ዋሽንግተን ዲሲ — የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን ዛሬ በዋይት ሃውስ ተቀብለው ሲያነጋግሩ፤ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ በሐማስ ላይ እያካሄደች ያለችው ጦርነት ‘ልዩ ትኩረት ያገኛል’ ተብሎ ይጠበቃል። አንድ ከፍተኛ የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር ባለሥልጣን በትላንትናው ዕለት ለጋዜጠኞች ሲናገሩ ባይደን “ለእስራኤል ደህንነት መጠበቅ ያላቸውን የማያወላውል ድጋፍ” እንደሚገልጹ እና በውይይታቸውም ወቅት በመካከለኛው ምስራቅ ካሉት በኢራን የሚደገፉት እንደ ሃማስ፣ ሂዝቦላ እና የየመኑ ሸማቂ ቡድን ሁቲ በእስራኤል ደህንነት ላይ የደቀኑትን ስጋት አስመልክቶም ይወያያሉ ብለዋል። ሁለቱ መሪዎች በጋዛ ካለው ሰብአዊ ሁኔታ በተጨማሪ ለጦርነቱ ማብቂያ ለማበጀት ከተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ በተያዘው ጥረት፣ ጋዛ ውስጥ በሃማስ ተይዘው የሚገኙት ታጋቾች ስለሚፈቱበት ሁኔታ፣ እስራኤል ፍልስጤማውያን እስረኞችን ስለምትለቅበት እና እንዲሁም ጋዛ ውስጥ ለፍልስጤማውያን የሚደርስ የሰብአዊ ርዳታ በሚጨምርበት መንገድ ዙሪያ ይወያያሉ። ዩናይትድ ስቴትስ ከግብፅ እና ከኳታር ጋራ በመተባበር በመሥራት ላይ የምትገኘው የተኩስ አቁም ድርድር ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች እስራኤል እና ሃማስ በየበኩላቸው ከሚጠይቋቸው መጣጣም ያልቻሉ ፍላጎቶች የተነሳ ለወራት መራዘሙ ይታወሳል። ኔታንያሁ ለመጪው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ የፓርቲያቸው ዕጩ ለመሆን ግንባር ቀደም ከሆኑት ከምክትል ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ ጋራም የሚገናኙ ሲሆን የሪፐብሊካን ፓርቲው ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ ደግሞ ነገ አርብ ተቀብለው እንደሚያነጋግሯቸው ተመልክቷል፡፡ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ደጃፍ በሺዎች የተቆጠሩ የፍልስጤማውያን ደጋፊውዎች እና ጦርነቱን የሚቃወሙ ሰዎች የተቃውሞ ሰልፍ ከሃምሳ በላይ ዲሞክራት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት በትላንቱ ንግግራቸው ላይ ሳይገኙላቸው ቀርተዋል፡፡ ይሁን እና ኔታንያሁ ግን ጋዛ ላይ እየተካሄደ ባለው ጦርነት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንደሚደረስ እንደሚተማመኑ ተናግረዋል፡፡ ሆኖም ለወራት የዘለቀው እና አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ድርድር እየተሳካ ስለመሆኑ የሰጡት ፍንጭ የለም፡፡ የሆነ ሆኖ ጠቅላይ ሚንስትሩ ፕሬዝደንት ባይደንን ለእስራኤል ከሃማስ ጋራ በምታካሂደው ጦርነት የምትዋጋበት ብዛት ያለው የጦር መሣሪያ በፍጥነት በመላክ ስላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል። ሥልጣን ላይ በነበሩበት ዘመን የዩናይትድ ስቴትስን ኤምባሲ ከቴል አቪቭ ወደ ኢየሩሳሌም በማዛወራቸው እና ሌሎች ድጋፎችን በመስጠታቸው የቀድሞውን ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕንም አመስግነዋቸዋል፡፡
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)፣ 14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን ለማካሔድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ሲገልጽ፣ የፓርቲው የቁጥጥር ኮሚሽን በአንጻሩ፣ ከጉባኤው ዝግጅት ራሱንና አባላቱን እንዳገለለ አስታውቋ፡፡
His remarks came in a rare Oval Office address to the American people explaining why he stepped down from the 2024 presidential race
His speech came after days of silence following his announcement he was ending his campaign for a second term
Police in Nairobi arrested some protesters Thursday
ዋሽንግተን — የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ከፕሬዝደንታዊ ምርጫው ፍክክር በድንገት ራሳቸውን ካገለሉ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ የሰጡበትን ንግግር ዛሬ ምሽት አድርገዋል። በአሜሪካ ፖለቲካ ከ50 ዓመታት በላይ ያስቆጠሩት ፕሬዝደንቱ ከኋይት ሐውስ «ኦቫል ኦፊስ» ጽሕፈት ቤታቸው ባደረጉት ንግግር «ይህንን ጽሕፈት ቤት እጅግ በጣም አከብረዋለሁ፣ ነገር ግን ሀገራችንን ከእርሱ በላይ እወዳታለሁ» ብለዋል። «የሀገራችንን አንድነት ለመጠበቅ የተሻለው መንገድ ችቦውን ለዐዲሱ ትውልድ ማስተላለፍ ነው» ሲሉ በንግግራቸው መልዕክት ያስተላለፉት ጆ ባይደን፣ ለዐዲስ ትውልድ ቦታውን መልቀቅ የተሻለ ነው ብለው መወሰናቸውን ተናግረዋል። የ81 ዓመቱ ባይደን ከሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩ ተፎካካሪው ከቀድሞ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ጋራ ካደረጉት ያልተዋጣ ክርክር በኋላ፣ በቀጠሉት ሳምንታት ዲሞክራቶች ከምርጫው ራሳቸውን እንዲያገሉ ቢወተውቷቸውም አሻፈረን ብለው የከረሙ ሲኾን በአንድ ወቅት «እሱን የማደርገው እግዚአብሔር አድርግ ካለኝ ብቻ ነው» ማለታቸው ተጠቅሷል። ባይደን በፕሬዝደንትነት በድጋሚ ለመመረጥ ከሚያደርጉት የምርጫ ፉክክር በድንገት ራሳቸውን ካገለሉ እና ቦታውን እንዲወዳደሩበት ምክትላቸው ካማላ ሃሪስን ዕጩ አድርገው ካቀረቡ በኋላ ንግግር ሲያደርጉ የመጀመሪያቸው ነው። «አሜሪካውያን ወገኖቼ» በማለት ንግግራቸውን የጀመሩት ባይደን ፣ ንግግር በሚያደርጉበት ኦቫል ጽሕፈት ቤት፣ በታላላቆቹ የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ፎቶ ግራፍ ተከበው ንግግር በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። «ሀገራችን የምትመራባቸውን ኗሪ ቃላት የጻፉት ቶማስ ጄፈርሰን፣ ፕሬዝደንቶች ነገሥታት እንዳልሆኑ ያስተማሩን ጆርጅ ዋሽንግተን፣ ክፉ መሥራትን እምቢኝ እንድንል የተማጸኑን አብራሃም ሊንከን፣ በፍርሃት እንዳንበገር ያበረታቱን ፍራንክሊን ሩዘቬልት» በማለት የቀደሙትን የዩናይድት ስቴትስ ፕሬዝደንቶች አስታውሰዋል። «ይኽንን ታላቅ ጽሕፈት ቤት አከብረዋለኹ። ከዛ የበለጠ ግን ሀገሬን እወደዋለኹ» ብለዋል። ባይደን ከውድድሩ ለመውጣት የወሰኑት በሪፐብሊካን ፓርቲው ዕጩ በቀድሞው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሊሸነፉ እንደሚችሉ የሚጠቁሙ ስጋቶች እየተበራከቱ በመሄዳቸው ነው። ባይደን ቢሸነፉ፣ ሌሎቹንም ዲሞክራቶች አብረው ለሽንፈት ሊዳርጉ እንደሚችሉ የጠቆሙ የሕዝብ አስተያየት ግምገማዎችን ተከትሎ ለበርካታ ቀናት ምን ማድረግ እንዳለባቸው በጭንቀት ሲያወጡ ሲያወርዱ ከቆዩ በኋላ ነው። «አሜሪካን ታላቅ ሀገር የሚያደርጋት በነገሥታት እና በአምባ ገነኖች የማትገዛ ስለሆነች ነው» ያሉት ባይደን፣ «የሚያስተዳድራት ሕዝቧ ነው። ታሪክ በናንተ እጅ ነው፣ ሥልጣን በእናንተ እጅ ነው፣ የአሜሪካ እምነቷ ያለው በእናንተ እጅ ነው» ብለዋል። ፕሬዝደንት ባይደን ከፕሬዝደንታዊ ምርጫው ዕጩ ተፎካካሪነት ለመውጣት መወሰናቸውን ባለፈው እሁድ በማኅበራዊ መገናኛ ካስታወቁ ወዲህ ዛሬ ለሕዝቡ ያደረጉት የመጀመሪያ ንግግራቸው ነው። ባይደን በፕሬዝደንትነት በሚቆዩባቸው በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ትኩረታቸው ሥራቸውን ማከናወን እንደሚሆን ተናግረዋል። «ለዲሞክራሲ መቆም ከማናቸውም የሥልጣን ስም ይልቃል። የእኔ ብርታት እና ደስታ ምንጭ የአሜሪካን ሕዝብ ማገልገል ነው። ይሁን እንጂ አንድነታችን ምሉእ ይሆንልን ዘንድ የምናደርገው የተቀደሰ ጥረታችን የእኔ የግል ጉዳይ ሳይሆን የእናንተ የቤተሰቦቻችሁ የወደፊት እጣ ፈንታችሁ ነው። ያሉት ባይደን »የሀገራችን ዲሞክራሲ በመራጮቿ እጅ ነው " ብለዋል ጆ ባይደን በፕሬዝደንትነት የሥልጣን ዘመናቸው ያከናወኗቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰጡት አመራር፣ ለሀገራቸው ያላቸው ራዕይ ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን የሚያበቃቸው መኾኑን የተናገሩት ባይደን ፣ ነገር ግን የፓርቲያቸውን አንድነት መምረጥ ስላለባቸው ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል። ፕሬዚደንት ባይደን ከሪፐብሊካን ፓርቲው ተፎካካሪያቸው ዶናልድ ትረምፕ ጋር ባደረጉት ክርክር ድክመት ያሳዩበት አፈጻጸም በአእምሮአዊ ብቃታቸው ዙሪያ ጥያቄ ካስከተለ በኋላ ከውድድሩ እንዲወጡ ውትወታው በርትቶባቸው ነበር ። ከእጩ ተፎካካሪነቱ ራሳቸውን ለማግለል ከወሰኑ በኋላ ግን ዲሞክራቶች ከጎናቸው በመቆም በፕሬዚደንትነት ስለአስመዘገቧቸው ክንዋኔዎች እንዲሁም ስለግል ባህሪአቸው አክብሮታቸውን ሲገልጹላቸው ይሰማሉ ። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር፣ በ1972 ዓም በ29 ዓመታቸው ለዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ተመርጠው የፖለቲካ ሞያቸውን የጀመሩት ባይደን፣ እንደ እ.አ.አ ጥር 20 ቀን 2025 ዓ.ም. በ82 ዓመታቸው ከሁሉም የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች የዕድሜ ባለጸጋው ፕሬዝደንት ኾነው የሥልጣን ዘመናቸውን ያጠናቅቃሉ። ፕሬዝደንት ባይደን በቀሪው የፕሬዝደንትነታቸው የመንፈቅ ጊዜ ሥራቸውን በትኩረት እያከናወኑ እንደሚቆዩ ያስታወቁ ሲሆን ነገ ሐሙስ ከእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋራ ተገናኝተው ስለጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ጥረቶች ይወያያሉ ። /ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል/
ዋሽንግተን — - ካማላ ሐሪስም የምርጫ ዘመቻቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ለኮቪድ 19 መጋለጣቸውን ተከትሎ ለአንድ ሳምንት ተገልለው የቆዩት ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ትላንት ማክሰኞ ወደ ኋይት ሐውስ ቤተ መንግሥት ተመልሰዋል፡፡ ባይደን ሙሉ በሙሉ ከእይታ ተሰውረው ይሰንብቱ እንጂ ከፕሬዚደንታዊ ምርጫ ፉክክሩ ለመውጣት ያደረጉት ውሳኔ የሳምንቱ አቢይ ዜና አድርጓቸዋል፡፡ ምክትል ፕሬዚደንታቸው ካማላ ሐሪስም በምርጫ ዘመቻ እየተዘዋወሩ መሆናቸውን አክላ የአሜሪካ ድምጹዋ አኒታ ፓወል ከኋይት ሐውስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
Authorities say the plane, which belonged to Saurya Airlines, was taking off when it crashed in the eastern part of Kathmandu airport.
The natural disasters are among the deadliest recorded in the east African nation.
Regulators also looking at Delta's treatment of passengers stranded by canceled and delayed flights and whether it violated federal rules.