17 February 2025   18:53:22
Ethiopia



ጣሊያን 49 ፍልሰተኞችን ወደአልቤኒያ ላከች

ጣሊያን ባህር ላይ ያገኘቻቸውን 49 ፍልሰተኞች በባሕር ኃይል መርከብ አሳፍራ ወደአልቤኒያ ልካለች። ጣሊያን  ስደተኞችን በሦስተኛ ሀገር ለማስፈር ያላት ዕቅድ

አፍሪካ ኅብረት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚነት ትኩረት እንዲሰጡ ትግራይ ክልል ጥሪ አቀረበ

ትግራይ ክልል ይኽን ጥሪ ያቀረበው፣ አዲስ አበባ ላይ ሲካሔድ የቆየው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ማጠናቀቂያ ቀን፣ በፕሪቶሪያ የተደረሰው በዘላቂነ�
የአሜሪካ ድምፅ

አፍሪካ ኅብረት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚነት ትኩረት እንዲሰጡ ትግራይ ክልል ጥሪ አቀረበ

ትግራይ ክልል ይኽን ጥሪ ያቀረበው፣ አዲስ አበባ ላይ ሲካሔድ የቆየው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ማጠናቀቂያ ቀን፣ በፕሪቶሪያ የተደረሰው በዘላቂነት ተኩስ የማቆም የሰላም ስምምነት በተመለከተ ለጋዜጠኞች በተሰጠ የማብራሪያ ሪፖርት ላይ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ላይ ያተኮረው ሪፖርት፣ ከመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ሲካሔድ ፣አጠቃላይ ሂደቱና ተገኝተዋል የተባሉ ትምሕርቶችን የተመለከተ ሪፖርት ይፋ ተደርጓል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ሌላኛውን የህወሓት ቡድንን የሚመሩት ዶ.ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ተገኝተዋል። ሁለቱ መሪዎች የእጅ ሰላምታ ተሰጣጥተውና ጎን ለጎን ተቀምጠው ተቀምጠው ማብራሪያና ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች፣ እንዲሁም ዋና አደራዳሪ የነበሩትን ኦሉሴጉን ኦባሳንጆን አና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ኃላፊዎችን ጨምሮ የተለያዩ አካላት ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓ መካከል ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በፕሪቶሪያ የተደረሰው በዘላቂነት ተኩስ የማቆም የሰላም ስምምነት በአፍሪካ ኅብረት መሪነት እውን የኾነ የመጀመሪያው ውጤታማ ተብሎ የሚጠቀስ የሰላም ስምምነት ነው፡፡ በሪፖርቱ ላይ መነሻውን በትግራይ ክልል አድርጎ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች የተስፋፋው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፣ ከተቀሰቀሰ ከአንድ ዓመት በኋላ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን፣ የቀድሞውን የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ የኅብረቱ የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ በማድረግ ለግጭቱ መፍትሔ እንዲያፈላልጉ በመሾም ግጭቱን በሰላም ለማስቆም ከተለያዩ አካላት ጋራ ያደረጋቸውን ጥረቶች ተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች ቀርበዋል፡፡  በአፍሪካ ኅብረት በነበረው በዚህ ዝግጅት ላይ ንግግር ካደረጉ አካላት መካከል የሆኑት ተሰናባቹ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት፣ “ይህ ሪፖርት በመላው አፍሪካ ሰላምን ለማስፈን ለምናደርገው ጥረት መማሪያ የሚኾነን ነው” ብለዋል፡፡ የፕሪቶሪያው የሰላም ሂደት “ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” የሚለውን መርህ አጉልቶ የሚያሳይ ነው” ያሉት ዋና አደራዳሪው የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በበኩላቸው፣ “አፍሪካዊ ተቋማት በአህጉሪቱ ያሉ ግጭቶችን መፍታት እና ሰላም ማውረድ እንደሚችሉ የሚያሳይ ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ህወሃትን በመወከል ስምምነቱን የፈረሙት የአሁኑ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው፣ “ብዙ የስምምነቱ ይዘቶች አልተፈጸሙም” በማለት፣ የአፍሪካ ኅብረት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ “አልተፈፀሙም” ባሏቸው ነጥቦች ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡ ከእነዚኽም መካከል የተፈናቃዮች ጉዳይ እና የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ ማስፈታት፣ መበተን እና ወደ ማኅበረሰቡ መልሶ ማዋሃድ (ዲዲአር) እንደሚገኙበት በአጽንኦት ገልፀዋል፡፡ «ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትኩረት የሚያደርገው በትጥቅ ማስፈታት ጉዳይ ላይ ብቻ ነው» ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ነገር ግን እነዚህን ታጣቂዎች መልሶ የማቋቋም ጉዳይም አብሮ የሚሄድ ጉዳይ መሆኑ መዘንጋት የለበትም ብለዋል፡፡ አሁን እዚህ እየተናገርን ባለንበት ወቅት “በርካታ ሴቶች እና ህፃናት በመጠለያዎች በስቃይ ላይ ይገኛሉ” በማለት፣ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች “በሕገመንግሥቱ የትግራይ አካል ወደሆኑ ወሰኖች የመመለሳቸው ጉዳይ” በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እና በአፍሪካ ኅብረት ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ብለዋል። የኢትዮጵያን መንግሥት በመወከል በፕሪቶሪያው ድርድር ከተሳተፉት ባለሥልጣናት አንዱ የሆኑት አሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትረ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ስምምነቱን ለመፈፀም የሚያስችሉ ርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡ ያልተፈፀሙ የሰምምነቱ ነጥቦች ደግሞ “በንግግር እና ሕግን ባከበረ መልኩ መቀጠል አለባቸው ብለዋል፡፡ የሰላም ስምምነቱን በዋና አደራዳሪነት የመሩት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ኦባሳንጆ፣ የዲዲአር እና የአወዛጋቢ ቦታዎች ጉዳይ መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ በይደር መታየት እንዳለባቸው ገልፀው “የስምምነቱን ተፈጻሚነት ሊጎዱ እና ወደ ኋላ ሊመልሱት አይገባም” ብለዋል፡፡

የሩስያ ወታደሮች በምስራቅ በዩክሬን ሃይሎች ላይ ጥቃቱን አጠናክረው ቀጥለዋል  

የሩስያ ወታደሮች በምስራቃዊ ዩክሬን ጥቃታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ አጠናክረዋል ሲል የኪዬቭ ጦር አስታውቋል፡፡  አንድ የኔቶ ባለስልጣን ሞስኮ ጦርነቱን ለመጨ�
የአሜሪካ ድምፅ

የሩስያ ወታደሮች በምስራቅ በዩክሬን ሃይሎች ላይ ጥቃቱን አጠናክረው ቀጥለዋል  

የሩስያ ወታደሮች በምስራቃዊ ዩክሬን ጥቃታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ አጠናክረዋል ሲል የኪዬቭ ጦር አስታውቋል፡፡  አንድ የኔቶ ባለስልጣን ሞስኮ ጦርነቱን ለመጨረስ በሚደረገው ውይይት የጥቃቱን ፍጥነት እና ጥንካሬ እንደሚጨምር ተንብየዋል።   ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሰላም እንዲሰፍን ግፊት እያደረጉ ባሉበትና የአሜሪካና ሩሲያ ባለስልጣናት በሚቀጥሉት ቀናት በሳውዲ አረቢያ ይገናኛሉ ትብሎ በሚጠበቅበት በአሁኑ ወቅት የሩስያ ጦር የተከፈተው ዋናዎቹ ጥቃቶቹ ያተኮሩት በፖክሮቭስክ የሎጂስቲክስ ማእከል አቅራቢያ መሆኑ ተገልጿል፡፡  የኪየቭ ጦር ትላንት ከሩሲያ ጋር በ24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ 261 ውጊያዎች ማድረጉን ገልጿል፣ ይህም በዚህ አመት ከፍተኛው ቁጥር ሲሆን በቀደሙት ቀናት ከተመዘገበው በመቶ እጥፍ የሚበልጥም ነውም ብሏል፡፡   የዩክሬን ወታደራዊ መረጃ እንደሚያመለክተው የሞስኮ ወታደሮች በእኤአ 2024 አጋማሽ ጀምሮ በምስራቅ በኩል መንደር በመንደር ቀስ በቀስ የገፉ መምጣታቸውን አስታውቀዋል።  ምንም እንኳን ፕሬዚደንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በምስራቅ በኩል “ ጥሩ ውጤት” ተገኝቷል ያሉ ቢሆንም፡፡  የወታደራዊ ሃይሉ ቃል አቀባይ በበኩላቸው የኪየቭ ሀይሎች የፒሽቻን መንደር መልሰው መያዛቸውን ተናግረዋል።   ፕሬዘዳንት ትራምፕ በመጀመሪያ ኪዬቭ ጋር ሳይማክሩ እና አውሮፓውያንን ሙሉ በሙሉ ለመተው ከሩሲያውያን ጋር በቀጥታ ለመገናኘት መገፋፋቸው በዩክሬን እና በአውሮፓ በኩል አስደንጋጭ ሁኗል ። የዩክሬን ባለስልጣናትም ትራምፕን ለማወደስ ጥንቃቄ አድርገዋል፡፡   ኪየቭ በሳዑዲ አረቢያ በሚደረገው ድርድር ላይ ለመሳተፍ እንዳልተጋበዘችና በማንኛውም ሁኔታ ከሩሲያ ባለስልጣናት ጋር ከመገናኘቷ በፊት ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ አጋሮቿ ጋር የጋራ ስትራቴጂ መንደፍ እንደምትፈልግ አስታውቃለች። 

በሩዋንዳ የሚደገፉት አማጽያን ሁለተኛ ከተማ ያዙ 

በሩዋንዳ የሚደገፉ አማፂያን ዛሬ ጥዋት በምስራቅ ኮንጎ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ  የሆነችውን ቡካቩን ይዘዋል፡፡  በአካባቢው ካለው የመንግስት ጦር ጥቂት መከላ�
የአሜሪካ ድምፅ

በሩዋንዳ የሚደገፉት አማጽያን ሁለተኛ ከተማ ያዙ 

በሩዋንዳ የሚደገፉ አማፂያን ዛሬ ጥዋት በምስራቅ ኮንጎ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ  የሆነችውን ቡካቩን ይዘዋል፡፡  በአካባቢው ካለው የመንግስት ጦር ጥቂት መከላከል ብቻ የገጠማቸው አማጽያኑ በከተማዋ የሚገኘውን የደቡብ ኪቩ ግዛት አስተዳደር ፅህፈት ቤትን የተቆጣጠሩት  ሲሆን አብዛኞቹም የአማፂያኑን ግስጋሴ በመፍራት ሸሽተዋል።    የኤም 23 አማፂያን በ101 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘውና ባለፈው ወር ከተቆጣጠሯት የጎማ ከተማ ለቀናት ተጉዘው ዛሬ እሁድ ጥዋት ማዕከላዊ ቡካቩ  ደርሰው በከተማው ሲዘዋወሩና በርካታ ነዋሪዎች በደስታ ሲጮሁ የአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኞች ተመልክተዋል። ይሁን እንጂ በአብዛኛው የከተማው ክፍሎች የሚገኙ ቤቶች ነዋሪዎች የሌሉባቸው ባዶ ሁነዋል፡፡   የኤም 23 አማፅያን በማዕድን የበለፀገውን ምስራቃዊ የኮንጎ  ክፍል ለመቆጣጠር ከሚሞክሩ ከአንድ መቶ በላይ ታጣቂ ቡድኖች ጎልተው ለመውጣት የቻሉ  ሲሆን ከጎረቤት ሩዋንዳ በመጡ 4ሽህ ወታደሮች እንደሚደገፉም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡  አማፅያኑ 1.3 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያለባትን ከተማ ሙሉ በሙሉ ስለመቆጣጠራቸው እስካሁን ግልጽ አልሆነም፡፡ ነገር ግን አመታትን ባስቆጠረው ውጊያ በማእከላዊ ቡካቩ መገኘታቸው ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ መስፋፋት ነው። በጎርጎሪዮሳዊዉ 2012 ከብሄር ግጭት ጋር በተገናኘ በተደረገዉ ጦርነት ጎማን ብቻ ከተቆጣጠሩበት ጊዜ በተለየ በአሁኑ ወቅት አማፂያኑ የፖለቲካ ስልጣንን ለማግኘት ፍላጎት አላቸው ሲሉ ተንታኞች ይናገራሉ።  የአማጽያኑ ወደ ቡካቩ መገስገስ ተከትሎ ብዙ የኮንጐ ወታደሮች ቅዳሜ እለት ከሺህ ከሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች ጋር ሲሸሹ ታይተዋል።  የኮንጎው ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኬዲ በብዙ ርቀት በምትገኘው ዋና ከተማ ኪንሻሳ የፀጥታ ስብሰባ አካሂደዋል፡  የቡካቩ ከተማ  በኤም 23 «የአጭር ጊዜ» ወረራ የተደረገባት ቢሆንም በኮንጎ ጦር ሰራዊት እና በአካባቢው ሚሊሻ አጋሮች ቁጥጥር ስር እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ በኤክስ ገጻቸው አስታውቀዋል፡ ዛሬ  በአብዛኛዎቹ የቡካቩ አካባቢዎች ምንም አይነት ውጊያ እንድሌለና  የኮንጐ ሃይሎችም እንዳልታዩ የአሶሼትድ ፕሬስ ዘገባ ያስረዳል፡፡   

ደቡብ አፍሪካውያን ነጮች ትራምፕን በመደገፍ ሰልፍ አካሄዱ 

አንዳንድ ደቡብ አፍሪካውያን ነጮች ትላንት ቅዳሜ ፕሪቶሪያ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ተሰባስበው ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያላቸውን ድጋፋ  የገለጡ ሲሆን
የአሜሪካ ድምፅ

ደቡብ አፍሪካውያን ነጮች ትራምፕን በመደገፍ ሰልፍ አካሄዱ 

አንዳንድ ደቡብ አፍሪካውያን ነጮች ትላንት ቅዳሜ ፕሪቶሪያ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ተሰባስበው ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያላቸውን ድጋፋ  የገለጡ ሲሆን  በገዛ መንግሥታቸው የዘረኝነት ሰለባ መሆናቸውንም ተናግረዋል።  በመቶዎች የሚቆጠሩት ሰልፈኞቹ  “ለፕሬዚዳንት ትራምፕ ፈጣሪ ይመስገን” የሚል ፅሁፎችን የያዙ እና በደቡብ አፍሪካ መንግስት የታወጀና አናሳ ነጭዎችን ለአድሎ የሚዳርግ የዘረኝነት ህግ ነው ያሉትንም  የሚተቹ ሌሎች መፈክሮችን ይዘው ታይተዋል።  የደቡብ አፍሪካ መንግስት በበኩሉ አዲሱ ህግ ከዘር ጋር የተያያዘ ነው ሲሉ ፕሬዘዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ እና በህጉ ላይ ያነሱት ጥያቄ የተሳሳተ መረጃ እና የተዛባ ነው ሲል አስተባብሏል፡፡  የትራምፕ አስተዳደር በደቡብ አፍሪካ ላይ የሰነዘረው ትችት እና ቅጣት በሀገሪቱ ለዘመናት የዘለቀው የአናሳ ነጮች አገዛዝና በጥቁሮች ላይ ያደረሱትን የጭቆና ጥፋቶችን ለመፍታት እየተወሰደ ያለውን ርምጃ አሳሳቢነት ከፍ አድርጎታል፡፡   የደቡብ አፍሪካ መንግሥት እንደሚለው፣ የመሬት ሕጉ  አብዛኛው የእርሻ መሬቶች የአገሪቱ ሕዝብ 7 በመቶው ብቻ በሆኑ ነጮች ባለቤትነት የተያዘውን በእኩልነትና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማከፋፈል ያለመ ነው፡፡   ነጭ ሰልፈኞች ወረራ ነው ያሉትን  ህግ ጨምሮ በ1994 ከአፓርታይድ ስርዐት ማብቂያ ጀምሮ ለጥቁሮች የቅድሚያ እድሎችን ለመስጠት የተደረጉ ማሻሽያዎችን የሚያመለክቱ ባነሮችን ይዘውም ታይተዋል።  “ብላክ ኢኮኖሚክ ኢምፓወርመንት” በመባል የሚታወቁት እነዚህ ህጎች ለአንዳንድ ነጮች የብስጭት ምክንያት ሆነዋል። 

በኦስትርያ አንድ ሰው ስድስት መንገደኞችን በስለት በመውጋት ጉዳት አደርሰ 

በደቡባዊ ኦስትሪያ የምትገኘው ቪላች ከተማ አንድ ሰው ቀን ላይ ስድስት መንገደኞችን በስለት ወግቶ የ14 አመት ወንድ ልጅ ሲገድል አምስት ሰዎችን ደግሞ አቁስሏል�
የአሜሪካ ድምፅ

በኦስትርያ አንድ ሰው ስድስት መንገደኞችን በስለት በመውጋት ጉዳት አደርሰ 

በደቡባዊ ኦስትሪያ የምትገኘው ቪላች ከተማ አንድ ሰው ቀን ላይ ስድስት መንገደኞችን በስለት ወግቶ የ14 አመት ወንድ ልጅ ሲገድል አምስት ሰዎችን ደግሞ አቁስሏል፡፡  ጥቃቱን ያደርሰው የ23 ዓመቱ ተጠርጣሪ ብዙም ሳይቆይ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በኦስትሪያ የመኖሪያ ፍቃድ ያለው ሶሪያዊ እንደሆነ ተገልጿል።   በምግብ አቅራቢ ድርጅት ውስጥ የሚሠራ ሌላ ሶሪያዊ መኪናውን ወደ ተጠርጣሪው በመንዳት ጉዳቱን ለማስቆምና እንዳይባባስ ረድቷል ሲልም ፖሊስ አስታውቋል። የኦስትሪያ ነፃ የሶሪያ ማህበረሰብ ከጥቃቱ ራሱን ያገለለ መግለጫ አውጥቷል።  60ሽህ የሚጠጉ ነዋሪዎች በሚኖሩባት ከተማ ነዋሪዎቹ ጥቃቱ በተፈፀመበት ቦታ ላይ ሻማ አብርተዋል። የኦስትሪያው ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ቫን ደር ቤለን ጥቃቱን “አሰቃቂ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ የኦስትሪያ ነፃ የሶሪያ ማህበረሰብ  በፌስቡክ በጥቃቱ እንደሌለበት በማሳወቅ ለተጎጂ ቤተሰቦች የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።  የኦስትሪያ ባለስልጣናት የስለት ጥቃቱን «እስላማዊ የሽብር ክስተት» በማለት ፈርጀውታል። የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ጌርሃርድ ካርነር ዛሬ እንደተናገሩት «በዚህ ከተማ ውስጥ ንፁሃን ዜጎችን ያለ ልዩነት በጩቤ በገደለው እስላማዊ ጥቃት አድራሽ  ቁጣ ተሰምቶኛል» ብለዋል።  ካርነር በቪላች ውስጥ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ጥቃት አድራሹ ከእስላማዊ መንግስት ቡድን ጋር ግንኙነት እንደነበረውና እራሱን  በአጭር ጊዜ ውስጥ አክራሪ አድርጎ በቀጥታ ድህረገጾች ሲያቀርብ ነበር ብለዋል፡፡  ይህ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኦስትሪያ ውስጥ ሁለተኛው ገዳይ ጥቃት ነው። እ.ኤ.አ. በህዳር 2020፣ ከዚህ ቀደም እስላማዊ መንግስት ቡድንን ለመቀላቀል የሞከረ አንድ ሰው በቪየና ውስጥ ጥቃት አድርሶ እንደነበረ አሶሼትድ ፕሬስ አስታውሷል፡፡ 

 ታዳጊዎችን የሚያግዘው ማኅበር

በሐረር  ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በቁሳቁስና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያግዘው ድንበር የለሽ የሐረር ልጆች ማኅበር ሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ የከተማዋ ተወ�
የአሜሪካ ድምፅ

 ታዳጊዎችን የሚያግዘው ማኅበር

በሐረር  ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በቁሳቁስና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚያግዘው ድንበር የለሽ የሐረር ልጆች ማኅበር ሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ የከተማዋ ተወላጆች የተመሰረተ ነው፡፡ ደግሞ በትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ምገባ ለመጀመር የገንዘብ ድጋፍን እያፈላለገ እንደሚገኝ የማኅበሩ ፕሬዝደንት  ዶክተር ማሾ አብርሃ ተናግረዋል፡፡ ነዋሪነታቸውን በዩናይትድ ስቴትት ጆርጅያ ግዛት ካደረጉት የማኅበሩ ፕሬዝደንት  ዶክተር ማሾ ጋራ ያደረግነውን ቆይታ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።   

የቡና ዲፕሎማሲ

ኢትዮጵያውያን አንኳር ባህል እና የማኅበራዊ ሕይወት ማድመቂያ የኾነው የቡና አፈላል ሥነ ሥርዐት በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ መሰብሰቢያ አዳራሽ �
የአሜሪካ ድምፅ

የቡና ዲፕሎማሲ

ኢትዮጵያውያን አንኳር ባህል እና የማኅበራዊ ሕይወት ማድመቂያ የኾነው የቡና አፈላል ሥነ ሥርዐት በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለእንግዶች መስተናገጃ ቀርቧል። ከጉባኤው ጎን ለጎን የኢትዮጵያ ባህል እና ቱሪዝም ሀብቶችን ለተሳታፊዎች የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ መኾኑንም የቱሪዝም ሚኒስትር ድኤታ ዶር. እንደገና አበበ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ ተፈጽመዋል ላላቸው ቀደምት በደሎች የካሳ ጥያቄ አነሳ

ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው 38ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ «የማካካሻ ፍትሕ» ጥያቄ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኗል፡፡ በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያው
የአሜሪካ ድምፅ

አፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ ተፈጽመዋል ላላቸው ቀደምት በደሎች የካሳ ጥያቄ አነሳ

ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው 38ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ «የማካካሻ ፍትሕ» ጥያቄ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኗል፡፡ በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ የማካካሻ ጥያቄው “የርዳታ ሳሆን የፍትሕ ጥያቄ ነው” ብለዋል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ደግሞ “ለማካካሻ ፍትሕ ማዕቀፎች ጊዜው አሁን ነው” ሲሉ ጥያቄው መልስ እንዲያገኝ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው የኅብረቱ ዋና አዳራሽ ሲጀመር፣ እንደ የባሪያ ፍንገላ፣ ቅኝ ግዛት እና አፓርታይድ ላሉ በአህጉሪቱ ለተፈጸሙ ቀደምት ኢ-ፍትሐዊ ተግባራት የማካካሻ ፍትሕ ጥያቄ ማቅረብን ዋነኛ አጀንዳው አድርጓል፡፡ «የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል መሪ ቃል በተጀመረው በዚህ ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ጥያቄው ፍትሕን የመሻት ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡ “የማካካሻ ጥያቄው የበጎ አድራጎት ወይም የገንዘብ ርዳታ ጥያቄ አይደለም» ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ «ስለ ፍትሕ ነው። የሚሊዮኖችን ክብር የመመለስ እና ጥልቅ የሆነ የድህነት፣ የመበላለጥ እና የአድሎ ጠባሳን መፈወስን የሚጠይቅ ነው። በሀብቶቻችን እና ዕድሎቻችን ላይ የሚፈጸመው ስልታዊ ብዝበዛን እንዲቆም ይጠይቃል። በተጨማሪም በአህጉሪቱ ውስጥ ባሉ ማኅበረሰቦች ላይ የተፈጠሩ በደሎችን ለማረም ድፍረት የተሞላበት ርምጃ የሚወሰድበት የለውጥ ሂደት እንዲኖር የሚጠይቅ ነው። ከሁሉም በላይ፣ የማካካሻ ጥሪው የእያንዳንዱን ሰው እኩልነት ለማረጋገጥ ቃላትን ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ ድርጊቶችን ይጠይቃል።” ብለዋል። በኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥም፣ የኅብረቱ የካሳ ጥያቄ አግባብ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ “አፍሪካ የሁለት ከባድ እና የተወሳሰቡ ኢፍትሃዊ ድርጊቶች ሰለባ መሆኗን ዓለም መዘንጋት የለበትም።እነዚህም፣ የቅኝ ግዛት እና የአትላንቲክ የባሪያ ንግድ ከፍተኛ ተጽዕኖዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጊቶች ሥረ መሰረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዓመታትን ያስቆጠረ ነው፡፡ መራራ ፍሬው ግን አፍሪካውያንን እና ዘርዓ-አፍሪካውያንን እስከ ዛሬ ድረስ እየጎዳ ነው፡፡ ከቅኝ ግዛት መላቀቅ በራሱ መድኃኒት አይደለም። የፖለቲካ ነፃነት፣ ሀገሮችን በብዝበዛ ላይ ከተመሠረቱ መዋቅሮች እና ለበርካታ ዐስርት ዓመታት ከዘለቀው የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ እና ተቋማዊ የኢንቨስትመንት እጥረት ነፃ አላደረገም። ለማካካሻ ፍትህ ማዕቀፎች ጊዜው አሁን ነው።” ብለዋል። የኅብረቱ አባል ሀገራት መሪዎች በሁለት ቀናት በሚያደርጉት ውይይት በዚሁ የማካካሻ ፍትኅ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያደርጉ፣ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ስፍራን ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ዛሬ የተረከቡት የአንጎላው አቻቸው ዡዋ ሎሬንሶ ተናግረዋል፡፡ “በዚህ ጉባኤ በብዙ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል» ያሉት ዡዋ ሎሬንሶ "ነገር ግን ለአህጉራችን በጣም አስፈላጊ የሆኑት የአፍሪካ ህብረት የስራ ማዕቀፍ እና ለዚህ ዓመት በመሪ ሃሳብነት የተመረጠውን፣ ለአፍሪካ እና ለትውልደ አፍሪካውያን የማካካሻ ፍትህን ተግባራዊ እንዲሆን የማድረግ ጉዳይ ዋናዎቹ ናቸው” ብለዋል። የማካካሻ ፍትሕ ጥያቄውን በተመለከተ አስተያየታቸውን የሰጡን የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪና የፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ሄኖክ ጌታቸው፣ ጠያቄው አሁን ዋና አጀንዳ ቢሆንም ከከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ጀምሮ በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲነሳ የነበረ ነው ብለዋል፡፡ ከማካካሻ ፍትሕ በተጨማሪ፣ የአኅጉሪቱ ፈተና ኾኖ የቀጠለውን የሰላምና ፀጥታ እጦት ጨምሮ፣ የወጣቶች ጥያቄ፣ ትምህርትና ጤናን የመሳሰሉ ጉዳዮችም የውይይት አጀንዳዎች እንደሚሆኑም ተገልጿል፡፡ ተሰናባቹ የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሃማት፣ በአኅጉሪቱ የቀጠሉ ግጭቶች ከሌሎች ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ቀውሶች ጋር ተዳምረው በአብዛኛው የኅብረቱ አባል አገራት ወትሮውንም የነበረውን የደኅንነት ምግብ የጤና እና መሰል ችግሮች እያባባሰ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የተማሪዎችን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ግንዛቤ የሚያዳብረው መርሐ ግብር

«ሞዴል ዩኤን» ወይም «አምሳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት»፦ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ዲፕሎማሲን እንዲማሩ፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የትኩረ
የአሜሪካ ድምፅ

የተማሪዎችን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ግንዛቤ የሚያዳብረው መርሐ ግብር

«ሞዴል ዩኤን» ወይም «አምሳለ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት»፦ ተማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ዲፕሎማሲን እንዲማሩ፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የትኩረት አቅጣጫ በኾኑ የልማት ግቦች ላይ ግንዛቤን እንዲያዳብሩ የሚደረግ የውይይት እና የክርከር መርሐ ግብር ነው፡፡  መርሐ ግብሩ፣ ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ በብዙ ሀገራት የተዘረጋ መድረክ ነው። በዩናይትድ ስቴትስ ከሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ የኾነው ጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ፣ በየዓመቱ ከልዩ ልዩ የዓለም ክፍሎች ለመጡ ተማሪዎች መርሐ ግብሩን ያዘጋጃል፡፡በዘንድሮው መርሐ ግብር፣ 45 ኢትዮጵያውያን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ከባላፈው ቅዳሜ የካቲት አንድ 2017 ዓ.ም አንስቶ ሁለት ሳምንት በሚዘልቀው መርሃግብር ላይ ለሁለተኛ ጊዜ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ የመርሐ ግብሩ አስተባባሪ፣ በትምህርት ላይ የሚሠራው «ኦል ፋውንዴሽን» ሲኾን፣ የተቋሙ መሥራች እና የቦርድ ፕሬዝዳንት አቶ ኑርሑሴን ሐሰን ሑሴን፣ ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ ቆይታ አድርገዋል፡:

የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾኑ

ጅቡቲን ለብዙ ዓመታት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ያገለገሉት መሐመድ ዓሊ ዩሱፍ ቀጣዩ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾነው ተመረጡ። ‘ አዲስ አበባ ውስ�
የአሜሪካ ድምፅ

የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾኑ

ጅቡቲን ለብዙ ዓመታት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ያገለገሉት መሐመድ ዓሊ ዩሱፍ ቀጣዩ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ኾነው ተመረጡ። ‘ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሔደ ባለው 38ኛው የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ላይ፣ መሪዎቹ በሚስጥር በሰጡት ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ኮሚሽኑን በሊቀመንበርነት እንዲመሩ ተመርጠዋል። ኮሚሽኑን እንዲመሩ በሊቀመንበርነት የተመረጡት የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ በተካሔደውና ብርቱ ፉክክር በታየበት፣ እንዲኹም እስከ ሰባተኛ ዙር ድረስ በዘለቀ ምርጫ ሁለት ሦስተኛ ድምጽ አግኝተው ነው። ከሳምንት በፊት 60ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት ዩሱፍ፣ በምርጫው አሸናፊ የኾኑት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነው። ዩሱፍ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዙሮች በ18 እና በ19 ድምፅ አግኝተው ከራኢላ ጋራ በተቀራረበ ሁኔታ ሁለተኛ ዙር ላይ ነበሩ። ከሦስተኛው ዙር ጀምሮ በተካሔዱት የድምጽ አሰጣቶች ግን ዩሱፍ በመሪነት ቀጥለዋል። በመጨረሻም ለአሸናፊት የሚያበቃው 33 ድምጽ በማግኘት የመሪነቱ ቦታ ተረክበዋል። አዲሱ የኅብረቱ ተመራጭ ኮሚሽነት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር፣ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኾነው አገልግለዋል። በአፍሪካ አህጉር ረዥም ጊዜ ያገለገሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ናቸው።  ከኅብረቱ ከታገዱት ስድስት ሀገራት በስተቀር 55ቱም የአባል ሀገራት በ38ኛው የኅብረቱ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጭ ለቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት እንደተናገሩት፣ 29 ፕሬዝዳንቶች ፣ ሦስት ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ አራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች እና አንድ ንጉስ በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል። ከአፍሪካ ኅብረት አባልነት የታገዱት ስድስቱ ሀገራት ቡርኪናፋሶ፣ጋቦን፣ጊኒ፣ማሊ፣ኒጀር እና ሱዳን ናቸው። የዘንድሮው የመሪዎች ጉባኤ በመካሔድ ላይ የሚገኘው በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግጭት እየተባባሰ ባለበት ወቅት አማጽያን በምስራቃዊ የሀገሪቱ ክፍሎች እየገሰገሱ ባሉበት ወቅት ነው። የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች አስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ጥሪ አቅርበዋል። መሪዎቹ ሊወያዩበት ያቀዱት ሌላው የግጭቱ ዋና ማዕከል ሱዳን ናት። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ሱዳን ውስጥ የሚገኙ ተፋላሚ ወገኖች ጦርነቱን እንዲያቆሙ እና የሰብአዊ አገልግሎት ሠራተኞች እና ሲቪሎችን ደኅንነት እንዲጠብዙ ጥሪ አቅርበዋል። ጉቴሬዥ 26 ሚሊዮን ለሚጠጉ አስቸኳይ ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሱዳናውያን ዜጎች 6 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ጠይቀዋል።

የኤም 23 አማጽያን በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሁለተኛ ቁልፍ ከተማ ተቆጣጠሩ

በምሥራቃዊ ኮንጎ ውስጥ ያሉ አማፂዎች ለዓመታት ከዘለቀውን፤ ከመንግስት ሃይሎች ጋር ያደረጉት ውጊያ  ተባብሶ ከቀጠለ በኋላ ትላንት አርብ ዕለት ወደ ሁለተኛዋ
የአሜሪካ ድምፅ

የኤም 23 አማጽያን በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሁለተኛ ቁልፍ ከተማ ተቆጣጠሩ

በምሥራቃዊ ኮንጎ ውስጥ ያሉ አማፂዎች ለዓመታት ከዘለቀውን፤ ከመንግስት ሃይሎች ጋር ያደረጉት ውጊያ  ተባብሶ ከቀጠለ በኋላ ትላንት አርብ ዕለት ወደ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ ቡካቩ መግባታቸውን የአካባቢው እና የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች አስታውቀዋል። የኤም 23 አማፂዎች ወደ ከተማዋ ካዚንጉ እና ባጊራ ዞን ገብተው 1.3 ሚሊዮን ህዝብ ወደ የሚኖርበት መሃል ከተማ እየገሰገሱ ነው፤ በማለት በደቡብ ኪቩ የሚገኘው የሲቪል ማኅበረሰብ ምክትል ፕሬዝዳንት ዣን ሳሚ ተናግረዋል። ምክትል ፕሬዝዳንት ዣን ሳሚ በከተማው አንዳንድ አካባቢዎች የተኩስ ልውውጥ መደረጉን አስታውቀዋል። የተለያዩ በድረገጽ ላይ የተለጠፉ ተንቀሳቃሽ ምስሎች አማፂዎቹ አማ ወደ ባጊራ ወደተሰኙ አካባቢዎች ሲዘምቱ የሚያሳዩ ይመስላል። ከተንቀሳቃሽ ምስሎቹ በአንዱ ላይ፤ ከጀርባ ያለው ድምጽ “እዚያ አሉ... ብዙዎቹ አሉ” እያለ የሚጮህ ድምጽ ይሰማበታል።   ከክስተቱ ሰዓታት በፊት አማፂያኑ በካቩሙ ከተማ የሚገኘውን ሁለተኛውን አውሮፕላን ማረፊያ መቆጣጠራቸውን አስታውቀዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቅርቡ ከመንግስት ሃይሎች ጋር የቀጠለው ጦርነት 350,000 ተፈናቃዮችን ያለ መጠለያ አስቀርቷል በማለት አስጠንቅቋል። የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት ሩዋንዳ የኤም 23 አማፂ ቡድንን እየደገፈች ነው በማለት በተደጋጋሚ ቢወንጅለም  ሩዋንዳ አስተባብላለች። በአንጻሩ ኪጋሊም በበኩሏ ኪንሻሳ እ.ኤ.አ.1994 በሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ያስከተለውን፤ የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ሃይል (ኤፍ.ዲ.ኤል.አር) ጋር በመተባበር የሁቱ ታጣቂ ቡድን ትደግፋለች በማለት የምትከስ ሲሆን ኪንሻሳ ውንጀላውን አትቀበለውም።

የአንጎላውን ፕሬዝደንት ዡዋ ሎሬንሶ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ኾኑ

በአዲስ አበባ እየተካሔደ ባለው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የአንጎላውን ፕሬዝደንት ዡዋ ሎሬንሶ  የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነታቸውን ተረክበዋል�
የአሜሪካ ድምፅ

የአንጎላውን ፕሬዝደንት ዡዋ ሎሬንሶ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ኾኑ

በአዲስ አበባ እየተካሔደ ባለው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የአንጎላውን ፕሬዝደንት ዡዋ ሎሬንሶ  የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነታቸውን ተረክበዋል።  ዡዋ ሎሬንሶ ተሰናባቹን ሊቀመንበር የሞሪታኒያ ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ኦልድ ቼክ ጋዙዋንን ተክተዋል። ብሩንዲ፣ ጋና እና ታንዛኒያ የአፍሪካ ኅብረት ምክትል ሊቀመንበር እንዲኾኑ ተመርጠዋል።  ከኅብረቱ ከታገዱት ስድስት ሀገራት በስተቀር 55ቱም የአባል ሀገራት በ38ኛው የኅብረቱ መሪዎች ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ ነው።  የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጭ ለቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት እንደተናገሩት፣ 29 ፕሬዝዳንቶች ፣ ሦስት  ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ አራት  ጠቅላይ ሚኒስትሮች እና አንድ ንጉስ በጉባኤው ላይ ተሳትፈዋል። ከአፍሪካ ኅብረት አባልነት የታገዱት ስድስቱ ሀገራት ቡርኪናፋሶ፣ጋቦን፣ጊኒ፣ማሊ፣ኒጀር እና ሱዳን ናቸው። የዘንድሮው የመሪዎች ጉባኤ በመካሔድ ላይ የሚገኘው በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግጭት እየተባባሰ ባለበት ወቅት አማጽያን በምስራቃዊ የሀገሪቱ ክፍሎች እየገሰገሱ ባሉበት ወቅት ነው። የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች አስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ጥሪ አቅርበዋል። ሱዳን መሪዎቹ ሊወያዩበት ያቀዱት ሌላው የግጭቱ ዋና ማዕከል ነው። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዥ ሱዳን ውስጥ የሚገኙ ተፋላሚ ወገኖች ጦርነቱን እንዲያቆሙ እና የሰብአዊ ሠራተኞችን ጨምሮ ሲቪሎችን እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል። ጉቴሬዥ 26 ሚሊዮን የሚጠጉ ሱዳናውያን አስቸኳይ ርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች 6 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ጠይቀዋል።

የዐቅም ውስንነት ያለባቸውን ልጃገረዶች እና ቤተሰቦቻቸውን በማገዝ የሚያበቃው ተቋም

‘ሪሶርስስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን ላይፍ’ ወይም በአኅጽሮት 'ሪል ገርልስ'፦ ነዋሪነታቸውን በዩናይትድ ስቴትስ ባደረጉት የሦስት ልጆች እናት ወሮ. ፀሓይ ወዳጆ የ�
የአሜሪካ ድምፅ

የዐቅም ውስንነት ያለባቸውን ልጃገረዶች እና ቤተሰቦቻቸውን በማገዝ የሚያበቃው ተቋም

‘ሪሶርስስ ኢንሪቺንግ አፍሪካን ላይፍ’ ወይም በአኅጽሮት 'ሪል ገርልስ'፦ ነዋሪነታቸውን በዩናይትድ ስቴትስ ባደረጉት የሦስት ልጆች እናት ወሮ. ፀሓይ ወዳጆ የተመሠረተ ተቋም ነው።  ተቋሙ፣ ላለፉት ኻያ ዓመታት፣ ከ650 በላይ ልጃገረዶችንና ከሦስት ሺሕ በላይ ቤተሰቦችን፥ በገንዘብ፣ በደንብ አልባሳት፣ በጥናት ድጋፍ እና በግል በማማከር የማብቃት(ሜንቶርሽፕ) አገልግሎትን በመስጠት አግዟል።  ወ/ሮ ፀሓይ፣ «የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሳለሁ ትምህርቴን እንዳላቋርጥ ታደገውኛል፤» የሚሏቸው ስዊዲናዊቷ ኤቫ ኖርዲን ያሳደሩባቸው በጎ ተጽእኖ፣ የዛሬውን ተቋም የመመሥረት ሐሳብ በልባቸው እንዲጠነሰስ መነሻ እንደኾናቸው ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።  ኤደን ገረመው፣ ወሮ. ፀሓይንና በተቋሙ ድጋፍ የተደረገላቸውን ወጣቶች አነጋግራ ተከታዩን ጥንቅር አሰናድታለች።

ለአስታማሚዎች ሊደረጉ የሚገቡ ድጋፎች

አስታማሚዎች ወይም እንክብካቤ አድራጊዎች የታማሚን ንጽህና መጠበቅ፣ መመገብ፣ መድሃኒት በአግባቡ እንዲወስዱ ማገዝን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊነቶችን ይሸከማሉ�
የአሜሪካ ድምፅ

ለአስታማሚዎች ሊደረጉ የሚገቡ ድጋፎች

አስታማሚዎች ወይም እንክብካቤ አድራጊዎች የታማሚን ንጽህና መጠበቅ፣ መመገብ፣ መድሃኒት በአግባቡ እንዲወስዱ ማገዝን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊነቶችን ይሸከማሉ። አብዛኞቹም ተገቢ የሆነ ታማሚን የመንከባከብም ሆነ እራሳቸውን የሚጠብቁበት መንገድ ግንዛቤ ስለሌላቸው፤ ጊዜ በገፋ ቁጥር እራስን ለመጣል፣ ለብቸኝነት፣ እና ድባቴ ይጋለጣሉ። ለመሆኑ አስታማሚዎች ምን ዓይነት ድጋፍ ይሻሉ?

የትረምፕ በጅምላ ማባረር እና እስራትን የማስፋት የኢምግሬሽን ፖሊሲዎች

የትረምፕ አስተዳደር የተወሰኑ ስደተኞችን በአስቸኳይ ወደ ኩባ ጓንታናሞ ቤይ መላኩ እና ሌሎችንም በጅምላ የማባረር እቅድ በፍጥነት እያካሄደ ነው። የዩናይት�
የአሜሪካ ድምፅ

የትረምፕ በጅምላ ማባረር እና እስራትን የማስፋት የኢምግሬሽን ፖሊሲዎች

የትረምፕ አስተዳደር የተወሰኑ ስደተኞችን በአስቸኳይ ወደ ኩባ ጓንታናሞ ቤይ መላኩ እና ሌሎችንም በጅምላ የማባረር እቅድ በፍጥነት እያካሄደ ነው። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ቢሮ በገቡበት የመጀመሪያ ቀን ሕገ ወጥ ስደትን በአስቸኳይ ብሔራዊ ዐዋጅነት አውጥተዋል። በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት የገቡትን ቁልፍ ቃል በመከተል በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸውን ስደተኞች ለማባረር ቃል ገብተዋል። አሊኒ ቫሮስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ፕሬዝደንት ትረምፕ የህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ኔራንድራ ሞዲን በኋይት ቤተ መንግሥት አስተናገዱ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ትላንት ሐሙስ ከህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ኔራንድራ ሞዲ  ጋራ በርከት ያሉ የኃይል ምንጭ (ኤነርጂ) እና የመከላከያ �
የአሜሪካ ድምፅ

ፕሬዝደንት ትረምፕ የህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ኔራንድራ ሞዲን በኋይት ቤተ መንግሥት አስተናገዱ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ትላንት ሐሙስ ከህንድ ጠቅላይ ሚንስትር ኔራንድራ ሞዲ  ጋራ በርከት ያሉ የኃይል ምንጭ (ኤነርጂ) እና የመከላከያ ስምምነቶች  ተፈራርመዋል። ሞዲ ፕሬዝደንት ትረምፕ ሁለተኛውን የሥልጣን ዘመናቸውን ከጀመሩ ወዲህ ኋይት ሃውስን ሲጎበኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። ትረምፕ በአሜሪካ የንግድ አጋሮች ላይ አጸፋ ቀረጥ እንደሚጣል አመልክተዋል። ህንድ ቀረጦቹን ለመከላከል ጥረት ስታደርግ መቆየቷን ጠቅሳ አኒታ ፓወል ከኋይት ሐውስ ያሰናዳችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ትረምፕ ሩሲያ ወደ ቡድን ሰባት እንድትመለስ ላቀረቡት ጥያቄ፣ ክሬምሊን ቡድኑ ጠቀሜታውን አጥቷል ስትል ምላሽ ሰጠች

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሩሲያ ወደ ቡድን ሰባት ሀገራት አባልነት እንድትመለስ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ ክሬምሊን፣ የቡድን �
የአሜሪካ ድምፅ

ትረምፕ ሩሲያ ወደ ቡድን ሰባት እንድትመለስ ላቀረቡት ጥያቄ፣ ክሬምሊን ቡድኑ ጠቀሜታውን አጥቷል ስትል ምላሽ ሰጠች

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሩሲያ ወደ ቡድን ሰባት ሀገራት አባልነት እንድትመለስ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውን ተከትሎ፣ ክሬምሊን፣ የቡድን ሰባት ከዚህ በኋላ በዓለም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ያላቸውን ሀገራት እንደማይወክል አስታውቃለች። ትረምፕ ትላንት ሐሙስ «ቢመለሱ ደስ ይለኛል። እነሱን ከቡድኑ ማስወጣት ስህተት ነበር ብዬ አምናለሁ። ሩሲያን የመውደድ እና ያለመውደድ ጥያቄ አይደለም። ይሄ ቡድን ስምንት ነበር።» ብለዋል። ሩሲያ ቡድን ስምንት ተብሎ ይጠራ የነበረው የዓለማችን ባለጸጋና ኃያላን ሀጋራት ማኅበር አባል የነበረች ሲሆን፣ እ.አ.አ በ2014 ሞስኮ የዩክሬን አካል የነበረውን ክሬሚያ ቀጠና ወደ ግዛቷ መጠቅለሏን ተከትሎ ከቡድኑ እንድትወጣ ተደርጋለች። የትረምፕን ንግግር ተከትሎ ምላሽ እንዲሰጡ የተጠየቁት የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በሰጡት አስተተያየት «አሁን ቡድን ሰባት ተብሎ የሚጠራው ቡድን ጠቀሜታውን አጥቷል። ከእድገት አንፃር በተለያዩ መመዘኛዎች መሪ ያልሆኑ ሀገራትን የያዘ ስብስብ ነው» ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። የዕድገት ማዕከል ወደሌሎች የዓለም ቀጠናዎች ተሻግሯል« ያሉት ቃል አቀባዩ፣ ይልቁንም »ቡድን 20 በተሰኘው ማዕቀፍ ውስጥ ገንቢ ሥራችንን በተሻለ ሁኔታ የመቀጠል ፍላጎት አለን። ቡድን 20 የዓለምን ኢኮኖሚ የተሻለ ያንፀባርቃል" ሲሉ ተናግረዋል። 

የጀርመኑ ቀኝ አክራሪ ፓርቲ ድጋፍ ማሰባሰቡን ቀጥሏል

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2013 የተመሰረተው የቀኝ አክራሪው 'አማራጭ ለጀርመን' ፓርቲ በመላ ሀገሪቱ ጠንካራ ድጋፍ እያገኘ መኾኑ ተገልጿል። ጀርመን በዚህ ወ
የአሜሪካ ድምፅ

የጀርመኑ ቀኝ አክራሪ ፓርቲ ድጋፍ ማሰባሰቡን ቀጥሏል

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2013 የተመሰረተው የቀኝ አክራሪው 'አማራጭ ለጀርመን' ፓርቲ በመላ ሀገሪቱ ጠንካራ ድጋፍ እያገኘ መኾኑ ተገልጿል። ጀርመን በዚህ ወር ለምታካሂደው አጠቃላይ ምርጫ ተፎካካሪ ሆኖ የቀረበው ፓርቲ የሚያገኘው ድጋፍ የጨመረው፣ በዋናነት በሀገሪቱ በሚገኙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ምክንያት መሆኑም ተመልክቷል። የስደተኞች ጉዳይ፣ ፓርቲው ማዕከል አድርጎ የሚሠራበት ዋና አጀንዳ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሩሲያ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በአስቸኳይ ማንሳትን የመሳሰሉ ሌሎች ጉዳዮች ላይም ትኩረት ማድረግ ጀምሯል። አፍዲ በሚል ምጽሃረ ቃል የሚጠራው አማራጭ ለጀርመን ፓርቲው ለቻንስለርነት እንዲወዳድሩ ያጫቸው አሊስ ዊዴል፣ ስደተኞችን በጅምላ ወደመጡበት መመለስ የሚለው አዲስ ፅንሰ ሐሳብ ደጋፊ መሆናቸው ተመልክቷል። የፖለቲካ ተንታኞች ዊዴል ቻንስለር የመሆን እድላቸው አናሳ ነው ቢሉም፣ የፓርቲው ድጋፍ እየጨመረ መሄድ፣ ፖለቲከኞች በስደተኞች ዙሪያ የሚያደርጓቸውን ውይይቶች እና ክርክሮች እንደገና እንዲያስቡበት እያስገደዳቸው ነው። አፍዲ ለመጀመሪያ ጊዜ በፓርላማ መቀመጫ ያገኘው እ.አ.አ በ2017 ዓ.ም 12.6 ከመቶ ድምፅ አግኝቶ ነው። ፓርቲው የፖለቲካ ተዋናይ ሆኖ ድጋፍ እያገኘ ባለበት ወቅትም፣ የኦስትሪያው ፍሪደም ፓርቲ እና የፈረንሳዩ ናሽናል ራሊ የመሳሰሉ ቀኝ አክራሪ ፓርቲዎች ያላቸው ተቀባይነት እያደገ መሆኑ ተመልክቷል። 

በርካታ ዓመታትን ያስቆጠሩ የብሔራዊ ቤተመንግሥት ታሪካዊ ተሽከርካሪዎች

በፈረንሳይ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የታደሰውና በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመንግሥት ወይም ኢዮቤልዩ  ቤተመንግሥት ካካተታቸው ነገሮች አ�
የአሜሪካ ድምፅ

በርካታ ዓመታትን ያስቆጠሩ የብሔራዊ ቤተመንግሥት ታሪካዊ ተሽከርካሪዎች

በፈረንሳይ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የታደሰውና በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመንግሥት ወይም ኢዮቤልዩ  ቤተመንግሥት ካካተታቸው ነገሮች አንዱ የተሽከርካሪዎች ትዕይንት ማሳያ ሰፍራ ነው። ከቀዳማዊ አጼ ኃ/ሥላሴ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ድረስ የነበሩ መሪዎች የተገለገሉባቸውና የተለያዩ አገራት አቻዎቻቸውን ያስተናገዱባቸው ተሽከርካሪዎች በስፍራው ለዕይታ መቅረባቸውን የብሔራዊ ቤተመንግሥት ሙዚየምና ቅርስ አስተዴደር ማዕከል ኃላፊ ምንተስኖት ጢቆ ይናገራሉ። ለትዕይንት ከቀረቡት ተሽከርካሪዎች መካከል፣ የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ መሪ የነበሩት ማርሻል ቲቶ እና የቀድሞው የኩባ ፕሬዝዳንት ፊደል ካስትሮ ወታደራዊ ትዕይንቶችን በአዲስ አበባ የተመለከቱባት በአሜሪካን የተመረተች ላንድ ሮቨር ተሽከርካሪ ትገኛለች። ተሽከርካሪዋ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ እና በኮሎኔል መንግሰቱ ኃይለማርያም የስልጣን ዘመን አገልግሎት መስጠቷን አቶ ምንተስኖት ጠቅሰዋል። ሌሎች ታሪካዊ ተሽከርካሪዎችና ንጉሳዊ የባቡር ፉርጎዎችም በዚህ የተሽከርካሪዎች ትዕይንት ማሳያ ስፍራ ይገኛሉ።

አባ ፍራንሲስ ለብሮንካይትስ ሕክምና ሆስፒታል ገቡ 

የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አባ ፍራንሲስ፣ ብሮንካይተስ ለተሰኘ የመተንፈሻ አካል ኢንፌክሽን ሕክምና ዛሬ አርብ ጠዋት ሆስፒታል መግባታቸውን ቫቲካን በአወጣው መ
የአሜሪካ ድምፅ

አባ ፍራንሲስ ለብሮንካይትስ ሕክምና ሆስፒታል ገቡ 

የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አባ ፍራንሲስ፣ ብሮንካይተስ ለተሰኘ የመተንፈሻ አካል ኢንፌክሽን ሕክምና ዛሬ አርብ ጠዋት ሆስፒታል መግባታቸውን ቫቲካን በአወጣው መግለጫ አስታውቋል። «አባ ፍራንሲስ ዛሬ ጠዋት የተለመደውን የቤተክርስቲያን ሥርዓታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ አስፈላጊ ለሆኑ ምርመራዎች እና የብሮንካይትስ ሕክምና ሆስፒታል ገብተዋል» ሲል በመግለጫው የገለጸው ቫቲካን፣ አሁንም በሆስፒታል እንደሚገኙ አመልክቷል። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ አባ ፍራንሲስ ለምዕመናኑ ጠንካራ የጉንፋን በሽታ እንደያዛቸው ተናግረው የነበረ ቢሆንም፣ ቫቲካን ሕመማቸው በቫይረስ ወይም በባክቴርያ አማካኝነት የሚከሰት የሳምባ በሽታ ወይም ብሮንካይትስ መሆኑን አስታውቋል። አባ ፍራንሲስ ዛሬ ጠዋት ሆስፒታል እስከሚከቡ ድረስ፣ ቫቲካን በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ሆነው የዕለት ተዕለት ሥራቸውን ሲያከናውኑ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ጠዋት ከስሎቫኪያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ፊኮው ጋራ ተገናኝተዋል። የ88 ዕድሜ ያላቸው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ፍራንሲስ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በኢንፍሉዌንዛ እና ተያያዥ የጤና ችግሮች ሲሰቃዩ መቆየታቸው ይታወሳል።

የኮንጎ ጦርነት 350 ሺሕ ሰዎችን ካለመጠለያ አስቀርቷል - ተመድ

በኮንጎ የሚካሄደው ጦርነት 350 ሺህ የሚሆኑ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሰዎችን ካለመጠለያ ማስቀረቱትን ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በምስራቃ
የአሜሪካ ድምፅ

የኮንጎ ጦርነት 350 ሺሕ ሰዎችን ካለመጠለያ አስቀርቷል - ተመድ

በኮንጎ የሚካሄደው ጦርነት 350 ሺህ የሚሆኑ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሰዎችን ካለመጠለያ ማስቀረቱትን ያስታወቀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በምስራቃዊ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ያለው ኹኔታ በፍጥነት እያሽቆለቆለ ነው ብሏል። ባለፈው ሳምንት የኮንጎን ትልቁን ምስራቃዊ ከተማ፣ ጎማን የተቆጣጠረው እና በሩዋንዳ የሚደገፈው የኤም 23 ታጣቂ ቡድን ወደ ደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍል እየገፋ ሲሆን፣ ይህም በሺሕች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በሚገኙበት ደቡባዊ ክፍል ሰፊ ሰብአዊ ቀውስ ሊፈጥር ይችላል ሲሉ የአካባቢው ባለሥልጣናት አስጠንቅቀዋል። የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (ዩኤን ኤች ሲ አር) ቃል አቀባይ ኢዩጂን ቢዩን በጄኔቫ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉት 350 ሺሕ ሰዎች በጊዜያውነት ተጠልለውባቸው የነበሩት ካምፖች በመውደማቸው ምንም ዐይነት መጠለያ እንደሌላቸው ገልጸዋል። በጎማ የሚገኙ 70 ከመቶ መጠለያ ጣቢያዎች ሙሉ ለሙሉ መውደማቸውን እና ሚኖቫ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች መጠለያዎች ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸውም አስረድተዋል። በኮንጎ ወንጀል እና የበሽታ አደጋ መጨመሩንም ያመለከተው ኮሚሽኑ፣ ሌሎች ተቋማትም በግጭቱ ምክንያት ርዳታ ለማቅረብ መቸገራቸውን አብራርቷል። ሩዋናዳ አማፂያኑን የኤም 23 ቡድን በወታደሮቿ እና በጦር መሳሪያ ድጋፍ ትሰጣለች በሚል ከኮንጎ እና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ክስ የሚቀርብባት ሲኾን፣ ኪጋሊ በበኩሏ ክሱን አትቀበልም። አሁን እንደአዲስ በተቀሰቀሰው ጦርነት ቢያንስ 3ሺሕ ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፣ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። 

«ከግራሚ መልስ ለአዲስ አልበም እየተዘጋጀሁ ነው» - ዋይና

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ቢል ክሊንተን የንግግር ጸሐፊ የነበረችው የአር ኤንድ ቢ እና ሶል ሙዚቃ አቀንቃኝ ዋይና አራተኛ አልበሟን ለሕዝብ ለማድረስ በዝ�
የአሜሪካ ድምፅ

«ከግራሚ መልስ ለአዲስ አልበም እየተዘጋጀሁ ነው» - ዋይና

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ቢል ክሊንተን የንግግር ጸሐፊ የነበረችው የአር ኤንድ ቢ እና ሶል ሙዚቃ አቀንቃኝ ዋይና አራተኛ አልበሟን ለሕዝብ ለማድረስ በዝግጅት ላይ ትገኛለች። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2009 ዓ.ም በሙዚቃ ዘርፍ የተሻለ እመርታን ላሳዩ የጥበብ ሰዎች በየዓመቱ የሚሰጠው ግራሚ ሽልማት እጩ የነበረችው ዋይና፣ ግራሚ በማኅበረሰብ ለውጥ ዙሪያ ለሚያቀነቅኑ ሰዎች እውቅና እንዲሰጥ አዲስ የሽልማት ዘርፍ እንዲካተትም አድርጋለች። ዋይና ባለፈው ሳምንት በሎስ አንጀለስ ከተካሄደው ግራሚ ሽልማት መልስ በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ተገኝታ ስለራሷ እና ስለሥራዋ አጋርታናለች።   (ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።)

የፕሬዝዳንት ትራምፕ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ርምጃዎች እና ሉላዊ ተጽእኗቸው 

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዩናይትድ ስቴት ከዓለም አቀፉ ጤና ድርጅት አባልነት እንድትወጣ የሚያዝዘውን ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዝን ጨምሮ የው�
የአሜሪካ ድምፅ

የፕሬዝዳንት ትራምፕ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ርምጃዎች እና ሉላዊ ተጽእኗቸው 

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዩናይትድ ስቴት ከዓለም አቀፉ ጤና ድርጅት አባልነት እንድትወጣ የሚያዝዘውን ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዝን ጨምሮ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲያቸው አካል የኾኑ ልዩ ልዩ ርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩብዮም፣ ከዚኽ በኋላ አሜሪካ፣ በዓለም አቀፍ ሥርዓቱ ብሔራዊ ጥቅሟን ማዕከል አድርጋ እንደምትንቀሳቀስ፣ ሹመታቸውን ለማስጸደቅ በሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ተገኝተው ማብራርያ በሰጡበት ወቅት ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ እየተከተሉ ያሉትን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ምንነትና በዓለም አቀፉ ሥርዓት ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ በተመለከተ፣ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲቲዩት የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መሪ ተመራማሪ የኾኑትን ዶክተር ዳር እስከዳር ታየን አነጋግረናል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።   

የዩኤስኤአይዲ መታገድ የማያዳግም ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል ዲሞክራት ሕግ አውጭዎችን አሳስቧቸዋል

  የትረምፕ አስተዳደር የውጭ ርዳታን ማቆሙ፣ የአሜሪካን ደኅንነት እና በውጭ ያላትን ስፍራ በዘላቂነት ሊጎዳው ይችላል" ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ዲሞክራት ሕ�
የአሜሪካ ድምፅ

የዩኤስኤአይዲ መታገድ የማያዳግም ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል ዲሞክራት ሕግ አውጭዎችን አሳስቧቸዋል

  የትረምፕ አስተዳደር የውጭ ርዳታን ማቆሙ፣ የአሜሪካን ደኅንነት እና በውጭ ያላትን ስፍራ በዘላቂነት ሊጎዳው ይችላል" ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ዲሞክራት ሕግ አውጭዎች፣ትላንት ረቡዕ ተናገሩ። ሪፐብሊካኖች በበኩላቸው፣ “የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት ወይም በምኅጻሩ የዩኤስኤአይዲ መገምገም ብክነት እና ማጭበርበርን ለመዋጋት አስፈላጊ ነው” በማለት ይቃወማሉ። የቪኦኤ የምክር ቤት ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ፕሬዝደንት ትረምፕ የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ጀምረዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሦስት ዓመት የተጠጋውን የዩክሬን ጦርነት ለማስቆም የታለመውን የዲፕሎማሲ ዘመቻቸውን ትላንት ረቡዕ ከፍተዋል፡
የአሜሪካ ድምፅ

ፕሬዝደንት ትረምፕ የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ጀምረዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሦስት ዓመት የተጠጋውን የዩክሬን ጦርነት ለማስቆም የታለመውን የዲፕሎማሲ ዘመቻቸውን ትላንት ረቡዕ ከፍተዋል፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን ለምታደርግላት ድጋፍ በምላሹ የሚጠብቁባት የሚመስሉትን ሁኔታዎችም ዘርዝረዋል፡፡ ትረምፕ በኋይት ሃውስ ኦቫል ኦፊስ ጽሕፈት ቤታቸው  እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር በ2022 ሩስያ በከፈተችው ወረራ የተቀሰቀሰውን የዩክሬን ጦርነት በሚመለከት ጋዜጠኞች ላቀረቡላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ «ለምንሰጠው ገንዘብ በምላሹ ጸጥታ እንዲኖር እንፈልጋለን» ብለዋል፡፡ የቀድሞውን ፕሬዝደንት ጆ ባይደን  ለኪቭ የሚሰጡትን ድጋፍ በሚመለከት « ገንዘባችንን ስንሰጥ በምላሹ በብድር መልክ አለያም  በጸጥታ ወይም ደግሞ በነዳጃቸው ወይም በጋዛቸውም ቢሆን አንድ ነገር መጠየቅ አለብን ብያቸው ነበር» ብለዋል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ከ2022 ጀምሮ ለዩክሬን ወደ183 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወታደራዊ እና ወታደራዊ ያልሆነ ርዳታ መፍቀዱን ትላንት ለምክር ቤቱ የቀረበው የቁጥጥር ሪፖርት አመልክቷል፡፡ ከተፈቀደው ርዳታ እስካሁን ለዩክሬን ያልተላከው 40 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ ቀደም ሲልም ማክሰኞ ምሽት ፕሬዝደንት ትረምፕ ከሩስያ እስር ቤት የተለቀቁትን አሜሪካዊ መምህር ማርክ ፎግል በኋይት ሀውስ ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ከዚያም  በማስከተል ትላንት ዕኩለ ቀን ላይ  ከሩስያ ፕሬዝደንት ቭላዲሚር ፑቲን ጋራ በስልክ መነጋገራቸውን እና  ጦርነቱን ለማስቆም በአስቸኳይ ከዩክሬን ፕሬዝደንት ዜሌንስኪ ጋራ ድርድር ለመጀመር መስማማታቸውን  አስታውቀዋል፡፡  ቀጥለውም  ምክትል ፕሬዝደንታቸውን ጄ ዲ ቫንስን እና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮን ከዜሌንስኪ ጋራ እንዲነጋገሩ ወደሚዩኒክ ልከዋቸዋል፡፡

ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን ተኩስ አቁም ስምምነት እንደሚያከብር ቃል ገባ

አክራሪው  ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ውል እንደሚያከብር ዛሬ ሐሙስ ቃል ገብቷል፡፡ ይህ የሆነው ተኩስ አቁሙን ጥሷል በማለት አንዱ ሌላኛ
የአሜሪካ ድምፅ

ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን ተኩስ አቁም ስምምነት እንደሚያከብር ቃል ገባ

አክራሪው  ሃማስ ከእስራኤል ጋራ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ውል እንደሚያከብር ዛሬ ሐሙስ ቃል ገብቷል፡፡ ይህ የሆነው ተኩስ አቁሙን ጥሷል በማለት አንዱ ሌላኛውን ወገን እየወነጀሉ ባሉበት እና ጦርነቱ ሊያገረሽ ይችላል የሚል ስጋት በሚሰማበት በዚህ ወቅት ነው፡፡ የሃማስ ቃል አቀባይ አብደል ላቲፍ አል ካኑዋ  “የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲፈርስ አንፈልግም፡፡ ስለዚህም አፈጻጸሙ በጥንቃቄ  ሥራ  ላይ እንዲውል ብርቱ ፍላጎት አለን” ያሉ ሲሆን «ወራሪዋ እስራኤልም ይሄን እንድታረጋግጥ» ብለዋል፡፡   በተጨማሪም ካኑዋ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ እና ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሚሰነዘር “የማስፈራራት እና የዛቻ ቋንቋ” የተኩስ አቁም ስምምነቱን አፈጻጸም አያግዝም ብለዋል፡፡ ሃማስ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ እስራኤል በጋዛ የአየር ድብደባ በመፈጸም  እና ርዳታ እንዳይገባ በመገደብ ስምምነቱን ጥሳለች ሲል የከሰሰ ሲሆን፤ ቡድኑ የሚለቀቁት ታጋቾች ለሌላ ጊዜ እንደሚያስተላልፍም ተናግሯል። ትላንት ረቡዕ እስራኤል ወታደራዊ ተጠባባቂዎቿን ከጠራች በኋላ፤ የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የትረምፕን ማስጠንቀቂያ ደግመዋል። ካትዝ “ሃማስ ታጋቾቹን መልቀቅ ካቆመ የተኩስ አቁሙ አይኖርም፤ ጦርነት ይሆናል ማለት ነው።” ያሉ ሲሆን ጦርነቱ የበለጠ ጠንካራ እንደሚሆን እና “ትራምፕ ለጋዛ ያላቸውን ራዕይ እውን ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል” በማለት አክለዋል። የተኩስ አቁም ስምምነቱ ባለፈው ወር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፤ በዩናይትድ ስቴትስ በአሸባሪነት የተፈረጀው ሃማስ 21 ታጋቾችን ሲለቅ  በአንጻሩ እስራኤል ከ730 በላይ እስረኞችን መልቀቋ ይታወሳል። የፊታችን ቅዳሜ በሚካሄደው የታጋቾች ልውውጥ በእስራኤል  በመቶዎች በሚቆጠሩ የፍልስጤም እስረኞች ለውጥ ተጨማሪ ሶስት እስራኤላውያን እንዲፈቱ ተጠይቋል። የጋዛ ጦርነት የተቀሰቀሰው በጎርጎሮሳውያኑ ጥቅምት 2023 ሃማስ በእስራኤል ላይ ባደረሰው የሽብር ጥቃት 1200 ሰዎችን ገድሎ፤ 250 ሰዎችን ማገቱን ተከትሎ ነው ። እስራኤል በፈጸመችው የአጸፋ ጥቃት ከ48 ሺህ 200 በላይ ፍልስጤማውያንን የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሴቶች እና ህጻናት መሆናቸውን የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል፡፡  እስራኤል በበኩሏ ከተገደሉት  ወስጥ 17 ሺህ የሚሆኑት ታጣቂዎች ናቸው ብላለች፡፡  

ህወሓት ከተፈናቃዮች «በግዳጅ የገንዘብ መዋጮ በመሰብሰብ» አቤቱታ ቀረበበት

- «ከተፈናቃዮች በፈቃዳቸው የሚያዋጡ እንጂ በዕቅድ የሚሰበሰብ የፓርቲ ገንዘብ የለም፤» /ህወሓት/
የአሜሪካ ድምፅ

ህወሓት ከተፈናቃዮች «በግዳጅ የገንዘብ መዋጮ በመሰብሰብ» አቤቱታ ቀረበበት

- «ከተፈናቃዮች በፈቃዳቸው የሚያዋጡ እንጂ በዕቅድ የሚሰበሰብ የፓርቲ ገንዘብ የለም፤» /ህወሓት/

በትራምፕ የስደተኞች ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዝ ሊታወቁ የሚገባቸው ጉዳዮች

ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ኋይት ሃውስ በተመለሱበት የሥልጣን ዘመናቸው መጀመሪያ ቀን ከፈረሟቸው ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዞች መካከል ስደተኞችን �
የአሜሪካ ድምፅ

በትራምፕ የስደተኞች ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዝ ሊታወቁ የሚገባቸው ጉዳዮች

ዶናልድ ትራምፕ ዳግም ወደ ኋይት ሃውስ በተመለሱበት የሥልጣን ዘመናቸው መጀመሪያ ቀን ከፈረሟቸው ፕሬዝዳንታዊ የሥራ ማስፈጸሚያ ትእዛዞች መካከል ስደተኞችን የተመለከተው አንዱ ነው፡፡ ትእዛዙን ተከትሎ፣ በአሜሪካ በሕገ ወጥ መንገድ የሚኖሩና በወንጀል አድራጎት ውስጥ የተሳተፉትን ወደ አገራቸው የመመለስ ሥራ ተጀምሯል፡፡ ለመኾኑ፣ ይኸው ፕሬዘዳንታዊ ትእዛዝ በውስጡ ያካተታቸው ጉዳዮች ምንድን ናቸው? ከዚኹ ጋራ በተያያዘስ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ሊያውቋቸው የሚገቡ ጉዳዮች ምንድን ናቸው?አስማማው አየነው፣ በካሊፎርኒያ ሎስ ኤንጀለስ አካባቢ የኢምግሬሽን ጉዳዮች ጠበቃ ከኾኑት ወ/ሮ ሙሉ እመቤት ዓለማየሁ ያደረገው ቆይታ ምላሹን ይዟል።  ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 

የበረታው የጋዜጠኝነት ፈተና በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ኹኔታ፣ ጋዜጠኞች፥ በነጻነት ዘገባዎችን እንዳይሠሩ አዳጋች እየኾነ መምጣቱን፣ በልዩ ልዩ ብዙኀን መገናኛዎች ላይ የሚሠሩ ባለሞያዎ�
የአሜሪካ ድምፅ

የበረታው የጋዜጠኝነት ፈተና በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ኹኔታ፣ ጋዜጠኞች፥ በነጻነት ዘገባዎችን እንዳይሠሩ አዳጋች እየኾነ መምጣቱን፣ በልዩ ልዩ ብዙኀን መገናኛዎች ላይ የሚሠሩ ባለሞያዎች እና የሞያው ማኅበራት ይናገራሉ። እስር፣ የመረጃ ዕጦት እና አስቸጋሪ የኢኮኖሚ ኹኔታም ከሚገጠሟቸው ፈተናዎች መካከል መኾናቸውንም ገልጸዋል።  አስተያየት ሰጪዎቹ፣ መንግሥት ብዙኀን መገናኛን በተመለከተ የወጡትን ሕጎች ተግባራዊ እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ በዚኽ ጉዳይ ላይ፣ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን ሓላፊዎች ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።   

የ‍ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች እና ተወካዮች በመቐለ

የዩናይትድ ስቴትስ፣ የብሪታንያ፣ የጀርመን፣ የጣልያን፣ የፈረንሳይ እና የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደሮች እና ተወካዮች ከትግራይ ክልል ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬ
የአሜሪካ ድምፅ

የ‍ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች እና ተወካዮች በመቐለ

የዩናይትድ ስቴትስ፣ የብሪታንያ፣ የጀርመን፣ የጣልያን፣ የፈረንሳይ እና የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደሮች እና ተወካዮች ከትግራይ ክልል ጊዝያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ እና ከህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ጋራ ተወያዩ። በኢትዮጵያ የዩናትድ ስቴትስ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ፣ ማክሰኞ የካቲት 4 ቀን 2017 ዓ.ም የዩናይትድ ስቴትስ፣ የታላቋ ብሪታንያ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ፈረንሳይ እና አውሮፓ ኅብረት አምባሳደሮች እና ተወካዮች በፕሪቶሪያ የተፈረመው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት አስመልከቶ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ እና ከህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ጋራ ተገናኝተው እንደተወያዩ አስታውቋል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በወ‍ይይቱ ወቅት «የፕሪቶርያው ስምምነት በምልዓት ባለመተግበሩ ተፈናቃዮችን ለመመለስ አልተቻለም፣ የትግራይን ችግርም ለመፍታትም አልተቻለም» ሲሉ ለልዑካኑ ተናግረዋል። “በፕሪቶሪያ የተፈረመው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት ትግበራ ላይ ያሉት ለውጦች እና በትግበራው የሚያጋጥሙ እንቅፋቶችን አስመልክቶ  ከአሁን በፊት ያካሄደነው ውይይት ተከታይ ነው። በዚህ ውይይትም የሚያጋጥሙን ችግሮች መፍትሄ ለማስገኘት ያግዛል። የስምምነቱ አንኳር የሆነው ተፈናቃዮች ወደ ቀየ መመለስ  አለመፈፀም አሁን የገጠመን ችግር ነው። በትግራይ በአሁኑ ግዜ ያለው ፖለቲካዊ ቀውስ መነሻውም ይህ አለመፈፀሙ ነው።” ብለዋል አቶ ጌታቸው። ልዑካኑን የመሩት በኢትዮጵያ የብሪታኒያ  አምባሳደር  ዳረን ዊልች በበኩላቸው፣ «የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች በብዛት ሆነው ወደ መቐለ የተጓዙት የፕሪቶሪያው ሰምምነት በምልዓት እንዲተገበር ባላቸው ፍላጎት ነው» በማለት አስረድተዋል። «መምጣታችን ግጭትን በዘላቂነት ለማቆም የተደረሰው ስምምነት በተሻለ መልኩ እንዲተገበር ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ እንደሚፈልግ ማሳያ ነው። ስምምነቱ እንደግፋለን። የስምምነቱ ትግበራ ብዙዎች እንደሚሹት በፍጥነት እየተተገበረ እንዳልሆነ እንረዳለን።  ይህ ውይይታችን ስለሁኔታው በተሻለ ለመረዳት ያግዘናል፣ እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ስምምነቱን ለመፈፀም የሚጠበቅበትን  እገዛም እንድንመለከት ያግዛል” ብለዋል አምባሳደሩ። ልዑካኑ ከህወሓት  ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል ጋራም እንደተወያዩ ፓርቲው በፌስቡክ ገፁ አስታውቋል። ዶክተር ደብረፅዮን በውይይቱ የፕሪቶርያ ስምምነት በምልዓት ባለመተግበሩ የክልሉ ህዝብ ስቃይ፣ መከራ እና እንግልት ቀጥሏል። ተፈናቃዮች በመጠለያ ካምፕ እየተንገላቱ ይገኛሉ» በማለት ለልዑካኑ ገልፀውላቸዋል። የስምምነቱ መተግበር ለዘላቂ ሰላም ትልቅ ሚና እንዳለውም አስረድተዋል። የትግራይ የወሰን አስተዳደር ወደ ቅደመ ጦርነት እንዲመለስ፣ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ እና የክልሉ የመልሶ ግንባታ ሥራ እንዲጀመር ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና እንዲያሳድር ጠይቀዋል። ልዑካኑ በመቐለ ሰብዓ ካሬ ተብሎ የሚያወቀውን የተፈናቃኖች ካምፕ ጎብኝተዋል።    

ሲሸልስ በዓመቱ ከአፍሪካ አነስተኛው ሙስና የተመዘገበባት ሀገር ሆነች

ዓለም አቀፉ የጸረ ሙስና ድርጅት ‘ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል’ በያዝነው ሳምንት ይፋ ባደረገው የሀገራት የሙስና ይዞታ ዓመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው፡ 72 �
የአሜሪካ ድምፅ

ሲሸልስ በዓመቱ ከአፍሪካ አነስተኛው ሙስና የተመዘገበባት ሀገር ሆነች

ዓለም አቀፉ የጸረ ሙስና ድርጅት ‘ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል’ በያዝነው ሳምንት ይፋ ባደረገው የሀገራት የሙስና ይዞታ ዓመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው፡ 72 ነጥብ ያስመዘገበችው ሲሼልስ ከአፍሪካ ሀገራት በሙሉ በሙስና ዝቅተኝነት ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን፤ ካቦ ቨርዲ በ62፣ ቦትስዋና በ57፣ ሩዋንዳ ደግሞ በ57 ነጥቦች በደረጃው ሰንጠረዥ ተከታታዩን እርከኖች ተቆናጠዋል። በሪፖርቱ መሰረት ክፉኛ በሙስና የተዘፈቁት የአፍሪካ ሀገራት ተርታ 8 ነጥብ ያስመዘገበችው ሶማሊያ 9 ነጥብ ያስመዘገበችው ደቡብ ሱዳን፡ እንዲሁም በተመሳሳይ 13 ነጥቦች ያስመዘገቡት ሊቢያ፣ ኤርትራ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ ይገኙባቸዋል። ከሁለት ዓመት በፊት እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2023 ከወጣው መረጃ ጋራ ሲነጻጸር ኤርትራ በ8 ነጥብ ዝቅ በማለት ከቀድሞውም በከፋ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በ99ኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ ዘንድሮም እንዳለፈው ዓመት 37 ነጥብ ነው ያስመዘገበችው። በዓለም አቀፍ ደረጃ ዴንማርክ በ90 ነጥብ በሙስና ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ ፊንላንድ በ88 ነጥብ፣ ሲንጋፖር ደግሞ በ84 በሁለተኛ እና በሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ዩናይትድ ስቴትስ በአንጻሩ በ65 ነጥብ 28 ላይ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጣሉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ ትላንት ሰኞ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጥለዋል። በቀረጡ በጣም የሚጎዱት ለአሜሪካ ዋናዎ�
የአሜሪካ ድምፅ

ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጣሉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ ትላንት ሰኞ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጥለዋል። በቀረጡ በጣም የሚጎዱት ለአሜሪካ ዋናዎቹ የብረታ ብረት እና አሉሚነም አቅራቢዎች የሆኑት ካናዳ እና ሜክሲኮ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተመልክቷል። ትረምፕ ንግድን በሚመለከት እየወሰዱ ያሉት ርምጃ ከዋናዋ የዩናይትድ ስቴትስ ተቀናቃኝ ከቻይና በኩል የበረታ ነቀፌታ አስከትሏል። የአሜሪካ ድምጽ የኋይት ሐውስ ዘጋቢ አኒታ ፓወል ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ወጣቶችና የአካባቢያቸው ሰላም

ጦርነት፣ ግጭት አለመረጋጋት እና ሰላም ማጣት በወጣቶች ህይወት ላይ ምን ዐይነት ተፅዕኖ እንደፈጠረ የወጣቶችን አስተያየት ጠይቀናል። ምላሻቸውን ከተያያዘው �
የአሜሪካ ድምፅ

ወጣቶችና የአካባቢያቸው ሰላም

ጦርነት፣ ግጭት አለመረጋጋት እና ሰላም ማጣት በወጣቶች ህይወት ላይ ምን ዐይነት ተፅዕኖ እንደፈጠረ የወጣቶችን አስተያየት ጠይቀናል። ምላሻቸውን ከተያያዘው ፋይል ማግኘት ትችላላችኹ። በሌላ በኩል እናንተም አስተያየታችኹን አጋሩን፣ በአካባቢያችሁ ያለው የሰላም ሁኔታ በኑሮአችኹ ላይ ያስከተለው ጫና ምን ይመስላል? የማኅበረሰቡን ችግር ለምቅረፍም ኾነ በሰላም ዙሪያ ለማገዝ የወጣቶች ተሳትፎ ምን ሊኾን ይገባል ትላላችኹ? አስተያየታችኹን አጋሩን።

የወጣቶች የሰላምና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄ   

መንግሥት፣ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚታዩትን አለመረጋጋቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ወጣቶች ጥሪ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ በ�
የአሜሪካ ድምፅ

የወጣቶች የሰላምና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄ   

መንግሥት፣ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚታዩትን አለመረጋጋቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ወጣቶች ጥሪ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ በተካሔደ ሀገር አቀፍ የወጣቶች መድረክ ላይ የተሳተፉ ወጣቶች፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት አስተያየት፣ በሀገሪቱ የሚታዩት ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ወጣቱ በነፃነት እንዳይሠራ እያደረጉት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ወጣቶቹ፣ መንግሥት ለእነዚህ ችግሮች መፍትሔ እንዲሰጥ እና የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተቃሚነት እንዲያረጋግጥም ጠይቀዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

Get more results via ClueGoal