንታቸውን የሚመርጡበት ሂደት ነው። በስተመጨረሻ አሸናፊውን የሚመስኑት የኤሌክቶራል ኮሌጅ አባላት ናቸው።  ሂደቱ እንዴት እንደሚካሄድ ከተያያዘው መግለጫ ይከታተሉ። 

ለትግራይ ክልል ተረጂዎች ገቢ ማሰባሰብ ተጀመረ

በትግራይ ክልል 4.5 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው፣ «አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ» የተባለ ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው ተጎጂዎቹን
የአሜሪካ ድምፅ

ለትግራይ ክልል ተረጂዎች ገቢ ማሰባሰብ ተጀመረ

በትግራይ ክልል 4.5 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው፣ «አስቸኳይ ምላሽ ለትግራይ» የተባለ ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው ተጎጂዎቹን ለመርዳት ዛሬ ባስጀመረው የገቢ ማሰባሰቢያ 130 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን እና፣ ፌደራል መንግሥቱ 130 ሚሊዮን ብር ለመስጠት ቃል መግባቱ ታውቋል። /ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

በትረምፕ እና ሀሪስ ምርጫ ዘመቻ “የውስጥ ጠላት” እና “ያልተረጋጋ” መባባሉ ተባብሷል

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ልንታገለው የሚገባን «የውስጥ ጠላት» አለን የሚለው ንግግር በተቃዋሚዎቻቸው ውስጥ ትልቅ የ
የአሜሪካ ድምፅ

በትረምፕ እና ሀሪስ ምርጫ ዘመቻ “የውስጥ ጠላት” እና “ያልተረጋጋ” መባባሉ ተባብሷል

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ልንታገለው የሚገባን «የውስጥ ጠላት» አለን የሚለው ንግግር በተቃዋሚዎቻቸው ውስጥ ትልቅ የትችት ማዕበል አስነስቷል፡፡ ይሁን እንጂ ሁለቱ የሪፐብሊካን እና የዴሞክራቲክ እጩዎች በምርጫ ዘመቻው ቅስቀሳቸው የሚጠቀሙባቸው የጋሉ ንግግሮች “ዋይት ሀውስን የማሸነፍ ዕድላቸውን ሊጎዳ ይችላል” በሚል የተንታኞችን ማስጠንቀቂያ አስከትሏል፡፡ የቪኦኤ ቬሮኒካ ባልደራስ ኤግልሲያስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።    

በታጣቂዎች ተፈጸመ በተባለ ጥቃት 19 ሚሊሽያ አባላት ኦሮሚያ ውስጥ መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ጀልዱ ወረዳ፣ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ተፈጸመ በተባለ ጥቃት፣ 19 ሚሊሽያ አባላት መገደላቸውን ቤተሰቦች እና የአካባቢ
የአሜሪካ ድምፅ

በታጣቂዎች ተፈጸመ በተባለ ጥቃት 19 ሚሊሽያ አባላት ኦሮሚያ ውስጥ መገደላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ጀልዱ ወረዳ፣ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ተፈጸመ በተባለ ጥቃት፣ 19 ሚሊሽያ አባላት መገደላቸውን ቤተሰቦች እና የአካባቢው ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ምላሽ ማግኘት አልቻልንም። /ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

ደቡብ ሱዳን  ያለዕድሜ መዳርን ለማስወገድ የያዘችው አዲስ ጥረት

ደቡብ ሱዳን በትምሕርት ቤት ፣በሴቶች እና ሴቶች ተማሪዎች ብዛት ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ትልቅ ጥረት በማድረግ ላይ ነች። መፍትሄ ይሆን ዘንድ ልጅ ያላቸው ታዳ
የአሜሪካ ድምፅ

ደቡብ ሱዳን  ያለዕድሜ መዳርን ለማስወገድ የያዘችው አዲስ ጥረት

ደቡብ ሱዳን በትምሕርት ቤት ፣በሴቶች እና ሴቶች ተማሪዎች ብዛት ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ትልቅ ጥረት በማድረግ ላይ ነች። መፍትሄ ይሆን ዘንድ ልጅ ያላቸው ታዳጊ ልጃገረዶችን ትምሕርት ቤት እንዲገቡ በማድረግ የተያያዘችው ጥረት ትልቅ ውጤት እያመጣ መሆኑ ተነግሯል። ይህ የደቡብ ሱዳን አዲስ መርሐ ግብር በልጅነት የልጅ እናት ሆነው ትምሕርታቸው የተሰናከለባቸውን ትምሕርታቸውን እንዲቀጥሉ ለማስቻል ተነስቷል። ሺላ ፖኒ ከጁባ ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ጉቴሬዥ ኢትዮጵያ ገብተዋል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጀት ዋና ፀሐፊ  አንቶኒዮ ጉተሬዥ በተመድ እና የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ለመገኘት አዲስ አበባ ገብተዋል።  ለ
የአሜሪካ ድምፅ

ጉቴሬዥ ኢትዮጵያ ገብተዋል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጀት ዋና ፀሐፊ  አንቶኒዮ ጉተሬዥ በተመድ እና የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ለመገኘት አዲስ አበባ ገብተዋል።  ለጉቴሬዥ አቀባበል ያደረጉት ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ በቀጠናዊና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ላይ እንደተወያዩ በ X ማኅበራዊ መድረክ ላይ ባጋሩት መልዕክት አስታውቀዋል። ጉቴሬዥ በተጨማሪም ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ጋራ ተነጋግረዋል። በሠላምና ፀጥታ፣ በዘላቂ ልማት እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ላይ ባሉ ተግዳሮቶችና ልምዶች ላይ መነጋገራቸውን ሙሳ ፋኪ ማሃማት አስታውቀዋል።

ፑቲን የብሪክስን ጉባኤ ያስተናግዳሉ

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪዎቹ ቀናት የዓለም መሪዎችን በመቀበል የብሪክስን ጉባኤ ያስተናግዳሉ። የቻይና፣ የሕንድ፣ የቱርክ፣ እንዲሁም የኢ
የአሜሪካ ድምፅ

ፑቲን የብሪክስን ጉባኤ ያስተናግዳሉ

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪዎቹ ቀናት የዓለም መሪዎችን በመቀበል የብሪክስን ጉባኤ ያስተናግዳሉ። የቻይና፣ የሕንድ፣ የቱርክ፣ እንዲሁም የኢራንን ጨምሮ በርካታ የዓለም መሪዎች የሚገኙበትና በሩሲያዋ ካዛን ከተማ የሚካሄደው ጉባኤ፤ በዩክሬን በሚካሄደው ጦርነትና በወጣባቸው የእስር የመያዣ ትዕዛዝ ምክንያት ከዓለም መድረክ ይገለላሉ ሲባሉ የነበሩት ፑቲን፣ አሁንም ተሰሚነት እንዳላቸው ማሳያ ነው ተብሏል። ሩሲያ የብሪክስን ጉባኤ በማስተናገድ፣ ከምዕራቡ ዓለም  ጋራ ውጥረቱ እየቀጠለ ቢመጣም ከአጋሮቿ ጋራ መቆሟን ለማመልከት የምትጠቀምበትና የጦርነት ኢኮኖሚዋን ለመደገፍ ስምምነትና ድርድር የምታደርግበት መድረክ መሆኑን ተንታኞች በመናገር ላይ ናቸው። ለሌሎቹ ለተሳታፊ ሃገራት ደግሞ ትርክቶቻቸውን አጉልቶ ለማሰማት ዕድል የሚሰጥ መድረክ ነው ተብሏል። ነገ ማክሰኞ ጉባኤውን የሚጀምረውና በማደግ ላይ ያሉ ኢኮኖሚዎች ስብስብ የሆነው ብሪክስ፤ በምዕራቡ ዓለም የሚመራውን የዓለም ሥርዓት ለመገዳደር በሚል ሲጀመር በአምስት ሃገራት የተቋቋመ ሲሆን፣ በያዝነው ዓመት ግን ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሃገራት ተቀላቅለዋል። ሌሎች በርካታ ሃገራትም ለመቀላቀል ጥያቄ በማቅረብ ላይ ናቸው።

በጫሞ ሓይቅ የጀልባ አደጋ የሞቱት ሰዎች አስከሬን ተገኘ

ባለፈው ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን በሚገኘው የጫሞ ሓይቅ በደረሰ የጀልባ አደጋ ሕይወታቸው ካለፈው 13 ሰዎች ውስጥ የአስራ ሁለቱን አስከሬን ማግኘታቸው
የአሜሪካ ድምፅ

በጫሞ ሓይቅ የጀልባ አደጋ የሞቱት ሰዎች አስከሬን ተገኘ

ባለፈው ሳምንት በደቡብ ኢትዮጵያ በጋሞ ዞን በሚገኘው የጫሞ ሓይቅ በደረሰ የጀልባ አደጋ ሕይወታቸው ካለፈው 13 ሰዎች ውስጥ የአስራ ሁለቱን አስከሬን ማግኘታቸውን የካባቢው ባለሥልታናት አስታውቀዋል። ባለፈው ሐሙስ አደጋው ሲደርስ ጀልባው 16 ሰዎችን አሳፍሮ እንደነበር ያስታውቀው የአካባቢው አስተዳደር፣ ሶስት ሰዎችን ወዲያውኑ ከአደጋው መታደግ እንደተቻለ ገልጿል። የጀልባዋ ተሳፋሪዎችም “የቀን ሠራተኞች” እንደሆኑ ተገልጿል። የዞኑ ፖሊስ ቃል አቀባይ የሆኑት ኮማንደር ረታ ተክሉ ለቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ ክፍል እንደተናገሩት፣ ጀልባው ቆሬ ዞን ከሚገኘው አቡሎ አርፊቾ አውራጃ ወደ ዞኑ መዲና አርባምንጭ በመጓዝ ላይ ነበር።

VOA60 Africa - Mozambique: Riot police fired tear gas to disperse protesters

Mozambique: Riot police fired tear gas to disperse a small crowd in Maputo after two of opposition leader Venancio Mondlane’s associates were shot dead over the weekend. Mondlane had called for a general strike to contest early results showing the ruling Fr
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - Mozambique: Riot police fired tear gas to disperse protesters

Mozambique: Riot police fired tear gas to disperse a small crowd in Maputo after two of opposition leader Venancio Mondlane’s associates were shot dead over the weekend. Mondlane had called for a general strike to contest early results showing the ruling Frelimo party ahead.

VOA60 America - US envoy in Beirut for talks with Lebanese officials

U.S. envoy Amos Hochstein visited Lebanon on Monday amid Biden administration efforts to halt the fighting between Israel and Hezbollah.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - US envoy in Beirut for talks with Lebanese officials

U.S. envoy Amos Hochstein visited Lebanon on Monday amid Biden administration efforts to halt the fighting between Israel and Hezbollah.

VOA60 World - Gulen, powerful cleric accused by Turkey of orchestrating a Turkish coup, dies

Turkish Muslim preacher Fethullah Gulen, who Ankara says was behind a 2016 failed coup against Turkish leader Tayyip Erdogan, has died at the age of 83 in the United States. The cleric had lived in the United States since 1999, when he came to seek medical tr
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Gulen, powerful cleric accused by Turkey of orchestrating a Turkish coup, dies

Turkish Muslim preacher Fethullah Gulen, who Ankara says was behind a 2016 failed coup against Turkish leader Tayyip Erdogan, has died at the age of 83 in the United States. The cleric had lived in the United States since 1999, when he came to seek medical treatment.

በጀርመን እስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ በማሴር የተጠረጠረ ሊቢያዊ በቁጥጥር ስር ዋለ

በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል ተብሎ የተጠረጠረ እና ከእስላማዊ መንግስት ቡድን ጋር ግንኙነት እንዳለው የተገለጸው ሊቢያዊ
የአሜሪካ ድምፅ

በጀርመን እስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ በማሴር የተጠረጠረ ሊቢያዊ በቁጥጥር ስር ዋለ

በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል ተብሎ የተጠረጠረ እና ከእስላማዊ መንግስት ቡድን ጋር ግንኙነት እንዳለው የተገለጸው ሊቢያዊ ተጠርጣሪ እሁድ ፍርድቤት እንደሚቀርብ የጀርመን አቃብያነ ህጎች አስታወቁ።  ስሙ ኦማር ኤ. እንደሆነ የተገለጸው ተጠርጣሪ፣ ቅዳሜ ምሽት በቁጥጥር ስር የዋለው፣ ከጀርመን ዋና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኘው በርናው ከተማ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ መሆኑን የፌደራል አቃቢያነ ህጎች ቢሮ አመልክቷል።  ቢሮው አክሎ፣ ኦማር ኤ. በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ «በጦር መሳሪያ የታገዘ ከፍተኛ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል» የሚል ክስ እንደተመሰረተበት አመልክቷል። የእስላማዊ መንግስት ርዕዮተ ዓለም ደጋፊ መሆኑን የገለጸው አቃቤ ህግ፣ ለጥቃቱ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅትም «ከእስላማዊ መንግስት አባላት ጋር በማህበራዊ ሚዲያ መልዕክት ተለዋውጧል» ብሏል።  በርሊን የሚገኙት የእስራኤል አምባሳደር ሮን ፕሮሶር በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት «የሙስሊም ፀረ-ሴማዊነት፣ ትርክት ብቻ ሳይሆን በዓለም ዙሪያ የሽብር ድርጊቶችን የሚያበረታታ እና የሚያነሳሳ ነው» ብለዋል። አክለውም የእስራኤል ኤምባሲዎች «በዲፕሎማሲው ጦር ሜዳ ግንባር ተሰላፊ ናቸው» ሲሉም አመልክተዋል።  የጀርመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ናንችይ ፌዘር በበኩላቸው፣ በጀርመን የሚገኙ አይሁዳውያንን እና የእስራኤል ተቋማትን መጠበቅ «ከምንም በላይ ቅድሚ የምንሰጠው ነው» ያሉ ሲሆን፣  የሕግ አስከባሪ አካላት ማንኛውንም እስላማዊ፣ ፀረ-ሴማዊ እና ፀረ-እስራኤል ጥቃቶችን ለመከላከል ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረጉ መሆናቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

እስራኤል በባህር ኃይል የንግድ ትርዒት እገዳ ምክንያት በማክሮን ላይ ህጋዊ እርምጃ ልትወስድ ነው

በፓሪስ በሚካሄደው ወታደራዊ የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እስ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በባህር ኃይል የንግድ ትርዒት እገዳ ምክንያት በማክሮን ላይ ህጋዊ እርምጃ ልትወስድ ነው

በፓሪስ በሚካሄደው ወታደራዊ የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፣ መስሪያቤታቸው በፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ላይ ክስ እንዲመሰርቱ ማዘዛቸውን እሁድ እለት አስታውቀዋል።  የእስራኤል ተቋማትን የማገድ ውሳኔው፣ እስራኤል በጋዛ እና ሊባኖን እያካሄደችው ባለው ጦርነት ምክንያት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተባባሰ የሄደው የማክሮን መንግስት ቅሬታ አካል ነው። እ.አ.አ ከህዳር 4 -7 በፓሪስ የሚካሄደው የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት አዘጋጅ ኢዩሮናቫል ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ፣ የፈረንሳይ መንግስት፣ የእስራኤል ልዑካን በትርዒቱ ላይ መሳተፍም ሆነ መሳሪያዎቻቸውን ማሳየት እንደማይችሉ ማሳወቁን አመልክቷል። ውሳኔው ሰባት ተቋማት ላይ ተፅእኖ ማሳደሩንም ጠቅሷል።   ውሳኔውን ተከትሎ ካትዝ በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈረው መልዕክት «የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት፣ በመጪው ወር ፓሪስ ላይ በሚካሄደው የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት ምርቶቻቸውን እንዳያሳዩ በመከልከላቸው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሕጋዊ እና ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ እንዲወስድ መመሪያ ሰጥቻለሁ» ብለዋል።  ካትዝ አክለው «ለሁለተኛ ጊዜ በእስራኤል ተቋማት ላይ የተጣለው እቀባም ሆነ ተቀባይነት የሌላቸው ቅድመ ሁኔታዎች ዲሞራሲያዊ ያልሆኑ ከመሆናቸውም በላይ፣ በሁለት ወዳጅ ሀገሮች መካከል ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው» ያሉ ሲሆን ፕሬዝዳንት ማክሮን ውሳኔያቸውን ሙሉ ለሙሉ እንዲሰርዙ አሳስበዋል። 

እስራኤል በጋዛ ጥቃት 73 ሰዎችን ስትገድል፣ በቤይሩት ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች

እስራኤል በሊባኖስ ዋና ከተማ የሂዝቦላህ «የትዕዛዝ ማዕከል» ነው ባለችው ዒላማ ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ጦርነቱ እሁድ እለት በሁለት ግንባር የተካሄ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በጋዛ ጥቃት 73 ሰዎችን ስትገድል፣ በቤይሩት ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች

እስራኤል በሊባኖስ ዋና ከተማ የሂዝቦላህ «የትዕዛዝ ማዕከል» ነው ባለችው ዒላማ ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ጦርነቱ እሁድ እለት በሁለት ግንባር የተካሄደ ሲሆን፣ በጋዛ ባካሄደችው የአየር ጥቃትም 73 ሰዎች መገደላቸውን የነፍስ አድን ሰራተኞች አስታውቀዋል።  የሂዝቦላህ ጠንካራ ይዞታ በሆነው ደቡባዊ ቤይሩት ላይ ጥቃቱ የተካሄደው፣ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በኢራን የሚደገፈው ቡድን መኖሪያ ቤታቸውን ዒላማ በማድረግ ሊገድሏቸው እንደሞከረ ገልጸው ከከሰሱ በኃላ ነው።  የእስራኤል ጥቃት ሃረት ሄሪክ ውስጥ በአንድ መስጊድ እና ሆስፒታል አቅራቢያ የሚገኝ የመኖሪያ ህንፃ መምታቱን የሊባኖስ ብሐራዊ የዜና ማሰራጫ አስታውቋል።  የእስራኤል ጦር በበኩሉ በቤይሩት የሚገኘውን «የሂዝቦላህ የስለላ ድርጅት ዋና ማዕከል» እና የምድር ውስጥ ጦር መሳሪያ ማከማቻ መምታቱን እና በሌሎች ጥቃቶች ደግሞ ሦስት የሂዝቦላህ ታጣቂዎች መግደሉን አስታውቋል።  እስራኤል ጥቃቱን ካደረሰች ደቂቃዎች በኃላ፣ ከሊባኖስ አቅጣጫ 70 ሚሳይሎች ወደ እስራኤል መተኮሳቸውን እና ሁሉንም አየር ላይ እንዳሉ ማክሸፋቸውንም ጦሩ ጨምሮ ገልጿል።  በሌላ በኩል እስራኤል በጋዛ ሰሜናዊ ግዛት ቤይት ላሃ በተሰኘ አካባቢ፣ መኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 73 ፍልስጠማውያን መገደላቸውን የጋዛ ሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ አስታውቋል።  

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት አለቃቸውን 'ጨካኝ' ሲሉ ከሰሷቸው

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ እሁድ እለት፣ አለቃቸውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ «ጨካኝ» እና «አረመኔ» ሲሉ በ
የአሜሪካ ድምፅ

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት አለቃቸውን 'ጨካኝ' ሲሉ ከሰሷቸው

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ እሁድ እለት፣ አለቃቸውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ «ጨካኝ» እና «አረመኔ» ሲሉ በመንቀፍ፣ ህይወታቸው አደጋ ላይ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።  ጋቻጉዋ ሐሙስ እለት በህግ መወሰኛ ምክርቤት ፊት ከተከሰሱባቸው 11 ክሶች አምስቱ ተቀባይነት በማግኘታቸው ከስልጣናቸው የተነሱ ሲሆን፣ በምትካቸው ሌላ የመሾሙን ሂደት ግን የፍርድ ቤት ውሳኔ አግዶታል።  «ፕሬዝዳንት እንዲሆን የረዳሁት፣ ያመንኩት እና እሱን በመደገፌ የተሳደድኩበት ሰው እንዴት በእኔ ላይ ይህን ላክል ጨካኝ ሊሆን እንደቻለ አስደንግጦኛል» ብለዋል ጋቻጉዋ። የ59 ዓመቱ አዛውንት የተመደቡላቸው የፀጥታ አካላት መነሳታቸውን እና ሁሉም ሰራተኞቻቸው አስገዳጅ እረፍት እንዲወጡ መደረጋቸውንም ገልጸው «በእኔ ላይ ወይም በቤተሰቤ ላይ የሆነ ነገር ቢደርስ፣ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ተጠያቂ መሆን አለባቸው» ሲሉ ተናግረዋል።  ጋቻጉዋ ይህንን ንግግር ያደረጉት፣ በደረታቸው ላይ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ሲታከሙበት ከነበረው ሆስፒታል ከወጡ በኃላ ነው።  «ይህን አይነት መጠን ያለው ጭካኔ አይገባኝም» ያሉት ጋቻጉዋ «አንድ ሰው በህይወቱ እጅግ በጣም መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ባለበት ወቅት እና በህይወት ለመቆየት በሚፍጨረጨርበት ወቅት፣ ሆን ተብሎ እንደዚህ አይነት ጭካኔ ይፈፀምበታል» ብለዋል። 

በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት ተቃጣ

የኢራኑ መሪ ባለፈው ዓመት በጎሮጎርሳዊያኑ ጥቅምት ሰባት ሀማስ የፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ዋናየእቅዱ መስራች የሆኑት የሀማሱ መሪ መገደላቸውን ተከትሎ፤ ሀማስ ከ
የአሜሪካ ድምፅ

በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት ተቃጣ

የኢራኑ መሪ ባለፈው ዓመት በጎሮጎርሳዊያኑ ጥቅምት ሰባት ሀማስ የፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ዋናየእቅዱ መስራች የሆኑት የሀማሱ መሪ መገደላቸውን ተከትሎ፤ ሀማስ ከእስራኤል ጋር የሚያደርገውንትግል እንደሚቀጥል ቃል በገቡበት ወቅት፤ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ መኖሪያ ቤትን ዒላማ ያደረገ የድሮን ጥቃት ምንም ዓይነት ጉዳት ሳያደርስ መክሸፉን የእስራኤል መንግስት ዛሬቅዳሜ ተናግሯል።   በአንጻሩ በጋዛ፣ የሆስፒታል ባለስልጣናት እና የአሶሺየትድ ፕሬስ ዘጋቢ እንደገለፁት  እስራኤል በፈጸመቻቸው የተለያዩ  ጥቃቶች ህጻናትን ጨምሮ በትንሹ 21 ሰዎች ተገድለዋል።   ዛሬ ቅዳሜ ማለዳ ከሊባኖስ አቅጣጫ የመጣውን የሰው አልባ ድሮን ጥቃት የሚያስጠነቅቁ ድምጾች በእስራኤል በከፍተኛ ሁኔታ ሲጮሁ ነበር ያለው የእስራኤል መንግስት ቃል አቀባይ  መግለጫ፤  ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በቂሳሪያ በሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት እሳቸውም ሆኑ ባለቤታቸው እንዳልነበሩ አስታውቆ  በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ብሏል።    በመስከረም ወር የየመን ሁቲ አማፂያን የኔታኒያሁ አይሮፕላን በቴል አቪቭ በሚገኘው ቤን ጉሪዮን አየርማረፊያ ሲያርፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ማስወንጨፋቸው ይታወሳል።   የኔታኒያሁ መኖሪያ ቤትን ዒላማ ካደረገው የድሮን ጥቃት  በተጨማሪ ቅዳሜ ማለዳ ላይ በሰሜንእስራኤል ከሊባኖስ የተነሱ ወደ 55 የሚጠጉ ዒላማዎች ላይ መተኮሱን የእስራኤል ጦር አስታውቋል።የተወሰኑት መክነዋል የተባለ ሲሆን፤ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ እስካሁን  የተገለጸ ነገር የለም።

የቡድን ሰባት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ ተጀመረ

በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየተባባሰ እና የዩክሬን ጦርነት ሦስተኛ ክረምቱን እየያዘ ባለበት በዚህ የውጥረት ወቅት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መከላከ
የአሜሪካ ድምፅ

የቡድን ሰባት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ ተጀመረ

በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየተባባሰ እና የዩክሬን ጦርነት ሦስተኛ ክረምቱን እየያዘ ባለበት በዚህ የውጥረት ወቅት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ በጣሊያን ተጀምሯል።   የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ወቅታዊ ፕሬዝዳንትነቱን የያዘችው ጣሊያን የሰሜን አትላንቲክ የቃልኪዳን ጦር ኔቶ መቀመጫ በሆነችው ኔፕልስ ጉባኤውን እያስተናገደች ነው።   ለኔቶ ሀላፊ ማርክ ሩቴ እና ለአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ሃላፊ ለሆኑት ጆሴፍ ቦሬል እንዲሁም ለጉባኤው ታዳሚዎች አቀባበል ያደርጉት የጣሊያኑ የመከላከያ ሚንስትር ጉዓዶ ክሮሴቶ “ዛሬ እዚህ መሰባሰባችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓታችንን ለመገደብ ለሚጥሩ ሁሉ ጠንካራ መልዕክት ያስተላልፋል ብዬ አምናለሁ” በማለት ተናግረዋል።   ጉባኤው በዋናነት የዩክሬን ጦርነት ላይ ትኩረቱን ቢያደርግም በአፍሪካ እና በፓስፊክ እስያ የጸጥታ ጉዳዮችም ላይ የሚወያይ ይሆናል።  

የኬኒያ ፍርድ ቤት የምክትል ፕሬዝዳንት ምርጫውን አገደ

የኬኒያ ህግ አውጭዎች የሀገሪቱን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጓን በከባድ የስነ ምግባርጉድለት እና ፕሬዚዳንቱን በማቃለል ክስ ከስልጣናቸው እንዲነ
የአሜሪካ ድምፅ

የኬኒያ ፍርድ ቤት የምክትል ፕሬዝዳንት ምርጫውን አገደ

የኬኒያ ህግ አውጭዎች የሀገሪቱን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጓን በከባድ የስነ ምግባርጉድለት እና ፕሬዚዳንቱን በማቃለል ክስ ከስልጣናቸው እንዲነሱ በማድረግ፤ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶለተተኪ ምክትል ፕሬዝዳንት እጩ አድርገው ያቀረቧቸውን በማጽደው ድምጽ ከሰጡ ከአንድ ቀንበኋላ የኬንያ ፍርድ ቤት  አዲሱን ምክትል ፕሬዝዳንት አግዷቸዋል።   ሩቶ ምክትል ፕሬዘዳንት ጋቻጉዋ ከስልጣናቸው እንደተነሱ የምክትል ፕሬዝዳንትነቱን ሥልጣንሹመት ለማካሄድ ጊዜ አላጠፉም።   ተተኪ ፕሬዝዳንት ለመምረጥ ተጨማሪ የ ሁለት ሳምንት ጊዜ የነበራቸው ዊሊያም ሩቶ ምርጫለማድረግ ፣ምክትል ፕሬዝዳንት ጋቻጓን እንዲተኩ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኪቱሬ ኪንዲኪንበፍጥነት ለእጩነት ያቀረቡ ሲሆን ከሰዓታት በኋላ የኪንዲኪ ሹመት ያለምንም ድምጸ ተዐቅቦ እና ተቃውሞ በ236 የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ድምጽ ጸድቋል።   ፍርድ ቤቱ አርብ ዕለት በሰጠው ብይን የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ጋቻጓ በመተካታቸው ዙሪያ  የተወሰደውን እርምጃ በመቃወም ያቀረቡት አቤቱታ “የህዝብ ጥቅም ጥያቄዎችን ዙሪያ ጠቃሚየህግ ጥያቄ አስነስቷል” ብሏል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በሀገራቸው ጸጥታ እያስከበሩ ወደሚገኙ ሀገራቶች ጉብኝት ማድረግ ጀመሩ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዛሬ ቅዳሜ ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል።  የአሁኑ ጉብኝታቸው በሶማሊያ ጸጥታ በሚያስከብሩ አራት ሀገራት ከሚያደርጉት
የአሜሪካ ድምፅ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በሀገራቸው ጸጥታ እያስከበሩ ወደሚገኙ ሀገራቶች ጉብኝት ማድረግ ጀመሩ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዛሬ ቅዳሜ ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል።  የአሁኑ ጉብኝታቸው በሶማሊያ ጸጥታ በሚያስከብሩ አራት ሀገራት ከሚያደርጉት የመጀመሪያው ነው።    ፕሬዝዳንቱ በካምፓላ ከዩጋንዳው አቻቸው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በጋራ ጉዳዮች፣ በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ ሽግግር አትሚስ ዙሪያ እና ቀጠናዊ ሰላምና መረጋጋትን በተመለከተ እንደሚወያዩ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ቤተመንግስት መግለጫ አስታውቋል።    ሀሰን ሼክ መሃሙድ በቀጣይ በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ አባል ሀገራት ወደ ሆኑትን ብሩንዲ፣ ኬኒያ እና ጅቡቲን ይጓዛሉ። የሶማሊያ ፕሬዘዳንት ቃል አቀባይ አብዱልቃድር ዲጌ ለአሜሪካ ድምጽ አፍሪካ ቀንድ ፕሬዘዳንቱ ኢትዮጵያን አይጎበኙም ሲሉ ተናግረዋል።   በሶማሊያ በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ጸጥታ ለማስከበር የተሰማሩ ቢሆንም ነገርግን በጎርጎርሳዊያኑ 2024 መግቢያ ላይ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የተፈራረመችው አጨቃጫቂ ውል ሶማሊያን ሉዓላዊነቴን ጥሳለች በሚል አስቆጥቷታል።   የኢትዮጵያ ሰራዊት በፊታችን ታህሳስ ሙሉ ለሙሉ ከሶማሊያ ለቆ የሚወጣ ሲሆን ሁለት የሶማሊያ ባለስልጣናት ምንጮች ግብጽ በሶማሊያ የአፍሪካ ቀንድ ሰላም አስከባሪ ተልዕኮ አባል ለመሆን ጥያቄ ማቅረቧን አረጋግጠዋል።  የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ አብዱልቃድር ዲጌ በሶማሊያ ቀጣዩ የሰላም አስከባሪ ማን እንደሚሆን መታየቱ ገና እንደቀጠለ ነው ብለዋል።

በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

በዲጂታል፣ ወይም በአጠቃላይ በኢንተርኔት አጠቃቀም ላይ ያለው ነፃነት ለተከታታይ 14 ዓመታት ማሽቆልቆሉን ‘ፍሪደም ሃውስ’ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ዓመታዊ ሪ
የአሜሪካ ድምፅ

በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

በዲጂታል፣ ወይም በአጠቃላይ በኢንተርኔት አጠቃቀም ላይ ያለው ነፃነት ለተከታታይ 14 ዓመታት ማሽቆልቆሉን ‘ፍሪደም ሃውስ’ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ አመልክቷል። በጥናቱ ከተካተቱ ሃገራት ውስጥ 41 በሚሆኑት በያዝነው ዓመት ምርጫ የሚካሄድ በመሆኑ ሁኔታውን አሳሳቢ እንደሚያደርገውና፣ ነጻና ክፍት የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት ዲሞክራሲ እውን እንዲሆን ወሳኝ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል። ኢትዮጵያም በጥናቱ ከተካተቱት ሃገራት አንዷ ስትሆን፣ ኢንተርኔት ሆን ተብሎ ከሚቋረጥበት፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ወይም ሌሎች የግንኙነት መንገዶች ከሚታገዱበት፣ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የመረጃ መረብ ላይ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ምክንያት የአካል ጉዳት ከሚደርስባቸውና ከሚገደሉበት ሃገራት ተርታ ተመድባለች፡፡ ሪፖርቱን የተመለከተው ባልደረባችን እንግዱ ወልዴ፣ ከቪኦኤዋ ቬሮኒካ ባልዴርስ ኤግሌሲያስ ዘገባ ጋራ አጣምሮ ተከታዩን አሰናድቷል።

Get more results via ClueGoal