Ethiopia



የኢትዮጵያንና የአፍሪካ ቀንድን ሁኔታ የዳሰሰው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በኢትዮጵያ እንደሚያደርጉት የሚጠበቀው ጉብኝት፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት፣ በሁለ
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮጵያንና የአፍሪካ ቀንድን ሁኔታ የዳሰሰው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ

የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በኢትዮጵያ እንደሚያደርጉት የሚጠበቀው ጉብኝት፣ ላለፉት ሁለት ዓመታት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረውን የሐሳብ ልዩነት ለማጥበብ የሚደረግ ዲፕሎማሲ አካል መኾኑን፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም፣ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣ ስለ ጉብኝቱ አብራርተዋል፡፡ በኢትዮጵያ እና በጅቡቲ፣ ለአንድ ሳምንት ጉብኝት ያደርጋሉ የተባሉት ልዩ መልዕክተኛው፣ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋራ እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡ በሌላ ዜና፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል የተጀመረው የሰላም ውይይት እንደተቋረጠ መኾኑን፣ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ተናግረዋል፡፡ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ቃል አቀባይም እንዲሁ፣ “ከመንግሥት ጋራ የቀጠለም ኾነ የታቀደ ውይይት የለም፤” ብሏል፡፡ በሌላ በኩል፣ በሁለቱ አካላት መካከል ግጭቶች መቀጠላቸው ይታወቃል፡፡ በዩናይትድ ስቴትስ ቨርጂኒያ የሚገኙት የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢም፣ ትላንት በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሠፈሩት ጽሑፍ፣ “እየተናፈሰ ካለው ወሬ በተፃራሪ፣ በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እና በመንግሥት መካከል፣ የቀጠለም ኾነ የታቀደ ውይይት የለም፤” ብለዋል። አቶ ኦዳ አክለውም፣ አሁን ላይ፣ ሁለተኛ ዙር ንግግር ባይዘጋጅም፣ ለሰላማዊ መፍትሔ ቁርጠኞች እንደኾኑና ወደፊት የሚደረግ ድርድር ወዲያውኑ ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ፣ ከኅብረተሰቡ እና ከልዩ ልዩ ዓለም አቀፍ አካላት፣ ተደጋጋሚ ጥሪዎች እየቀረቡ ቢኾንም፣ ከመጀመሪያው ዙር ውይይት ወዲህ በቀጠሉት ግጭቶች ሳቢያ፣ ስለ ውይይቱ ቀጣይነት የሚጠቁሙ አዝማሚያዎች አልታዩም፡፡ በሌላ በኩል፣ በምዕራብ ኦሮሚያ በቀጠለው ግጭት ምክንያት፣ በአካባቢው ሰብአዊ ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን፣ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ(OCHA)፣ ሰሞኑን ባወጣው የኹኔታ ሪፖርት አመልክቷል፡፡ በሪፖርቱ እንደተገለጸው፣ በግጭቱ ሳቢያ የተፈናቀሉ 859 ሺሕ ያህል ዜጎች፣ በደኅንነት ስጋት ውስጥ ከመኾናቸውም በተጨማሪ፣ የማኅበራዊ እና ሰብአዊ አገልግሎቶችን አያገኙም፡፡ አምባሳደር መለስ፣ በዛሬው መግለጫቸው ያነሡት ሌላው ጉዳይ፣ በሱዳን ያለውን ግጭት በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሰዎችን የተመለከተ ሲኾን፣ እስከ አሁን ገብተዋል ካሏቸው ከ30 ሺሕ በላይ ሰዎች ውስጥ የሚበዙት ኢትዮጵያውያን እንደኾኑ ተናግረዋል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ እንደኾነ የገለጸው ኦቻ በበኩሉ፣ በመተማ ድንበር ብቻ እንኳን፣ ከ33ሺሕ400 በላይ ሰዎች መግባታቸውን አመልክቷል፡፡ በሌላ ዜና፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኰንን፣ ከግንቦት 15 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም. በቻይና ስኬታማ ጉብኝት ማድረጋቸውን የገለጹት አምባሳደር መለስ፣ ለቻይናውያን የዐማርኛ ትምህርትን በመስጠት ላይ በሚገኘው፣ በቤጂንግ የዓለም አቀፍ ጥናት ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጁ፣ ሦስት የዐማርኛ መማሪያ መጻሕፍት ምረቃ ላይ መታደማቸውንም ተናግረዋል፡፡ በዐማርኛ ቋንቋ ትምህርት፣ ለምረቃ የደረሱ ተማሪዎች መኖራቸውንም የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ይህም፣ የሁለቱን ሀገራት፣ የባህል እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እንደሚያጠናክር አስገንዝበዋል፡፡

የወጣቷ መታገት ቤተሰቦቿን አስጨንቋል

የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ እና የዳሽን ባንክ ሠራተኛ የኾነችው እህታችን ጸጋ በላቸው፣ ከሥራ ወጥታ በኪራይ ወደምትኖርበት ቤት በማምራት ላይ ሳለች ከታገተችብን፣ ዛ
የአሜሪካ ድምፅ

የወጣቷ መታገት ቤተሰቦቿን አስጨንቋል

የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ እና የዳሽን ባንክ ሠራተኛ የኾነችው እህታችን ጸጋ በላቸው፣ ከሥራ ወጥታ በኪራይ ወደምትኖርበት ቤት በማምራት ላይ ሳለች ከታገተችብን፣ ዛሬ ዘጠነኛ ቀኗ ቢኾንም፣ የደረሰችበት አልታወቀም፤ ሲሉ፣ ታላቅ እህታቸው ነፃነት በላቸው፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ። የሲዳማ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በበኩሉ፣ ጸጋ በላቸውን ጠልፎ ወስዷል፤ የተባለውን የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ ኮንስታብል የኋላመብራቴ ወልደ ማርያምን ለመያዝ፣ የፖሊስ ቡድን አሠማርቼ አሠሣ እያካሔድኹ ነው፤ ሲል፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቋል። በወይዘሪት ጸጋ በላቸው ላይ በተፈጸመው የጠለፋ ወንጀል ጠረጠርኋቸው ያላቸውን ስምንት ሰዎችንም፣ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያደረገባቸው እንደሚገኝ፣ የቢሮው ሓላፊ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ሴቶች የሕግ ባለሞያዎች ማኅበር፣ በጸጋ በላቸው ላይ የተፈጸመውን የመብት ጥሰት እየተከታተለ እንደኾነ አመልክቷል።

ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂ እና የሩሲያ ፕሬዚደንት ፑቲን ተወያዩ

የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስ
የአሜሪካ ድምፅ

ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂ እና የሩሲያ ፕሬዚደንት ፑቲን ተወያዩ

የሩሲያ ፕሬዚደንት ቭላዲሚር ፑቲን የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን በክሬምሊን ቤተ መንግሥት ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው ባወጡት ቃል ፕሬዚደንት ኢሳይያስ እና ፕሬዚደንት ፑቲን ዛሬ ረቡዕ ከቀትር በኋላ ባደረጉት ቆይታ የአገሮቻቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት፡ ዐለም አቀፍ ጉዳዮች እንዲሁም በጋራ ትኩረት በሚሰጧቸው ሁኔታዎች ዙሪያ በስፋት መወያየታቸውን አስታውቀዋል፡፡ አያያዘውም “የኤርትራ ፕሬዚደንት ኢሳይያስ በሩሲያ ፌዴሬሽን ያደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት ለሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ፕሬዚደንት ፑቲን አስምረውበታል” ብለዋል፡፡ “የሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ርምጃ ሙሉ በሙሉ አመርቂ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ” ፑቲን መናገራቸው አክለው “በመጪው ሐምሌ ወር ሞስኮ በምታስተናግደው ሁለተኛው የሩሲያ እና የአፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ላይ እንዲገኙ ጋብዘዋቸዋል” ብለዋል፡፡ የኤርትራ ፕሬዚደንት በበኩላቸው ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገሮች ከፍተኛ የአጋርነት እና የምክክር ግንኙነት የሚያንጸባርቅ መሆኑን መናገራቸውን የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረ መስቀል አመልክተዋል፡፡

በትግራይ በጦርነቱ ወቅት የወጡ ሕጎች እንዲሻሩ ተጠየቀ

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል፣ የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ከመፈረሙ በፊት፣ ህወሓት ልዩ ልዩ የአስቸኳይ ጊዜ ሕጎች ደንግጎ እንደነበር ያስታ
የአሜሪካ ድምፅ

በትግራይ በጦርነቱ ወቅት የወጡ ሕጎች እንዲሻሩ ተጠየቀ

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል፣ የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ከመፈረሙ በፊት፣ ህወሓት ልዩ ልዩ የአስቸኳይ ጊዜ ሕጎች ደንግጎ እንደነበር ያስታወሰው ፓርቲው፣ ኾኖም ሒደቱ፣ ሕጋዊነትን የተከተለ እንዳልነበረና የሕጎቹ ይዘትም፣ ከክልሉ እና ከፌዴራሉ ሕገ መንግሥቶች ጋራ እንደማይጣጣም ገልጿል፡፡ ሕጎቹ ሥራ ላይ በዋሉባቸው ጊዜያትም፣ የተለያዩ ችግሮች ማስከተላቸውን ፓርቲው አመልክቷል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ እነዚኽን ሕጎች እንዲሽራቸው የጠየቀው ፓርቲው፣ ካልሆነ ግን፣ ጉዳዩን ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ አካል እንደሚወሰደው፣ የፓርቲው የሕግ እና የሥነ መንግሥት ክፍል ሓላፊ አቶ ተስፋኣለም በርኸ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ስለ ጉዳዩ፣ ከትግራይ ክልል ፍትሕ ቢሮ አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡ ማንነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን አንድ ከፍተኛ የሥራ ሓላፊ ግን፣ ቢሮው ሕጎቹን እየሻረ፣ ወደ መደበኛው የፍትሕ አሠራር ለመግባት እንቅስቃሴ መጀመሩንና በሕጎች ተከሠው ስለተፈረደባቸው ሰዎችም፣ የባለሞያዎች ቡድን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ እንደኾነ ጠቁመዋል፡፡

በጦርነት የተጎዳውን የዐማራ ክልል መልሶ ለመገንባት ከግማሽ ትሪሊዮን በላይ ብር ያስፈልጋል ተባለ

በዐማራ ክልል፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እና በሌሎች ግጭቶች ሳቢያ የደረሰውን ውድመት ተከትሎ፣ 12 ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ፥ በከፋ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ፣ በ
የአሜሪካ ድምፅ

በጦርነት የተጎዳውን የዐማራ ክልል መልሶ ለመገንባት ከግማሽ ትሪሊዮን በላይ ብር ያስፈልጋል ተባለ

በዐማራ ክልል፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እና በሌሎች ግጭቶች ሳቢያ የደረሰውን ውድመት ተከትሎ፣ 12 ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ፥ በከፋ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ፣ በክልሉ፣ በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤቱ ዋና ዲሬክተር ዶር. አባተ ጌታሁን፣ ዛሬ፣ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ በነበራቸው ቆይታ፣ ከሁለተኛው ዙር የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በኋላ የተደረገውን ጥናት መነሻ በማድረግ፣ በቅርቡ በተደረገው የክለሳ ጥናት፣ ክልሉ፥ በጦርነቱ እና ከጦርነቱ ጋራ በተያያዙ ግጭቶች የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት እና ለማቋቋም፣ 522 ቢልዮን ብር እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል፡፡ ለመልሶ ግንባታ የተጠየቀው ገንዘብ፣ እጅግ ከፍተኛ በመኾኑ፣ መንግሥታዊም ኾኑ መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች፣ የርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉ፣ የጽ/ቤቱ ዋና ዲሬክተር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በታጣቂዎች በታጎለው የምዕራብ ኢትዮጵያ የመጓጓዣ አገልግሎት ነዋሪዎች ለእንግልት እንደተጋለጡ ተናገሩ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞኖች መካከል፣ የመጓጓዣ አገልግሎት ከተቋረጠ ከሦስት ወራት በላይ ማስቆጠሩን፣ የአሜሪካ ድ
የአሜሪካ ድምፅ

በታጣቂዎች በታጎለው የምዕራብ ኢትዮጵያ የመጓጓዣ አገልግሎት ነዋሪዎች ለእንግልት እንደተጋለጡ ተናገሩ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ እና በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞኖች መካከል፣ የመጓጓዣ አገልግሎት ከተቋረጠ ከሦስት ወራት በላይ ማስቆጠሩን፣ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እና ነጋዴዎች ገለጹ። አስተያየት ሰጪዎቹ፣ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊትን ማስፈራሪያ እና ዝርፊያ በመስጋት አገልግሎቱ መቋረጡን ሲገልጹ፣ ይህም፣ ኅብረተሰቡን ለእንግልት ማጋለጡንና የፍጆታ እቃዎችን ወደ አካባቢው ለማስገባት አስቸጋሪ ኹኔታ በመፍጠሩ የዋጋ ንረትን ማስከተሉን፣ አክለው ተናግረዋል። የዞኑ ኮምዩኬሽን መምሪያ በበኩሉ፣ አገልግሎቱ እንዲቋረጥ መንሥኤ የኾነው፣ በአካባቢው የሚደረገው የታጣቂዎች እንቅስቃሴ ስለመኾኑ፣ ከነጋዴዎች ማረጋገጡን አስታውቋል። የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰሎሞን ታምሩ በበኩላቸው፣ “ሸኔ” ብለው የጠሩትና በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት፣ የዝርፊያ ተግባር በመፈጸሙ፣ ባለሀብቶች በመንገዱ ላይ መንቀሳቀስ በመስጋታቸው፣ የመጓጓዣ አገልግሎቱ መቋረጡን ገልጸው፣ የመንግሥት ኃይሎች ወደ አካባቢው እንደሚሠማሩ አስታውቀዋል። በተጨማሪም፣ የኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ጋምቤላ ክልሎች፣ የጋራ ሰላም እና ልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት፥ ከሚመለከታቸው የምዕራብ ወለጋ እና የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አመራሮች ጋራ ችግሩን ለመቅረፍ እየሠሩ ስለመኾኑ ገልጿል። በሌላ በኩል፣ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ፣ በአካባቢው፥ ታጣቂዎቻቸው ከመንግሥት ጋራ ውጊያ እያካሔደ በመኾኑ፣ የኅብረተሰቡ እንቅስቃሴ መገታቱን ጠቅሰው፣ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ግን በአካባቢው ዝርፊያ አልፈጸመም፤ አይፈጽምም፤” ሲሉ አስተባብለዋል።

የሱዳን ጦር ከተፋላሚው የፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋራ ንግግሩን አቋረጠ

የሱዳን ጦር ሠራዊት፣ አገሪቱን በበላይነት ለመቆጣጠር ለሳምንታት ሲዋጋ ከሰነበተው የፈጥኖ ደራሹ ኃይል ጋራ የጀመረውን ንግግር ማቋረጡን፣ የሠራዊቱ ቃል አቀ
የአሜሪካ ድምፅ

የሱዳን ጦር ከተፋላሚው የፈጥኖ ደራሽ ጦር ጋራ ንግግሩን አቋረጠ

የሱዳን ጦር ሠራዊት፣ አገሪቱን በበላይነት ለመቆጣጠር ለሳምንታት ሲዋጋ ከሰነበተው የፈጥኖ ደራሹ ኃይል ጋራ የጀመረውን ንግግር ማቋረጡን፣ የሠራዊቱ ቃል አቀባይ፣ ዛሬ ረቡዕ አስታውቋል፡፡ ውሳኔው፥ ሁለቱም ወገኖች፣ ሱዳንን ወደ ከፋ ቀውስ የከተታትን ግጭት እንዲያቆሙ ሲያደራድሩ ለቆዩት፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ሳዑዲ አረቢያ፣ “ትልቅ ክስረት ነው፤” ተብሏል፡፡ የሱዳን ጦር ቃል አቀባይ፣ ብርጋዴየር ጀነራል ናቢል አብደላ፣ ለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ ርምጃው፥ የፈጥኖ ደራሹ ኃይሎች፣ የሰብአዊ ተኩስ አቁም ስምምነቱን በተደጋጋሚ በመጣሳቸው እና በዋና ከተማዋ ካርቱም የሚገኙ ሆስፒታሎችንና የሲቪል መሠረተ ልማቶችን በተከታታይ ይዘው መቆየታቸውን በመቃወም የተወሰደ ርምጃ ነው፤ ብለዋል፡፡ አብደላ አክለውም፣ ተጨማሪ ርምጃዎች ላይ ከመወያየት በፊት፣ ሠራዊቱ፥ የተኩስ አቁሙ ዝርዝር ነጥቦች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥ ይፈልጋል፤ ብለዋል፡፡ ተፋላሚዎቹን ወገኖች ሲሸመግሉ ከቆዩት ሳዑዲ አረብያ ወይም ዩናይትድ ስቴትስ፣ ስለ ጉዳዩ ወዲያኑ የተሰጠ አስተያየት የለም፡፡ እስከ አሁን፣ በሁለቱ ወገኖች መካከል፣ በተለያዩ መንገዶች የተጣሱ ሰባት የተኩስ አቁም ስምምነቶች መደረጋቸው ተመልክቷል፡፡ የሱዳን ጦር ያሳለፈውን የንግግር ማቋረጥ ውሳኔ አስመልክቶ፣ የፈጥኖ ደራሹ ጦር በሰጠው ምላሽ፣ “የሳዑዲ አረብያንና የዩናይትድ ስቴትስን ተነሣሽነት፣ ያለምንም ቅድመ ኹኔታ እደግፋለኹ፤” ማለቱን፣ የአሶሺየትድ ፕሬስ ዘገባ አመልክቷል፡፡

ላቭሮቭ ምዕራቡ ዓለም በዩክሬን “የዘር ማጥፋትን እየደገፈ ነው” አሉ

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቫሮቭ፣ የምዕራቡ ዓለም፣ ለፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜለነስኪ “የሰላም ዕቅድ” በሚሰጠው ድጋፍ፣ ዩክሬን ውስጥ፣ “የዘ
የአሜሪካ ድምፅ

ላቭሮቭ ምዕራቡ ዓለም በዩክሬን “የዘር ማጥፋትን እየደገፈ ነው” አሉ

የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቫሮቭ፣ የምዕራቡ ዓለም፣ ለፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜለነስኪ “የሰላም ዕቅድ” በሚሰጠው ድጋፍ፣ ዩክሬን ውስጥ፣ “የዘር ማጥፋትን እየደገፈ ነው፤” ሲሉ፣ ትላንት ማክሰኞ፣ ብሩንዲ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናገሩ፡፡ ላቭሮቭ፣ እ.ኤ.አ. ግንቦት 31፣ ቡጅንቡራ ውስጥ ከብሩንዲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አልበርት ሺንጊሮ ጋራ በሰጡት መግለጫ፣ የዩክሬኑ “የሰላም ዕቅድ”፣ በምሥራቅ ዩክሬንና ክራይሚያ ውስጥ፣ “የሩሲያ የኾነውን ሁሉንም ነገር እያወደመ ነው፤” ብለዋል፡፡ ላቭሮቭ ይህን ስላሉበት ምክንያት አስረጅ አልጠቀሱም፡፡ ይኹን እንጂ ሩሲያ፣ ምዕራቡ ዓለም፥ በምሥራቅ ዶናባስ ግዛት እና በሌሎች አካባቢዎች፣ የሩሲያ ቋንቋ ተናጋሪ በኾኑ ዩክሬናውያን ላይ ስለሚፈጸመው ግድያ ችላ ይላል፤ የሚል ክሥ፣ ለረጅም ጊዜ ስታሰማ መቆየቷን፣ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የዜለነስኪ “የሰላም ዕቅድ”፥ የሩሲያ ጦር፣ እ.ኤ.አ. በ2014፣ ሞስኮ በኃይል ወደ ራሷ የቀላቀለቻትን ክራይሚያን ጨምሮ፣ ከሁሉም የዩክሬን ግዛቶች ለቆ እንዲወጣ የሚሻ ነው፡፡ ብሩንዲ የሚገኙት ላቭሮቭ፣ በተያዘው ዓመት፣ ቢያንስ አፍሪካን ሦስት ጊዜ ያህል መጎብኘታቸው ተነግሯል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ፣ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሞትሮ ኩሌባም፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሩዋንዳንና ሞዛቢክን የጎበኙት፣ ባለፈው ሳምንት እንደነበር፣ በሮይተርስ ዘገባ ተመልክቷል፡፡

VOA60 World - AP: At least 60 children died over the past six weeks in Khartoum orphanage

Sudan: An Associated Press report shows at least 60 infants, toddlers and older children have died over the past six weeks while trapped in harrowing conditions in an orphanage in Khartoum as fighting raged outside.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - AP: At least 60 children died over the past six weeks in Khartoum orphanage

Sudan: An Associated Press report shows at least 60 infants, toddlers and older children have died over the past six weeks while trapped in harrowing conditions in an orphanage in Khartoum as fighting raged outside.

VOA60 America - US Lawmakers to Vote on Debt Ceiling Deal

The U.S. House of Representatives is expected to vote Wednesday on legislation to suspend the federal debt ceiling. Less than a week remains before the government risks running out of money to pay its bills.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - US Lawmakers to Vote on Debt Ceiling Deal

The U.S. House of Representatives is expected to vote Wednesday on legislation to suspend the federal debt ceiling. Less than a week remains before the government risks running out of money to pay its bills.

VOA60 Africa - Sudanese Army Walks Away From Cease-Fire Talks with Paramilitary Forces

Sudan: Images posted on social media Tuesday show fighters from the paramilitary Rapid Support Forces clashing with Sudanese Armed Forces in Khartoum despite the cease-fire extension pledges by the two warring generals made earlier this week.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - Sudanese Army Walks Away From Cease-Fire Talks with Paramilitary Forces

Sudan: Images posted on social media Tuesday show fighters from the paramilitary Rapid Support Forces clashing with Sudanese Armed Forces in Khartoum despite the cease-fire extension pledges by the two warring generals made earlier this week.

ስጦታቸውን እንስጣቸው 

እምነቴ ድል ነሳ፣ «ስጦታቸውን እንስጣቸው» የተሰኘ፣ በጡት ማጥባት ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ደራሲ ናት። እምነቴ፣ ከጊዜው ቀድሞ የተወለደ ልጇ፣ መሠረታዊ የ
የአሜሪካ ድምፅ

ስጦታቸውን እንስጣቸው 

እምነቴ ድል ነሳ፣ «ስጦታቸውን እንስጣቸው» የተሰኘ፣ በጡት ማጥባት ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ደራሲ ናት። እምነቴ፣ ከጊዜው ቀድሞ የተወለደ ልጇ፣ መሠረታዊ የእድገት መመዘኛዎችን እንዲያሟላ ለማድረግ መፍትሔ በምትሻበት ወቅት ያገኘችው ምላሽ፣ የጡት ወተትን በደንብ ማጥባት የሚለው ነበር። ይኹን እንጂ፣ ጡት ማጥባት፥ እውቀትንና ጥንቃቄን የሚሻ እንደኾነም መማሯንም ትገልጻለች። የትምህርቷን ውጤታማነት ለማረጋገጥም፣ ዕለት ዕለት ማስታወሻ ትወስድ እንደነበር ትገልጻለች። ቆይታ፣ በልጇ ላይ ለውጥን ያየችው እምነቴ፣ ይህን እውቀቷንና ግንዛቤዋን በመጽሐፍ አሳትማለች። ባለፉት ዓመታት፣ በተለያዩ የሕክምና ጣቢያዎች ውስጥ፣ ስለ ጡት ማጥባት፣ በበጎ ፈቃድ ለእናቶች ግንዛቤ ለማስጨበጥ፣ አጫጭር ሥልጠናዎችን ስትሰጥ መቆየቷን ትናገራለች። በተጨማሪም፣ በሥነ ምግባር እና በታሪክ ላይ የሚያተኩሩ ሌሎች ሁለት መጻሕፍትንም ለኅትመት ብርሃን አብቅታለች።

በመንግሥት የቀረበው የ28 ቢሊዮን ዶላር የጦርነት ኪሳራ “ገለልተኛ እይታ እንደሚያስፈልገው ባለሞያዎች ተናገሩ

የኢትዮጵያ መንግሥት፣ መነሻውን በትግራይ ክልል ባደረገው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ የ28 ቢሊዮን ዶላር ወይም በወቅቱ ምንዛሪ ከ1ነጥብ5 ትሪሊዮን ብር በላይ
የአሜሪካ ድምፅ

በመንግሥት የቀረበው የ28 ቢሊዮን ዶላር የጦርነት ኪሳራ “ገለልተኛ እይታ እንደሚያስፈልገው ባለሞያዎች ተናገሩ

የኢትዮጵያ መንግሥት፣ መነሻውን በትግራይ ክልል ባደረገው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ የ28 ቢሊዮን ዶላር ወይም በወቅቱ ምንዛሪ ከ1ነጥብ5 ትሪሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን፣ ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በይፋ ባወጣው ዳሰሳዊ ጥናቱ አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ምሁራንና የምጣኔ ሀብት ባለሞያዎች፥ ዶ/ር አክሎግ ቢራራ፣ ዶ/ር ጉቱ ቴሶ እና አቶ እምነት ነጋሽ፣ ይፋ የተደረገው ጥናት፥ ተኣማኒነት እና ገለልተኝነት የጎደለው፣ ተጠያቂነትንም የማያመለክት እንደኾነ ተችተዋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ፣ ባለፈው ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ.ም.፣ የመሥሪያ ቤታቸውን የዘጠኝ ወራት የሥራ ክንውን ሪፖርት፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት፣ ለሁለት ዓመት የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ የ28 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ማድረሱን ገልጸዋል፡፡ በሚኒስትሩ ሪፖርት የተጠቀሰውን የጦርነት ኪሳራ መጠን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡት፣ በዓለም ባንክ አማካሪነት ለረጅም ዓመታት ያገለገሉት የምጣኔ ሀብቱ ባለሞያ ዶ/ር አክሎግ ቢራራ፣ “አገሪቱን እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ነው፤« ይላሉ፡፡ ጦርነቱ ለወደፊትም ገና ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍል ያመለከቱት ዶ/ር አክሎግ፣ አገሪቱ እስከ ዛሬ ታገኘው ከነበረው ገቢ ጋራ በማነጻጸር፣ የደረሰውን ጉዳት አብራርተዋል። ይህ ጦርነት እስከ ዛሬ ከነበሩት ጦርነቶች የተለየ ነው፡፡ ከባዕድ አገር ጋራ ሳይኾን፣ ከአንድ ቋት ጥሪት ተካፍለው በተዋጉ የአንድ ሕዝብ ወገኖች መካከል የተደረገ ጦርነት እንደነበረ የሚገልጹት፣ የምጣኔ ሀብት ባለሞያው ዶ/ር ጉቱ ቴሶ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ፣ ባለፉት 15 ዓመታት፣ በተለይ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ መጠነኛ የኢኮኖሚ እመርታዎችን ያሳየችበት፣ የተወሰኑ ኢንዱስትሪያል ፓርኮችን በመክፈት፣ የውጭ ባለሀብቶችን መሳብ የቻለችበት ወቅት እንደነበረ፣ ያወሱት ዶ/ር ጉቱ “ይህ ጦርነት፣ »በዚያ ወቅት ያተረፍናቸውን ግኝቶች ሁሉ ይዞት ጠፋ፤" ብለዋል። በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፈሰር የነበሩትና በተለይም በትግራይ ክልል ላይ በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎችን በሚያወጣው ቤልጅየም ገንት ዩኒቨርሲቲ፣ በምርምር ሥራ እና በሦስተኛ ዲግሪ ጥናት ላይ የሚገኙት አቶ እምነት ነጋሽ፣ የደረሰው ጉዳት፣ በገንዘብ እና በንብረት ውድመት ብቻ የሚተመን አለመኾኑን ይናገራሉ፡፡ የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ፣ ተቋማቸው፥ መነሻውን በትግራይ ክልል ባደረገው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት፣ የደረሰውን ጉዳት እና የመልሶ ግንባታ ፍላጎት የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት(Damage and Needs Assessment) በማከናወን፣ የጥናቱን ውጤት ለመንግሥት እንዳቀረበ መናገራቸውን፣ የአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል፡፡ አቶ እምነት ነጋሽ፣ በጦርነቱ ጉዳት መድረሱን ተቀብለው፣ ጥናቱ ግን፣ ታማኝነት የጎደለውና በገለልተኛ ወገን ያልተዘጋጀ መኾኑን በመጠቅስ ይከራከራሉ፡፡ ዶ/ር አክሎግ በበኩላቸው፣ ለዚኽ አውዳሚ ጦርነት የቁጥሩ መብዛት እና ማነስ ሳይኾን፣ ሓላፊነት እና ተጠያቂነት ያለበት ማን ነው? ብለን ልንጠይቅ ይገባል፤ ይላሉ፡፡ “ይህን ያህል ገንዘብ በጦርነቱ ካወጣን በኋላ፣ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ መጠየቃችን፣ ተመልሰን ወደዚያው ጦርነት ውስጥ ላለመግባታችን ዋስትናችን ምንድነው?” ብለው ይከራከራሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት ለመቀልበስና ከጦርነት በፊት ወደነበረበት ኹኔታ ለመመለስ እንዲቻል፣ እ.ኤ.አ. ከ2023 እስከ 2028 ድረስ የሚቆይ፣ የአምስት ዓመታት የመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ አገራዊ የዕቅድ ማኅቀፍ ማዘጋጀቱን፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ፣ ለምክር ቤቱ የፕላን የበጀት እና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ማስታወቃቸው ተነግሯል። በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥም፣ የደረሰውን ጉዳት መጠንና የመልሶ ግንባታ ፍላጎት የሚገልጽ ዝርዝር መረጃ ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስትሩ፣ በሰጡት መግለጫቸው ማመልከታቸው ተዘግቧል፡፡ /የባለሞያዎችን ሙሉ አስተያየት ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ይከታተሉ/

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከሦስት ሺሕ በላይ መምህራንና ተማሪዎች መሞታቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ በትግራይ ክልል ውስጥ፣ ከ3ሺሕ800 በላይ መምህራንና ተማሪዎች ሕይወት ማለፉን፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡ ተ
የአሜሪካ ድምፅ

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከሦስት ሺሕ በላይ መምህራንና ተማሪዎች መሞታቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ በትግራይ ክልል ውስጥ፣ ከ3ሺሕ800 በላይ መምህራንና ተማሪዎች ሕይወት ማለፉን፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡ ተቋሙ፣ ጦርነቱ በክልሉ ስላደረሰው ጉዳት በአካሔደው የዳሰሳ ጥናት፣ በትምህርት ሥርዐቱም ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን አመልክቷል፡፡ የጉዳት መጠኑ፣ በቅርቡ በተጀመረው የመማር ማስተማር ሒደት ላይ ከፍተኛ እክል እንደፈጠረ በተቋሙ የተገለጸ ሲኾን፣ የክልሉ የትምህርት ቢሮ በበኩሉ፣ የሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ አለማድረጋቸውን በመጥቀስ ወቀሳ አሰምቷል፡፡ የተቋሙ ዋና እንባ ጠባቂ ዶ/ር እንዳለ ኃይሌ፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፥ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከማይቆጣጠራቸው 26 ወረዳዎች ውጪ ባሉት የክልሉ አካባቢዎች፣ እስከ ወርኀ ነሐሴ 2013 ዓ.ም. ድረስ ብቻ ያለውን የጦርነት ጉዳት ያካተተ ጥናት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በጦርነቱ፥ በሺሕዎች የሚቆጠሩ መምህራንና ተማሪዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ መረጋገጡን የጠቀሱት ዋና እንባ ጠባቂው፣ ውድመቱ፥ በመማር ማስተማር ሒደቱም ላይ፣ አሉታዊ ተጽእኖ መፍጠሩን አመልክተዋል፡፡ የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሓላፊ ዶር. ኪሮስ ጉዑሽ በበኩላቸው፣ በጥናቱ ከተጠቀሰው ከነሐሴ 2013 ዓ.ም. በኋላም፣ በክልሉ በተካሔደ ጦርነት፣ ብዙ ውድመት መድረሱን ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ ጥናት እንደሚያሳየው፣ እስከ ነሐሴ 2013 ዓ.ም. ድረስ፣ 88 ከመቶ የሚኾኑት የመማሪያ ክፍሎች በሙሉ እና በከፊል ተጎድተዋል፤ 96 ከመቶ የሚኾኑት የተማሪዎች መቀመጫ ዴስኮች ወድመዋል፤ 95ነጥብ8 ከመቶ የመማሪያ ጥቁር ሰሌዳዎችም አልተገኙም፡፡ ይኸው የጉዳት መጠን፣ በቅርቡ በተጀመረው የመማር ማስተማር ሒደት ላይ እክል እንደፈጠረ፣ ዋና እንባ ጠባቂው ዶ/ር እንዳለ ኃይሌ ያስረዳሉ፡፡ በትግራይ ክልል የትምህርት ዘርፍ የደረሰው ውድመት፣ ግዙፍ እንደኾነ የሚናገሩት የቢሮ ሓላፊው ዶር. ኪሮስ ጉዑሽ፣ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ “የተማሪዎች አፈጻጸም ዝቅተኛ ነው፤ የትምህርት ጥራት ወረደ፤ ሲባል እንሰማለን፤ በትግራይ ግን ይህን መጠየቅ ቅንጦት ነው፤” ብለዋል፡፡ የሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ትምህርት መጀመራችንን አይተው ግብአት በማቅረብ ያግዙናል ብለን ተስፋ ብናደርግም፣ እስከ አሁን ድረስ፣ በተግባር ያየነው ነገር የለም፤ ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ ዶር. እንዳለም፣ ይህን ችግር ለመፍታት፣ የሁሉም አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አስተያየት የሰጡን የትምህርት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ዓመለ ወርቅ ሕዝቅኤል፣ መሥሪያ ቤታቸው፥ ወደ ትግራይ ክልል የትምህርት ቁሳቁስ ለመላክ በዝግጅት ላይ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡ መነሻውን በትግራይ ክልል በአደረገው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት፣ በክልሉ የትምህርት ዘርፍ ላይ ምን ያህል አጠቃላይ ውድመት እንደደረሰ፣ እየተጠና እንደኾነና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ፣ ዶር. ኪሮስ ጉዑሽ አክለው ገልጸዋል፡፡

ወላጆች በግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሬ ምሬታቸውን እየገለጹ ነው

በዐዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች፣ ለመጪው ዓመት የትምህርት ቤት ክፍያ፣ ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ ጭማሬ ለማድረግ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገ
የአሜሪካ ድምፅ

ወላጆች በግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሬ ምሬታቸውን እየገለጹ ነው

በዐዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች፣ ለመጪው ዓመት የትምህርት ቤት ክፍያ፣ ከ20 እስከ 100 በመቶ የሚደርስ ጭማሬ ለማድረግ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል። በርካታ ወላጆች፣ “የኑሮውን ኹኔታ ያላገናዘበ ነው” ሲሉ የጠሩትን ጭማሬ ሲቃወሙ፣ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባና ያለአግባብ የታቀደውን ክፍያ እንዲያስቆም ጠይቀዋል። በዐዲስ አበባ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች፣ የወርኀዊ ክፍያ ጭማሬ ዕቅዳቸውን ማቅረብ የጀመሩት፣ በሚያዝያ ወር ላይ ነው። በርካታ ወላጆች ግን ዕቅዱን ተቃውመዋል። የዐዲስ አበባ ከተማ የትምህርት እና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን በበኩሉ፣ ከወላጆች ጋራ በቂ ውይይት ሳይደረግ፣ የጭማሬ ዕቅዱን መተግበር እንደማይቻል በማሳሰቡ፣ ትምህርት ቤቶቹ ከወላጆች ጋራ የተለያዩ ስብሰባዎችን ሲያካሒዱ ቆይተዋል። ወላጆች ከየትምህርት ቤቶቹ አመራሮች ጋራ ባካሔዷቸው ስብሰባዎች፣ አንዳንድ የተጋነኑ ጭማሬዎች በተወሰነ መልኩ እንዲቀንሱ ቢያግዝም፣ አጥጋቢ ስምምነት ላይ ለመድረስ አለማስቻሉን ወላጆች በምሬት ይገልጻሉ። ሦስት ልጆቻቸውን ፊውቸር ታለንት አካዳሚ በተሰኘው ትምህርት ቤት የሚያስተምሩትና በመጪው ዓመትም አራተኛ ልጃቸውን ትምህርት ለማስጀመር መዘጋጀታቸውን የገለጹልን አቶ ለታሪክ ብሩ፣ ትምህርት ቤቱ በተማሪዎች ክፍያ ላይ 75 በመቶ ለመጨመር ዐቅዶ እንደነበር አውስተው፣ ከወላጆች ጋራ በተደረገው ውይይት፣ ጭማሬው፥ ከ20 እስከ 30 በመቶ እንዲኾን መስማማታቸውን ያስረዳሉ። የዋና መዲናዪቱ የትምህርት ቢሮ ተወካዮች በተገኙበት፣ ወላጆች ያቀረቡት የማሻሻያ ሐሳብ ግን፣ በትምህርት ቤቱ ተቀባይነትን አላገኘም። ወላጆች በመጪው ዓመት፣ በተማሪዎች ክፍያ ላይ 55 በመቶ ጭማሬ እንዲያደርጉ ትምህርት ቤቱ አስታውቋል። በፊውቸር ታለንት ትምህርት ቤት፣ የወላጅ ኅብረት ኮሚቴ ውስጥ ለአምስት አመት ማገልገላቸውን የሚገልጹት አቶ ለታሪክ፣ ጭማሬው፣ ከወላጆች ዐቅም በላይ ነው፤ ይላሉ። የከባድ መኪና አሽከርካሪ የነበሩትና አሁን በግል ሥራ የሚተዳደሩት አቶ ተሾመ ገብረየስም፣ ሁለት የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍሎች ተማሪዎች ልጆቻቸውን፣ በዚኹ ፊውቸር ታለንት ትምህርት ቤት ያስተምራሉ። እስከ አሁን በነበረው ተመን፣ በተርም(በሁለት ወር ከዐሥራ አምስት ቀን) 10ሺሕ 24 ብር ሲከፍሉ ቢቆይም፣በትምህርት ቤቱ ዕቅድ የተወሰነው 55 በመቶ ጭማሬ ግን፣ የወላጆችን ዐቅም ያገናዘበ አለመኾኑን በምሬት ያስረዳሉ። በዐዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ 1ሺሕ558 የግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ፣ 1ሺሕ 257 የሚኾኑቱ፣ በመጪው ዓመት የትምህርት ዘመን የክፍያ ጭማሬ ለማድረግ ማቀዳቸውን፣ የዐዲስ አበባ የትምህርት እና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል። ለጭማሬው በመነሻነት የሚያቀርቡትም፥ የቤት ኪራይ፣ የወረቀት እና የመሳሰሉት ግብዓቶች ዋጋ መናርንና የመምህራን ደመወዝ ጭማሬን ናቸው። አቶ ለታሪክ እንደሚያስረዱት ግን፣ ከፍተኛ ጭማሬ እያደረጉ ካሉት ትምህርት ቤቶች አንዳንዶቹ፣ የራሳቸው ሕንፃ ያላቸው ጭምር በመኾናቸው፣ የተጠቀሱት ምክንያቶች ተቀባይነት እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ በታቀደው የክፍያ ጭማሬ፣ የመምህራን ደመወዝ ማሻሻያው፣ እዚኽ ግባ የሚባል እንዳልኾነ አመልክተዋል። በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ኢትዮ-ብሔራዊ ትምህርት ቤት፣ ያቀደውን የ30 በመቶ ጭማሬ አስመልክቶ፣ ከወላጆች ጋራ ሁለት ጊዜ ስብሰባ ቢያካሒድም ያለስምምነት ተበትኗል። ኾኖም፣ ባለፈው ሳምንት ለወላጆች በላከው የውሳኔ ደብዳቤ፣ በመጪው ዓመት ወላጆች አሁን በሚከፍሉት ክፍያ ላይ 30 በመቶ እንደሚጨምሩ በመግለጽ፣ ዕቅዱን ማጽናቱን አሳውቋል። የስድስተኛ፣ የሰባተኛ እና የስምንተኛ ክፍል ልጆቻቸውን በትምህርት ቤቱ የሚያስተምሩት ወይዘሮ ትዕግሥት ተስፋዬ፣ እጅግ ከባድ ውሳኔ ከፊታቸው እንደሚጠብቃቸው በኀዘን ገልጸውልናል። “ኢትዮ-ብሔራዊ ትምህርት ቤት፣ በክፍለ ከተማው ካሉ ትምህርት ቤቶች የተሻለ ጥራት ያለውና በትምህርት አሰጣጡም የተመሰገነ ነው፤” የሚሉት ወይዘሮ ትዕግሥት፣ ወላጆች የተለየ የገቢ ጭማሬ ባላገኙበትና የኑሮ ውድነቱ ከፍተኛ ጫና በፈጠረበት በአሁኑ ወቅት፣ ትምህርት ቤቱ የወሰነው የክፍያ ጭማሬ፣ በርካታ የማኅበረሰቡን አባላት እንዳስቆጣ ተናግረዋል። የዐዲስ አበባ ትምህርት እና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን፣ የግል ትምህርት ቤቶቹ እያሳለፉ ባሉት ውሳኔ ዙሪያ ምን አስተያየት እንዳለው ለመጠየቅ በተደጋጋሚ ብንሞክርም ምላሽ አላገኘንም። ኾኖም፣ ወላጆች ከመንግሥት ምን ይጠብቃሉ? ስንል የጠየቅናቸው ወይዘሮ ትዕግሥት፣ “አሁንማ ረፍዷል” የሚል፣ በቅሬታ እና ቀቢጸ ተስፋ የተመላ ምላሽ ነው የሰጡን። በሌላ በኩል፣ የክፍያ ጭማሬ እንደሚያደርጉ ካሳወቁ ትምህርት ቤቶች ውስጥ፣ 1ሺሕ31 የሚኾኑቱ፣ ከወላጆች ጋራ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል፡፡ ከእነዚኽ ትምህርት ቤቶች አብዛኞቹ፣ ከ20 እስከ 60 በመቶ ጭማሬ ለማድረግ ከወላጆች ጋራ መስማማታቸውን አመልክቷል። ጭማሬውን መክፈል የሚችሉ ወላጆች፣ ልጆቻቸውን በትምህርት ቤቶቹ እያስተማሩ ሲቀጥሉ፣ ያልቻሉቱ ደግሞ፣ ልጆቻቸውን፥ ዐቅማቸው ወደሚፈቅድበት ትምህርት ቤት እንዲያዛውሩ ነው የተነገራቸው።

በኦሮሚያ ለተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋ የመንገድ ጥበት እና ብልሽት ተጠቃሽ መኾኑ ተገለጸ

· 20 የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሞቱበት ጠባቡ “ወሻ” መንገድ ማሳያ ኾኗል፤ በኦሮሚያ ክልል፣ በ2015 ዓ.ም. ያለፉት ዘጠኝ ወራት ባጋጠመ የትራፊክ አደጋ፣ ከአንድ ሺ
የአሜሪካ ድምፅ

በኦሮሚያ ለተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋ የመንገድ ጥበት እና ብልሽት ተጠቃሽ መኾኑ ተገለጸ

· 20 የዩኒቨርሲቲ መምህራን የሞቱበት ጠባቡ “ወሻ” መንገድ ማሳያ ኾኗል፤ በኦሮሚያ ክልል፣ በ2015 ዓ.ም. ያለፉት ዘጠኝ ወራት ባጋጠመ የትራፊክ አደጋ፣ ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎችን ሕይወት መቅጠፉን፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ። ለአደጋው መከሠት፥ የአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ፣ የተሽከርካሪዎች የቴክኒክ ችግር እና የመንገዶች ጥበት መንሥኤዎች እንደኾኑ፣ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ ደኅንነት ዘርፍ ሓላፊ ኮማንደር በላቸው ቲክ፣ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል። በያዝነው ሳምንት፣ የመዳወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራንን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችንና ሌሎች መንገደኞችን ጭኖ ወደ ሻሸመኔ ሲጓዝ የነበረው የተቋሙ ተሽከርካሪ፣ በምዕራብ አርሲ ዞን፣ ወሻ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በመገልበጡ፣ የ20 መምህራን ሕይወት ማለፉ ይታወሳል። በሥፍራው ያለው የመንገዱ ጥበት፣ ለተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋ መንሥኤ ስለ መኾኑ ተነግሯል፡፡ በችግሩ ዙሪያ፣ ከኦሮሚያ መንገዶች እና ከፌዴራል መንገዶች ባለሥልጣናት መልስ ለማግኝት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

በሃዲያ ዞን ደመወዝ በወቅቱ እንዲከፈላቸው የጠየቁ የመንግሥት ሠራተኞች ታሰሩ

በደቡብ ክልል ሃዲያ ዞን ምሥራቅ ባደዋቾ ወረዳ፣ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲከፈላቸው ጥያቄ ያቀረቡ የመንግሥት ሠራተኞችን ጨምሮ 40 ሰዎች መታሰራቸውን፣ የአሜሪ
የአሜሪካ ድምፅ

በሃዲያ ዞን ደመወዝ በወቅቱ እንዲከፈላቸው የጠየቁ የመንግሥት ሠራተኞች ታሰሩ

በደቡብ ክልል ሃዲያ ዞን ምሥራቅ ባደዋቾ ወረዳ፣ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲከፈላቸው ጥያቄ ያቀረቡ የመንግሥት ሠራተኞችን ጨምሮ 40 ሰዎች መታሰራቸውን፣ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ሠራተኞች ገለጹ። ከመምህራን በስተቀር አብዛኞቹ የመንግሥት ሠራተኞች፣ አሁንም ለተከታታይ ሦስት ወራት ደመወዝ ስላልተከፈላቸው፣ ለከፍተኛ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግር መጋለጣቸውን አመልክተዋል። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ፣ የምሥራቅ ባደዋቾ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኛ፣ ቀደም ሲል፣ ወርኀዊ ደመወዛቸው ወቅቱን ጠብቆ እንዲከፈላቸው ለተከታታይ ወራት ያቀረቡት ማመልከቻ ተቀባይነት ባለማግኘቱ፣ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ አቤቱታቸውን ለብዙኃን መገናኛ በማሰማታቸው፣ በወረዳው አስተዳደር፣ ተጨማሪ የመብቶች ጥሰቶች እንደተፈጸመባቸው አስታውቀዋል። በዚኽም ሳቢያ፣ 40 ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውንና ከእነርሱም መካከል 18ቱን ግለሰቦች እንደሚያውቋቸው የጠቀሱት ሠራተኛው፣ ግለሰቦቹ፥ በእስር ከአንድ ወር በላይ ቢያስቆጥሩም፣ እስከ አሁን ክሥ እንዳልተመሠረተባቸው ጠቁመዋል። በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ ነን፤ ያሉት ሌላው ሠራተኛ አቶ ብርሃኑ አበበ፣ የሚደርስባቸውን በደል እና ጫና እንኳን እንዳይናገሩ መከልከላቸውን ገልጸዋል። “የፌዴራል መንግሥት እና ገለልተኛ አካል ችግሩን ይፍታልን፤” ሲሉ አቶ ብርሃኑ ተማፅነዋል። ከወረዳው የመንግሥት ሠራተኞች አንዱ አቶ ብሩክ ናዳሞ እንደገለጹት፣ ሠራተኞች ደመወዝ ስለማይከፈላቸው፥ የቤት ኪራይ እና ወርኀዊ የአስበዛ ወጪ መሸፈን አለመቻላቸውንና ልጆቻቸውም መጎሳቆላቸውን፣ በአጠቃላይ ለከፍተኛ ኢኮኖሚያው እና ማኅበራዊ ችግር መጋለጣቸውን አስረድተዋል። ከመንግሥት ወገን ምላሽ ለማግኘት፣ ለዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫ፣ ለዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ሻለቃ ተሾመ ባትሶ፣ እንዲሁም ለዞኑ የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ሓላፊ አቶ ሳሙኤል ሹጉጤ ስልክ ብንደውልም፣ ስብሰባ ላይ እንደኾኑ በመግለጽ እና ቀጠሮ ከሰጡ በኋላ ስልካቸውን በማጥፋት፣ ለማግኘት በመቸገራችን አስተያየታቸውን ለማካተት አልቻልንም። ይኹን እንጂ፣ ከአንድ ወር በፊት፣ በጉዳዩ ላይ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም መጫ፣ የሠራተኞች የደመወዝ ክፍያ ችግር፣ ከዓመታት በፊት ለአርሶ አደሮች ከተሠራጨው የአፈር ማዳበርያ ግዥ ዕዳ ከፈላ ጋራ የተገናኘ መኾኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚኹ ጋራ በተገናኘ ሰዎች መታሰራቸውን አምነው፣ እስሩ፣ “በወንጀል ድርጊት በመሳተፋቸው ነው፤” ማለታቸው ይታወሳል። የባደዋቾ ወረዳ የመንግሥት ሠራተኞች ግን፣ ወርኀዊ ደመወዛቸው በወቅቱ እንዲከፈላቸው ከመጠየቅ በቀር፣ የተሳተፉበት የወንጀል ዐይነት አለመኖሩን በመግለጽ፣ አሁንም መብታቸው ተጠብቆ ለጥያቄያቸው ምላሽ እንዲሰጣቸው አመልክተዋል።

ሞስኮ በድሮን ተመታች

ዩክሬን ሞስኮ ላይ በርካታ የድሮን ጥቃቶች አድርሳብኛለች፤ ስትል ሩሲያ ክስ አሰማች።  ይኹን እንጂ፣ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፥ ወደ ከተማው የተቃረቡት ሁሉ
የአሜሪካ ድምፅ

ሞስኮ በድሮን ተመታች

ዩክሬን ሞስኮ ላይ በርካታ የድሮን ጥቃቶች አድርሳብኛለች፤ ስትል ሩሲያ ክስ አሰማች።  ይኹን እንጂ፣ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፥ ወደ ከተማው የተቃረቡት ሁሉም ድርኖች መደምሰሳቸውን ገልጿል፡፡ የሞስኮ ከንቲባ ሰርጌይ ሶብያኒን፣ ዛሬ ማለዳ በደረሰው የድሮን ጥቃት፣ ሁለት ሰዎች መቁሰላቸውንና አንደኛው ሆስፒታል መግባቱን ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ሁለት የመኖሪያ ቤት አፓርትመንቶች ላይ የነበሩ በርካታ ነዋሪዎች፣ ሕንጻዎቹን ለቀው ቢወጡም፣ ከቆይታ በኋላ መመለሳቸውን ተገልጿል፡፡በጥቃቱ የሞተ ሰው አለመኖሩ ተመልክቷል፡፡ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ፣ በሩሲያ ላይ የሚካሔዱ የድሮን ጥቃቶች እየጠነከሩ መጥተዋል፡፡ ኒዮርክ ታይስም ጋዜጣ እንደዘገበው፣ የዩናይትድ ስቴትስ የስለላ ድርጅት፣ ዩክሬን፥ በዚኽ ወር መጀመሪያ ላይ በክሬምሊን አቅራቢያ ከደረሰው የድሮን ጥቃት ጀርባ አለችበት፤ ብሎ ያምናል፡፡ ዩክሬን፣ በሩሲያ ውስጥ ባሉ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸም መጀመሯን በይፋ አምና አልተቀበለችም፡፡ ጥቃቱን የመረመረው የሩሲያ አጣሪ ኮሚቴ፣ በርካታ ድሮኖች ተመትተው መውደቃቸውንና ስብርባሪዎቻቸው መጠነኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ጠቅሷል፡፡ “ተመትተው ወድቀዋል፤” ስለተባሉት ድሮኖች ብዛት ግን፣ ኮሚቴው አልገጸለም፡፡ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴሩን የጠቀሱ በስም ያልተገለጹ ምንጮች፣ በሩሲያ ተመትተው የወደቁ ድሮኖች፣ ዐሥር እንደኾኑ ተናግረዋል፡፡ ከሩሲያ የደኅንነት ምንጮች፣ “ጥሩ መረጃዎችን ያገኛል፤” የተባለው ቤዛ የተባለው የቴሌግራም ቻናል፣ ሞስኮን ያጠቁት ድርኖች 25 እንደኾኑ ጠቅሷል፡፡

VOA60 World - Russia Blames Ukraine for Moscow Drone Attack

Russia/Ukraine: Officials said Russian air defenses stopped eight drones converging on Moscow in an attack that authorities blamed on Ukraine. Kyiv Mayor Vitali Klitschko said one person was killed in a third Russian assault on the city in 24 hours.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Russia Blames Ukraine for Moscow Drone Attack

Russia/Ukraine: Officials said Russian air defenses stopped eight drones converging on Moscow in an attack that authorities blamed on Ukraine. Kyiv Mayor Vitali Klitschko said one person was killed in a third Russian assault on the city in 24 hours.

VOA60 Africa - US President Biden condemned Uganda's new anti-gay law

U.S.: President Joe Biden condemned Uganda's new anti-gay law on Monday. Biden said in a statement that the United States will evaluate the implications of the law «on all aspects of U.S. engagement with Uganda.»
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - US President Biden condemned Uganda's new anti-gay law

U.S.: President Joe Biden condemned Uganda's new anti-gay law on Monday. Biden said in a statement that the United States will evaluate the implications of the law «on all aspects of U.S. engagement with Uganda.»

VOA60 America - Elon Musk visits China

Billionaire Elon Musk arrived in China on Tuesday for meetings with officials. According to a statement, during a meeting with Musk Foreign Minister Qin Gang said China will create a better market-oriented business environment for enterprises from all countri
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - Elon Musk visits China

Billionaire Elon Musk arrived in China on Tuesday for meetings with officials. According to a statement, during a meeting with Musk Foreign Minister Qin Gang said China will create a better market-oriented business environment for enterprises from all countries, including Tesla.

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኬንያ ድንገተኛ ጉብኝት አደረጉ

ትላንት ሰኞ፣ ድንገት ናይሮቢ የገቡት፣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋራ ተወያይተዋል። ጉብኝቱ የተካሔደ
የአሜሪካ ድምፅ

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኬንያ ድንገተኛ ጉብኝት አደረጉ

ትላንት ሰኞ፣ ድንገት ናይሮቢ የገቡት፣ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋራ ተወያይተዋል። ጉብኝቱ የተካሔደው፣ ሞስኮ እና ኪቭ፣ በገቡበት ጦርነት ሳቢያ፣ ከአፍሪካ የሚያገኙትን ድጋፍ ለማጠናከር፣ አንዳቸው የሌላቸውን ዳና እየተከተሉ በሚያካሒዱት ጉብኝት ዲፕሎማሲያዊ ላቂያ ለማግኘት በሚጣጣሩበት ጊዜ ነው፡፡ በምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ተሰሚነት ወዳላት ኬንያ የተደረገው የላቭሮቭ ጉብኝት፣ የዩክሬኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲምትሮ ኩሌባን፣ ያለፈው ሳምንት የናይሮቢ ጉብኝት ተከትሎ የተካሔደ ነው፡፡ ላቭሮቭ፣ “በጉብኝታችን ወቅት፥ በንግድ፣ በኢንቨትመንት እና ኢኮኖሚ፣ በባህል እና ሰብአዊ ርዳታ፣ እንዲሁም በትምህርት፣ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ስለሚኖረን ትብብር እና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ላይ እንነጋራለን፤” ሲሉ መናገራቸውን፣ ከጉብኝቱ በፊት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። ጉብኝቱ፣ አስቀድሞ ያልተገለጸና ከኬንያ ባለሥልጣናትም በኩል የወጣ መረጃ አልነበረም፡፡ የዓለም ኀያላን ሀገራት፣ 1ነጥብ3 ቢሊዮን ሕዝብ ባላት አፍሪካ ያላቸውን ተጽእኖ ለማሳደግ በሚያደርጉት ፉክክር፣ ላቭሮቭ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አህጉሪቱን ለበርካታ ጊዜያት ጎብኝተዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት፣ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኩሌባ፣ የተወሰኑ የአፍሪካ ሀገራት፣ ከ15 ወራት በላይ በቆየው የዩክሬን ጦርነት የሚያሳዩትን ገለልተኝነት እንዲያቆሙ በመጠየቅ፣ አፍሪካ ከኪቭ ጋራ ያላትን ትስስር እንድታሳድግ ግፊት አድርገዋል፡፡ ሩሲያ ዩክሬንን ለቃ እንድትወጣ፣ ባለፈው የካቲት፣ በተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የተላለፈውን ውሳኔ አስመልክቶ ድምፅ ከሰጡ 54 የአፍሪካ አገሮች መካከል 22 የሚኾኑቱ፣ ድምፅ አልሰጡም ወይም ተአቅቦ አድርገዋል፡፡ ውሳኔውን በመቃወም ድምፅ ከሰጡ አገሮች ውስጥ፣ ኤርትራ እና ማሊ ይገኙበታል፡፡

ከዘጠኝ ዓመት በፊት የተጠለፉት የቺቦክ ልጃገረዶች አሁንም አልተለቀቁም

የናይጄሪያ የጦር ሠራዊት፣ በአክራሪ እስላማዊው ቡድን ቦኮ ሐራም፣ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት የተጠለፉ ሦስት ተጨማሪ ሴት ተማሪዎችን፣ በዚኽ ሳምንት ማስለቀቁ ተዘ
የአሜሪካ ድምፅ

ከዘጠኝ ዓመት በፊት የተጠለፉት የቺቦክ ልጃገረዶች አሁንም አልተለቀቁም

የናይጄሪያ የጦር ሠራዊት፣ በአክራሪ እስላማዊው ቡድን ቦኮ ሐራም፣ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት የተጠለፉ ሦስት ተጨማሪ ሴት ተማሪዎችን፣ በዚኽ ሳምንት ማስለቀቁ ተዘግቧል፡፡ እ.አ.አ በ2014፣ የቦኮ ሐራም ታጣቂዎች፣ በቦርኖ ክፍለ ሀገር ቺቦክ ከተማ የሚገኝን የመንግሥት ትምህርት ቤት ወርረው፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ልጃገረዶችን ጠልፈው መውሰዳቸው ይታወሳል፡፡ ከዚያ ወዲህ፣ ከአጋቾቹ ጋራ በተካሔደ ድርድር ብዙዎች ልጃገረዶች ቢለቀቁም፣ አሁንም በጠላፊዎቻቸው እጅ ያሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ቲመቲ ኦቢዙ ከአቡጃ ያጠናቀረውን ዘገባ፣ ቆንጅት ታየ ለአፍሪካ ነክ ርእሶች ፕሮግራም እንደሚከተለው ታቀርበዋለች፡፡

በታዳጊው መርከብ 600 ፍልሰተኞች ከሥጥመት ተረፉ

«ድንበር የለሽ ሐኪሞች» የተባለው የሕክምና ገባሬ ሠናይ ቡድን፣ ባለፈው ቅዳሜ፣ በጣሊያን ሲሲሊ አቅራቢያ ያሠማራው መርከብ፣ ወደ ስድስት መቶ የሚደርሱ
የአሜሪካ ድምፅ

በታዳጊው መርከብ 600 ፍልሰተኞች ከሥጥመት ተረፉ

«ድንበር የለሽ ሐኪሞች» የተባለው የሕክምና ገባሬ ሠናይ ቡድን፣ ባለፈው ቅዳሜ፣ በጣሊያን ሲሲሊ አቅራቢያ ያሠማራው መርከብ፣ ወደ ስድስት መቶ የሚደርሱ ፍልሰተኞች፣ በአደገኛ ኹኔታ ይጓዙበት ከነበረ ጀልባ ላይ መታደጉ ተገለጸ፡፡ በአሕጽሮቱ (MSF) ተብሎ የሚጠራው «ድንበር የለሽ ሐኪሞች» ቡድኑ፣ በትዊተር ገጹ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ «ጂዎ ባሬንት» የተባለው የትድግና መርከቡ፣ ፍልሰተኞቹ ተጨናንቀው ይጓዙበት ወደነበረው ጀልባ አቅጣጫ ያመራው፣ ከጀልባዋ የድረሱልን ጥሪ ከተላለፈለት በኋላ ነው፡፡ የገባሬ ሠናይ ቡድኑ መርከብ፣ ከጣሊያን መንግሥት በተሰጠው መመሪያ መሠረት፣ ፍልሰተኞቹን፥ ባሪ ወደተባለው የደቡባዊ ጣሊያን ወደብ ይዞ እየቀዘፈ እንደኾነ ሲያስታውቅ፣ ጉዞው ወደ አርባ ሰዓታት ገደማ እንደሚወስድ ጠቁሟል፡፡ ሕገ ወጥ ፍልሰትን በሚመለከት፣ ጥብቅ ፖሊሲ የሚከተለው በጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ መሎኒ የሚመራው የጣሊያን መንግሥት፣ ባሕር ላይ በአደገኛ ኹኔታ ሲጓዙ የሚታደጋቸውን ፍልሰተኞች፣ ኾነ ብሎ ከተገኙበት ሥፍራ ርቆ ወደሚገኝ ወደብ በተደጋጋሚ እንዲወሰዱ ያደርጋል፤ በማለት ገባሬ ሠናይ ድርጅቶች እና ሌሎችም መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት ነቀፌታ ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡ እ.አ.አ በዘንድሮ 2023 እስከ አሁን ባለው ጊዜ፣ ከ47ሺሕ የሚበልጡ ፍልሰተኞች፣ ወደ ጣሊያን ምድር መድረሳቸው ተነግሯል፡፡ የጣሊያን የአገር ግዛት ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው፣ ባለፈው ዓመት፣ በዚኹ ተመሳሳይ ጊዜ የገቡት፣ 18ሺሕ ገደማ ነበሩ፡፡

በማዳበሪያ እጥረት የተቆጡ አርሶ አደሮች አቤቱታ

· የዐማራ ክልል በከፍተኛ የማዳበሪያ እጥረት መመታቱ ተገልጿል የአፈር ማዳበሪያ ፍለጋ እየተንከራተቱ የዘር ወቅት ያለፈባቸውና ለረኀብ የመጋለጥ ስጋት ያደረ
የአሜሪካ ድምፅ

በማዳበሪያ እጥረት የተቆጡ አርሶ አደሮች አቤቱታ

· የዐማራ ክልል በከፍተኛ የማዳበሪያ እጥረት መመታቱ ተገልጿል የአፈር ማዳበሪያ ፍለጋ እየተንከራተቱ የዘር ወቅት ያለፈባቸውና ለረኀብ የመጋለጥ ስጋት ያደረባቸው፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን ደቡብ ሜጫ ወረዳ አርሶ አደሮች፣ የምሬት አቤቱታ አቀረቡ፡፡ ዞኑ የሚገኝበት የዐማራ ክልል፣ በከፍተኛ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት መመታቱ ተገልጿል፡፡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የደቡብ ሜጫ ወረዳ አርሶ አደሮች፣ “ማዳበሪያውን ካልሰጣችኹን ሌሎች አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን እንድትሰጡን አንፈቅድላችኹም፤” በሚል በወረዳው ባለሥልጣናት ላይ ቁጣቸውን እየገለጹ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡ በ10 ሺሕዎች በሚቆጠሩ የወረዳው አርሶ አደሮች ተወክለው ወደ ባሕር ዳር ግብርና ቢሮ የተላኩ ስምንት አርሶ አደሮች እና አንድ የወረዳው ባለሞያ፣ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በዚኽ ወቅት የአፈር ማዳበሪያ ካላገኙ፣ በሚቀጥለው ዓመት ለረኀብ እንደሚጋለጡ አሳስበዋል፡፡ በክልሉ ከፍተኛ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት መኖሩን ያመነው፣ የዐማራ ክልል ግብርና ቢሮ፣ “ከፌደራል መንግሥት ጋራ እየተነጋገርኹበት ነው፤” ብሏል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፣ እጥረቱ የተከሠተው በመላ አገሪቱ እንደኾነ አመልክቶ፣የግብዓት ሥርጭቱ፥ ቅደም ተከተሉን ጠብቆ በወቅቱ ባለመድረሱ ችግሩ ማጋጠሙን አስረድቷል፡፡ ከዐማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ደቡብ ሜጫ ወረዳ፣ ወደ ባሕር ዳር የክልሉ ግብርና ቢሮ መጥተው፣ አቤቱታ ሲያሰሙ ያገኘናቸው ስምንት አርሶ አደሮች እና አንድ የግብርና ባለሞያ፣ በወረዳው ከፍተኛ የማዳበሪያ እጥረት መከሠቱን ተናግረዋል፡፡ አርሶ አደር ጌቱ ታመነ፣ ከደቡብ ሜጫ ለሁሉ ሰላም ቀበሌ እንደመጡ ይናገራሉ፡፡ በየዓመቱ በቆሎ ይዘሩ እንደነበር የገለጹት አርሶ አደሩ፣ ዘንድሮ፣ ከግንቦት 1 እስከ 16 ቀን ድረስ ተዘርቶ ማለቅ ሲኖርበት፣ በአፈር ማዳበሪያ እጥረት የተነሳ እስከ አሁን አልተዘራም፤ ብለዋል፡፡ ከአርሶ አደሮቹ ጋራ አቤቱታ ለማሰማት ወደ ቢሮው የመጡት፣ የደቡብ ሜጫ ወረዳ የግብርና ጽ/ቤት የግብአት ቡድን መሪ አቶ አለማ ዳኘው፣ በወረዳው፣ የአፈር ማዳበሪያ ባለመከፋፈሉ ቅር የተሰኘው አርሶ አደር መቆጣቱን አመልክተዋል፡፡ “አርሶ አደሩ ጅራፉን እንደያዘ፣ በመንግሥት ቢሮዎች ደጅ ነው የሚውለው፤” ብለዋል አቶ አለማ፡፡ ከቅሬታ አቅራቢ የወረዳው አርሶ አደሮች አንዱ ደጉ ካሳሁን፣ ማዳበሪያ ካላመጣችኹ አታገለገሉንም፤ ሲሉ፣ በአካባቢው ባለሥልጣናት ላይ ቁጣ እያሰሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ የሰባታሚት ቀበሌ አርሶ አደሮችም፣ የአፈር ማዳበሪያ ለማግኘት መንከራተታቸው፣ በእርሻ ሥራቸው ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን ተናግረዋል፡፡ በምዕራብ ጎጃም ዞን የደቡብ ሜጫ ወረዳ አርሶ አደሮች አቤቱታ፣ በዐማራ ክልል ደረጃ የሚታየው ከፍተኛ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት ማሳያ እንጂ፣ በኹሉም የክልሉ አካባቢዎች፣ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠናል፡፡ የዐማራ ክልል ግብርና ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ አቶ አምሳሉ ጎባው እንደሚገልጹት፥ የክልሉ መንግሥት፣ 5ነጥብ2 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት፣ ለግብርና ሚኒስቴር ጥያቄ ቢያቀርብም፣ እስከ አሁን የተላከው ግን፣ 1ነጥብ7 ሚሊዮን ኩንታል ብቻ ነው፡፡ ቀሪው 3ነጥብ5 ሚሊዮን ኩንታል በፍጥነት እንዲላክለት፣ ቢሮው፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋራ በመነጋገር ላይ ነው፡፡ ስለ ጉዳዩ፣ በግብርና ሚኒስቴር የግብአት አቅርቦት ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ተስፋ፣ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት የተከሠተው በመላ አገሪቱ መኾኑን ገልጸዋል፡፡ የችግሩ ዋና መንሥኤም፣ የግብአት ሥርጭቱ ቅደም ተከተልን ባለመጠበቁ እንደኾነ ጠቁመዋል፡፡ ለአገሪቱ በአጠቃላይ የሚያስፈልገው፣ ከ12 ሚሊዮን በላይ ኩንታል የማዳበሪያ ግዥ የተፈጸመ ሲኾን፣ ገሚሱ ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱንና ገሚሱ ደግሞ በጅቡቲ ወደብ ላይ እንደሚገኝ፣ አቶ መንግሥቱ አስረድተዋል፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ ከገባው ውስጥ፣ ከአራት ሚሊዮን ኩንታል በላይ መከፋፈሉን አክለው ገልጸዋል፡፡ ለእርሻ ሥራው ወሳኝ ግብአት የኾነው የዳፕ እና ዩሪያ የአፈር ማዳበሪያ እጥረት፣ በአጭር ጊዜ እንደሚፈታም፣ አቶ መንግሥቱ አመልክተዋል፡፡

ተመድ በሱዳን፣ ሔይቲ፣ ቡርኪናፋሶ እና ማሊ የረኀብ አደጋ ሊያጋጥም እንደሚችል አስጠነቀቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋም የኾኑት የዓለም ምግብ ድርጅት እና የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) በጋራ ባወጡት ሪፖርት፣ በዓለም ዙሪያ ከምግብ አቅ
የአሜሪካ ድምፅ

ተመድ በሱዳን፣ ሔይቲ፣ ቡርኪናፋሶ እና ማሊ የረኀብ አደጋ ሊያጋጥም እንደሚችል አስጠነቀቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተቋም የኾኑት የዓለም ምግብ ድርጅት እና የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) በጋራ ባወጡት ሪፖርት፣ በዓለም ዙሪያ ከምግብ አቅርቦት ጋራ የተያያዙ አፋጣኝ ርዳታ የሚሹ አደጋዎች እየጨመሩ እንደኾነ አስታውቀዋል። በተለይም፣ በሱዳኑ ጦርነት እና ሔይቲ፣ ቡርኪናፋሶ፣ እና ማሊ፥ በሰዎች እና በሸቀጦች ላይ በጣሉት የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት፣ የረኀብ አደጋ እየጨምረ መምጣቱን ተቋማቱ አመልክተዋል። አራቱ ሀገራት፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለረኀብ መጋለጣቸውን ወይም ማኅበረሰባቸው ወደ «አስከፊ ኹኔታ እየገቡ» መኾናቸውን ለይቶ፣ ቀደም ሲል በከፍተኛ ማስጠንቀቂያ ደረጃ ላይ ካስቀመጣቸው፥ አፍጋኒስታን፣ ናይጄሪያ፣ ሶማልያ፣ ደቡብ ሱዳንና የመን ጋራ ተቀላቅለዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት ተቋማት፣ በሪፖርታቸው፣ በከፍተኛ ደረጃ አሳሳቢ ኹኔታ ላይ ይገኛሉ፤ ካሏቸው ዘጠኝ ሀገራት በተጨማሪ፣ ሌሎች 22 ሀገራትም፣ ለከፍተኛ የምግብ ዋስትና ዕጦት በመጋለጣቸው፣ «አስጊ ኹኔታ ላይ ናቸው፤» ሲሉ፣ ለይተው አስቀምጠዋቸዋል። የሰዎችን ሕይወት እና እየጠፋ ያለውን የሥራ ዕድል ለማዳንም አስቸኳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጠይቀዋል። «ዓለም አቀፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እና ማንም ወደ ኋላ እንደማይቀር ለማረጋገጥ ከፈለግን፣ አሁን የተደቀነብንን አደጋ፣ በተለመደው መንገድ ማስተናገድ ከአሁን ወዲያ አማራጭ አይኾንም፤» ብለዋል፣ የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት ዋና ጸሐፊ ኩ ዶንዡ። አያይዘውም፣ ሰዎችን ከረኀብ አፋፍ ለመመለስ፣ ሕይወታቸውን መልሰው እንዲገነቡ ለመርዳት እና ለምግብ ዋስትና ማጣት የሚዳርጉ መንሥኤዎችን በዘላቂነት ለመፍታት፣ በግብርናው ዘርፍ አፋጣኝ ርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት ሪፖርት፣ በሱዳን ያለው ግጭት ወደ ጎረቤት ሀገራትም ሊሻገር ይችላል፤ የሚለው ስጋት፣ በአካባቢው ድኻ ሀገራት ላይ፣ የኢኮኖሚ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አስታውቋል። እ.አ.አ በ2023፣ ሊደርስ ይችላል ተብሎ ለሚጠበቀው ኤል-ኒኖ ለተሰኘው የአየር ንብረት መዛባት ተጋላጭ በኾኑ ሀገራት፣ የከፋ የአየር ንብረት ኹናቴዎችን ሊያስከትል ይችላል፤ የሚል ፍራቻም እንዳለ አመልክቷል።

በባለስቲክ ሚሳየሎች ሙከራ ጃፓን ሰሜን ኮሪያን አስጠነቀቀች

ጃፓን፣ ሰሜን ኮሪያ፥ እ.ኤ.አ. ከግንቦት 31 እስከ ሰኔ 11 ድረስ፣ የባለስቲክ ሚሳየሎቿን የማስወንጨፍ ሙከራ ለማድረግ ማቀዷን ከገለጸች በኋላ፣ የባለስቲክ ሚሳየ
የአሜሪካ ድምፅ

በባለስቲክ ሚሳየሎች ሙከራ ጃፓን ሰሜን ኮሪያን አስጠነቀቀች

ጃፓን፣ ሰሜን ኮሪያ፥ እ.ኤ.አ. ከግንቦት 31 እስከ ሰኔ 11 ድረስ፣ የባለስቲክ ሚሳየሎቿን የማስወንጨፍ ሙከራ ለማድረግ ማቀዷን ከገለጸች በኋላ፣ የባለስቲክ ሚሳየል መከላከያዋ በተጠንቀቅ እንዲቆም ዛሬ ሰኞ ትዕዛዝ ሰጥታለች፡፡ በግዛቷ ላይ ስጋት የሚጋርጥን ማንኛውም መሣሪያ፣ መትታ እንደምትጥልም፣ ጃፓን ከወዲሁ አስጠንቃቀለች፡፡ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሙዬ ኪሻዳ፣ ሰሜን ኮሪያ የምታስወነጭፋቸው ሚሳየሎች በሙሉ፣ እንደ ትንኮሳ ይቆጠራሉ፤ ሲሉ፣ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡ “የባለስቲክ ሚሳየል ቴክኖሎጂዎችን ማስወንጨፍ፣ ሳተላይት እንኳን ቢኾን፣ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎችን መጣስ እና የሰዎችን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥል ከባድ ችግር ነው፤” ሲሉም አክለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡ ጃፓን ወደ ምድር የቀረቡ የጦር መሣሪያዎችን አውርደው መጣል የሚችሉ የጦር መሣሪያዎችን፣ ወደ ኢኮናዋ ደሴቶች አሠማርታለች፡፡ ባለፈው ወርም እንዲሁ፣ ዒላማዎቻቸውን በሕዋ ላይ ቀድመው መምታት የሚችሉ ሚሳየሎችን የተሸከሙ፣ የባሕር ኃይል ደምሳሽ መሣሪያዎችን፣ ወደ ምሥራቅ ቻይና ባሕር መላኳ ተመልክቷል፡፡ የኑክሌር ጦር መሣሪያ የታጠቀችው ሰሜን ኮሪያ፣ የመጀመሪያዋ የኾነውን ወታደራዊ የስለላ ሳተላይት ሥራ ማጠናቀቋን አስታውቃለች፡፡ የአገሪቱ መሪ ኪም ጆን ኡን፣ ሳተላይቷ የምትመጥቅበትን የመጨረሻ ዝግጅት እንዳጸደቁም ታውቋል፡፡ ተንታኞች እንደገለጹት፣ ሳተላይቱ፥ ድርኖችን ጨምሮ በጦርነት ወቅት ዒላማዎችን በትክክል የመምታትን ዐቅም የሚያሳድግ የስለላ ቴክኖሎጂ ፕሮግራም አካል ነው፡፡ ሰሜን ኮሪያ፣ ባለፉት ቅርብ ወራት፣ ፈሳሽ ያልኾኑ ጠጣር የነዳጅ አማራጮችን(solid-fuel) የሚጠቀሙ፣ አህጉር አቋራጭ የባለስቲክ ሚሳየሎችን ጨምሮ፣ ተከታታይ ሚሳየሎችንና የጦር መሣሪያዎችን መሞከሯ ተመልክቷል፡፡

ሩሲያ ዩክሬንን በሚሳየል እና በድሮኖች አጠቃች

ሩሲያ፣ ዛሬ ሰኞ በፈጸመችው ጥቃት ሁለት ሕፃናት እና ነፍሰ ጡር ሴትን ጨምሮ፣ ስድስት ሰዎች መቁሰላቸውን በዩክሬን የኻርኪቭ ግዛት አገረ ገዥ ተናገሩ፡፡ አገ
የአሜሪካ ድምፅ

ሩሲያ ዩክሬንን በሚሳየል እና በድሮኖች አጠቃች

ሩሲያ፣ ዛሬ ሰኞ በፈጸመችው ጥቃት ሁለት ሕፃናት እና ነፍሰ ጡር ሴትን ጨምሮ፣ ስድስት ሰዎች መቁሰላቸውን በዩክሬን የኻርኪቭ ግዛት አገረ ገዥ ተናገሩ፡፡ አገረ ገዥው ኦሌ ሲነኹቦይ፣ በመኖሪያ ቤት ሕንፃዎች ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያሳይ ቪዲዮ፣ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አውጥተዋል፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው፥ ኢስካንደር ተብሎ በሚጠራው ሚሳየል እንደኾነ፣ አገረ ገዥው ተናግረዋል፡፡ ዛሬ ሰኞ ማለዳው ላይ፣ የዩክሬን ጦር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ቃል አቀባይ አርካዲ ኮቫሌ፣ ሩሲያ፥ 40 የክሩዝ ሚሳየሎች ወደ ዩክሬን መተኮሷን ገልጸዋል፡፡ በካስፔን የባሕር ግዛት ከሚገኝ የሩሲያ የጦር አውሮፕላን ከተተኮሱት ውስጥ፣ 37 ኬኤች 101 እና ኬኤች 555 የተባሉ ክሩዝ ሚሳየሎች፣ በዩክሬን መከላከያ መምከናቸውን ኮቫሌ ተናግረዋል፡፡ 29 ኢራን ሠራሽ ድሮኖች መደምሰሳቸውንም ኮቫሌ አስታውቀዋል፡፡ ለአምስት ሰዓታት የዘለቀው ጥቃት እኩለ ሌሊት ላይ ሲጀምር፣ ወታደራዊ ተቋማት እና ወሳኝ የመሠረተ ልማት አውታሮች፣ የምት ዒላማ መደረጋቸውን፣ የዩክሬን ባለሥልጣናት ገልጸዋል፡፡

VOA60 World - Turkish President Recep Tayyip Erdogan wins new five-year term

Turkish President Recep Tayyip Erdogan has a new five-year term in hand after prevailing in a runoff election that opposition members hoped would unseat him amid a cost-of-living crisis. Erdogan won Sunday’s second round with 52.2% of the vote.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Turkish President Recep Tayyip Erdogan wins new five-year term

Turkish President Recep Tayyip Erdogan has a new five-year term in hand after prevailing in a runoff election that opposition members hoped would unseat him amid a cost-of-living crisis. Erdogan won Sunday’s second round with 52.2% of the vote.

VOA60 Africa - Uganda's President Signs into Law Tough Anti-Gay Legislation

Uganda: President Yoweri Museveni has signed into law tough new anti-gay legislation, the speaker of the country's parliament said in a post on Twitter on Monday. Homosexuality is criminalized in more than 30 of Africa's 54 countries.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - Uganda's President Signs into Law Tough Anti-Gay Legislation

Uganda: President Yoweri Museveni has signed into law tough new anti-gay legislation, the speaker of the country's parliament said in a post on Twitter on Monday. Homosexuality is criminalized in more than 30 of Africa's 54 countries.

VOA60 America - US Leaders Urge Lawmakers to Approve Debt Ceiling Deal

U.S. President Joe Biden and House Speaker Kevin McCarthy urge lawmakers from their parties to approve an agreement to increase the country’s borrowing limit. The government will run out of cash to pay its existing bills June 5.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - US Leaders Urge Lawmakers to Approve Debt Ceiling Deal

U.S. President Joe Biden and House Speaker Kevin McCarthy urge lawmakers from their parties to approve an agreement to increase the country’s borrowing limit. The government will run out of cash to pay its existing bills June 5.

በፔሩ 58 ኪ.ግ. ኮኬይን ተያዘ

58 ኪሎግራም የሚመዝን ኮኬይን ትናንት መያዛቸውን የፔሩ አደንዛዥ እጽ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እሽጉ የናዚ ባንዲራ ምልክት የተደረገበትና ውደ ቤ
የአሜሪካ ድምፅ

በፔሩ 58 ኪ.ግ. ኮኬይን ተያዘ

58 ኪሎግራም የሚመዝን ኮኬይን ትናንት መያዛቸውን የፔሩ አደንዛዥ እጽ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እሽጉ የናዚ ባንዲራ ምልክት የተደረገበትና ውደ ቤልጂየም በማቅናት ላይ እንደነበር ተነግሯል። የአገሪቱ ፖሊስ እንዳለው ኮኬይኑ የተገኘው የላይቤሪያን ሰንደቅ ዓላማ በሚያውለበልብና የአስፋራገስ አትክልት በሚያመላልስ መርከብ ላይ ነው። መርከቡ መጀመሪያ ኢኳዶር ላይ መልህቁን ጥሎ እንደነበርም ተጠቁሟል። ፖሊስ በመርከቢቱ ላይ የተጫኑትን 80 የዕቃ መያዣዎች በመፈተሽ ላይ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ በፊት የተለያዩ ምልክቶች የተደረጉባቸው የአደንዛዥ እጽ ጥቅሎች ማግኘታቸውን የጠቀሰው ፖሊስ፣ የናዚ ጀርመን ባንዲራ ሲያገኙ ግን ለመጀመሪያ ግዜ ነው ብለዋል። ፔሩ ከኮሎምቢያ ለጥቃ በዓለም ሁለተኛ የኮካ ቅጠል አምራች ስትሆን፣ ኮኬይን በማምረትም ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

አምባሳደር ማይክ ሐመር በሎስ አንጀለስ ከትውልደ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ ያደረጉት ወይይት

የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በዩናይትድ ስቴትስ ካሊፎርኒያ ግዛት ሎስ አንጀለስ ከተማ እና በአካባቢው ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረ
የአሜሪካ ድምፅ

አምባሳደር ማይክ ሐመር በሎስ አንጀለስ ከትውልደ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ ያደረጉት ወይይት

የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር፣ በዩናይትድ ስቴትስ ካሊፎርኒያ ግዛት ሎስ አንጀለስ ከተማ እና በአካባቢው ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ተወካዮች ጋራ፣ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ኹኔታ ላይ ከሳምንት በፊት ውይይት አድርገዋል። አምባሳደሩ፣ ከኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋራ ያደረጉትን ውይይት አስመልክቶ፣ በፈቃዱ ሞረዳ፥ ሁለት የውይይቱን ተሳታፊዎች አነጋግሮ እንደሚከተለው ያቀርበዋል።

በመስጂዶችን መፍረስ ተቃውሞ ወቅት ህይወት መጥፋቱን ፖሊስ አስታወቀ

አንዋር መስጂድ አካባቢ ዛሬ ከጁምዓ ሶላት በኋላ ተደርጎ የነበረን ተቃውሞ ተከትሎ “መርካቶ አካባቢ ተፈጠረ” ሲል ፖሊስ ከገለፀው ረብሻና ግርግር ጋር ተያይዞ
የአሜሪካ ድምፅ

በመስጂዶችን መፍረስ ተቃውሞ ወቅት ህይወት መጥፋቱን ፖሊስ አስታወቀ

አንዋር መስጂድ አካባቢ ዛሬ ከጁምዓ ሶላት በኋላ ተደርጎ የነበረን ተቃውሞ ተከትሎ “መርካቶ አካባቢ ተፈጠረ” ሲል ፖሊስ ከገለፀው ረብሻና ግርግር ጋር ተያይዞ የሁለት ሰዎች ህይወት መጥፋቱንና በአሥሮች የሚቆጠሩ መጎዳታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። ጉዳት ደርሶባቸዋል ከተባሉት መካከል 42 የፖሊስ ባልደረቦችና ረዳቶች እንዲሁም ሌሎች አራት ሰዎች እንደሚገኙባቸው ይኸው የፖሊስ መግለጫ ጠቁሞ “ብጥብጡን መርተዋል፣ አስተባብረዋል ወይም ዋነኛ ተሳታፊ ነበሩ” ሲል የጠረጠራቸውን አሥራ አምስት ሰዎች መያዙን አስታውቋል። ሁለት የአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት አግልግሎት ሰጭ አውቶቡሶች ላይም ጉዳት መድረሱን ይኸው የፖሊስ መግለጫ ይናገራል። ሁኔታውን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ያስታወቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ አጭር መግለጫ ‘ጠፋ’ የተባለው ህይወት በማን እንደተፈፀመ አይናገርም። ሸገር ከተማ ውስጥ የመስጂዶችን መፍረስ በመቃወም አንዋር መስጊድ አካባቢ የነበረውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ መተኮሱን ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ሥፍራው ላይ እንደነበረና የሆነውን ሁሉ ማየቱን የተናገረ እማኝ ለቪኦኤ ገልጿል። መስጂዱ ውስጥ የነበሩ ምዕመናንም እንዳይወጡ ለተራዘመ ጊዜ ታግደው እንደነበርም እማኙ ጠቁሟል። ፒያሳ አካባቢ ባለው ኑር መስጂድም የተቃውሞ እንቅስቃሴ እንደነበር ሌላ እማኝ አመልክቷል። በአንዋር መስጂድ በነበረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት የፖሊስ አባላት ወደ መስጂዱ ለመግባት ሙከራ አድርገው እንደነበር ጥቆማዎች ቢደርሱንም ይህንን የሚያረጋግጥ ተጨማሪ መረጃ ወይም የፖሊስ ቃል ማግኘት አልቻልንም። በሸገር ከተማ አስተዳደር ውስጥ 19 መስጂዶች መፍረሳቸውን የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የመስጂዶች እና የአውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ ሼኽ አብዱልሃኪም ሁሴን በዳሶ ለቪኦኤ ተናግረዋል። የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከሁለት ቀናት በፊት ሰጥቶት በነበረ መግለጫ “የከተማ አስተዳደሩ እያካሄደ ነው” ያለውን መስጂዶችን የማፍረስ እንቅስቃሴ አውግዞ ምዕመናኑ ክልሉ ውስጥ በሚገኙ መስጂዶች ሁሉ ዛሬ ግንቦት 18 ተቃውሞ እንዲያሰሙ ጥሪ አስተላልፎ ነበር። የአሜሪካ ድምፅ ዛሬ ስለነበረው የተቃውሞ እንቅስቃሴ እንዲሁም መስጂዶችን ማፍረስን በተመለከተ ከሸገር ከተማ አስተዳደር፣ ከኦሮሚያ ክልል እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። ሆኖም የሸገር ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣናት ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ ለቪኦኤ በሰጧቸው መግለጫዎች መስጂዶችን ስለማፍረስ ለይተው ባይናግሩም በከተማው የሚካሄደው ግንባታዎችን የማፍረስ ዘመቻ “ሕግን የማስከበር እርምጃ ነው” ብለዋል። ይሁን እንጂ የሚፈርሱት ቤቶች አስተዳደሩ እንደሚለው ሕገወጥ ቢሆኑ እንኳ ለነዋሪዎች በቅድሚያ አማራጭ መዘጋጀት እንዳለበት ኢትዮጵያ የፈረመችው ዓለም አቀፍ ሕግ እንደሚደነግግ የገለፀው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ድርጊቱን በመቃወም የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል። የኢትዮጵያ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ደግሞ አንድ መቶ ሺህ አቤቱታዎች እንደቀረቡለት አመልክቷል።

Get more results via ClueGoal