በኬንያ እየተፈጸመ ነው የተባለው አፈና እንዲቆም የጠየቁ ተቃዋሚዎች እና ፖለቲከኞች ታሰሩ
newsare.net
በኬንያ መንግሥት ላይ ትችት የሚሰነዝሩ ወጣቶች ላይ ያነጣጠረው አፈና እንዲቆም በሚጠይቁ የጎዳና ላይ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ ተቃዋሚዎች እና አንድ ተቃዋሚ ፖለበኬንያ እየተፈጸመ ነው የተባለው አፈና እንዲቆም የጠየቁ ተቃዋሚዎች እና ፖለቲከኞች ታሰሩ
በኬንያ መንግሥት ላይ ትችት የሚሰነዝሩ ወጣቶች ላይ ያነጣጠረው አፈና እንዲቆም በሚጠይቁ የጎዳና ላይ ሰልፎች ላይ የተሳተፉ ተቃዋሚዎች እና አንድ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ሰኞ ዕለት መታሰራቸው ተገለጸ። የኬንያ ምክር ቤት አባል የሆኑት ሴናተር ኦኪያ ኦምታታህ፣ በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ተቃውሞ ያካሄዱ እና ፖሊስ በዚህ ወር ያገታቸውን ሰባት ሰዎች እንዲለቅ የሚጠይቁ መፈክሮችን ያሰሙ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ተቀላቅለዋል። ፖሊስ ተቃዋሚዎቹን ለመበተን አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ ቢሆን፣ ሴናተሩን ጨምሮ በርካታ ሰዎች እጅ ለእጅ ተቆላልፈው ከቦታው ለመነሳት ፈቃደኛ ባለመኾናቸው ለእስር መዳረጋቸው ተዘግቧል። የኬንያ ብሔራዊ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ባለፈው ሐሙስ በአወጣው መግለጫ በመንግሥት ተቺዎች ላይ እየተፈፀመ ነው የተባለው አፈና እየጨመረ መሄድ እንዳሳሰበው ገልጾ ነበር። በሰኔ ወር ከተካሄደው የመንግሥት ተቃውሞ ሰልፍ ወዲህ 82 ተመሳሳይ ውንጀላዎች እንደደረሱትም አመልክቷል። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በበኩላቸው ወጣቶች በሰላም እንዲኖሩ መንግሥት አፈናውን እንደሚያስቆም ቅዳሜ ዕለት ገልጸው ነበር። የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ከአፈናዎቹ ጀርባ ያለው የሀገሪቱ ፖሊስ መሆኑን በመግለፅ ክስ ቢያቀርቡም፣ ፖሊስ እጁ እንደሌለበት እና ደብዛቸው የጠፉ ሰዎች ጉዳይ ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጿል። Read more