02 March 2025   20:14:00
Ethiopia



የፈረንሳይ ኃይሎች ከቻድ ሙሉ ለሙሉ ለቀው ወጡ

የፈረንሳይ ኃይሎች ከምዕራብ አፍሪካዊቷ ቻድ ሙሉ ለሙሉ ለቀው ወጥተው መጨረሳቸውን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ማሃማት ኢድርስ በደስታ ተቀብለውታል። ይህም ፈረንሳ�

የአጥንት ብግነት አርተራይተስ

አርተራይተስ ወይም የአጥንት ብግነት መገጣጠሚያ ላይ የሚከሰት እብጠት፣ የአጥንት ድርቅ ብሎ የመሰማት ስሜት፣ የእንቅስቃሴ ማዳገት ምልክቶቹ ሲሆኑ፤ በአለም �
የአሜሪካ ድምፅ

የአጥንት ብግነት አርተራይተስ

አርተራይተስ ወይም የአጥንት ብግነት መገጣጠሚያ ላይ የሚከሰት እብጠት፣ የአጥንት ድርቅ ብሎ የመሰማት ስሜት፣ የእንቅስቃሴ ማዳገት ምልክቶቹ ሲሆኑ፤ በአለም ላይ ብዙዎችን ለህመም ብሎም ለአካል ጉዳት የዳረገ በሽታ ነው። ከመቶ በላይ የአጥንት ብግነት ዓይነቶች ሲኖሩ ከሁሉም ልቆ የሚታወቀው በእንግሊዘኛው ኦስቴዮ አርተራይተስ ተብሎ የሚጠራው ዓይነት ነው።

ሩቢዮ ለእስራኤል የሚደረግ የአራት ቢሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ እንዲፋጠን አደረጉ

የዩናይትድ ስቴትስ  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ትላንት ቅዳሜ  ለእስራኤል አራት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ  የተፋጠነ ወታደራዊ እርዳታ ለማድረስ  መፈረማ�
የአሜሪካ ድምፅ

ሩቢዮ ለእስራኤል የሚደረግ የአራት ቢሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ እንዲፋጠን አደረጉ

የዩናይትድ ስቴትስ  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ትላንት ቅዳሜ  ለእስራኤል አራት ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ  የተፋጠነ ወታደራዊ እርዳታ ለማድረስ  መፈረማቸውን ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ጥር ወር ላይ ሥራውን የጀመረው የትራምፕ አስተዳደር እስካሁን ድረስ 12 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ወታደራዊ ሽያጭ፤ ለእስራኤል መፍቀዱን ሩቢዮ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።   መግለጫው አያይዞም “አሜሪካ ለእስራኤል ደህንነት  ያላትን የረዥም ጊዜ ቃልኪዳን ለሟሟላት፤ ስጋቶችን ለመከላከል የሚያስችል ዘዴን ጨምሮ  ሁሉንም ያሏትን አማራጮች መጠቀሟን ይቀጥላል” ብሏል። ሩቢዮ ለእስራኤል ወታደራዊ ዕርዳታ ለማድረስ የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣናቸውን መጠቀማቸውን ገልጸዋል። በአሁን ሰዓት እስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪ ተብሎ የተመዘገበው ሀማስ ድርጅት ጋር በቋፍ ላይ ያለ የተኩስ አቁም ውስጥ ይገኛሉ።

የዩክሬኑ ዜለንስኪ በእንግሊዝ  ጠቅላይ ሚንስትር ስታርመር ሞቅ ያለ አቀባበል ተደረገላቸው

የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ጋራ የተጋጋለ ኃይለ ቃል ከተለዋወጡ ከአንድ ቀን በኋላ ለንደን ሲደር�
የአሜሪካ ድምፅ

የዩክሬኑ ዜለንስኪ በእንግሊዝ  ጠቅላይ ሚንስትር ስታርመር ሞቅ ያለ አቀባበል ተደረገላቸው

የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ጋራ የተጋጋለ ኃይለ ቃል ከተለዋወጡ ከአንድ ቀን በኋላ ለንደን ሲደርሱ፣ በእንግሊዝ ጠቅላይ ምኒስትር ኪር ስታርመር ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።  ሁለቱ ሀገራት የዩክሬን የመከላከያ አቅምን ለመደገፍ የ2.84 ቢሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ይፋ ያደረጉ ሲኾን፤ ብድሩ እንዳይንቀሳቀሱ ከታገዱ የሩሲያ ንብረቶች ሽያጭ ትርፍ ላይ የሚከፈል ነው። ሞስኮ ኪየቭን በወረረችበት ወቅት፣ የአውሮፓ ባለሥልጣናት፣ ከሩስያ ውጭ የሚገኙ ማንኛውንም የሩሲያ ንብረቶችን እንዳይንቀሳቀሱ በማገድ፣ ሞስኮን ለመቅጣት መወሰናቸው ይታወሳል።  ዜለንስኪ በዶውኒንግ ጎዳና ከአቻቸው ስታመር ጋራ ፎቶ ለመነሳት ለአፍታ የቆሙ ሲሆን፤ እንግሊዛውያን በጩኸት ድጋፋቸውን አሳይተዋቸዋል። ስታመርም ለዜለንስኪ “በዳውኒንግ ጎዳና ሁሌም እንቀበሎታለን” ብለዋቸዋል።  አክለውም፣  «ከቤት ውጭ በጎዳናው ላይ እንደሰሙት፣ በዩናይትድ ኪንግደም ሙሉ ድጋፍ አሎት፣ ምን ዐይነት ጊዜ ቢወስድም ሁሌም ከዩክሬን እና  ከእርሶ ጋራ እንቆማለን» ብለዋቸዋል። ሁለቱ መሪዎች 75 ደቂቃ የፈጀ ውይይት ካደረጉ በኋላ ስታመር ዜለንስኪን እስከ መኪናቸው ድረስ  ሸኝተዋቸዋል። ምንም እንኳን የትረምፕ እና ዜለንስኪ ውይይት ባለመግባባት ቢጠናቀቅም፣ የትረምፕ ድጋፍ ለዩክሬን በእጅጉ አስፈላጊ መኾኑን ዜለንስኪ ትላንት ቅዳሜ  አጽንኦት ሰጥተውበታል። 

በዩጋንዳ የአራት ዓመት ህጻን በኢቦላ መሞቱን የአለም የጤና ድርጅት አስታወቀ

በዩጋንዳ ሁለተኛው የኢቦላ ታማሚ የአራት ዓመት ህፃን ህይወቱ ማለፉን የአለም ጤና ድርጅት፤ የሀገሪቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ገልጿል። ሁኔታው በዩጋ�
የአሜሪካ ድምፅ

በዩጋንዳ የአራት ዓመት ህጻን በኢቦላ መሞቱን የአለም የጤና ድርጅት አስታወቀ

በዩጋንዳ ሁለተኛው የኢቦላ ታማሚ የአራት ዓመት ህፃን ህይወቱ ማለፉን የአለም ጤና ድርጅት፤ የሀገሪቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ገልጿል። ሁኔታው በዩጋንዳ  የተረጋገጠ የኢቦላ ሟቾችን አሃዝ አስር አድርሶታል። በምሥራቅ አፍሪካዊቷ  ሀገር መዲና ካምፓላ ሙላጎ ብሔራዊ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የሚያገለግል አንድ ወንድ ነርስ ከሞተ በኋላ፤ ሀገሪቱ ባለፈው ጥር ወር በአደገኛ ሁኔታ  ተላላፊ፣ ገዳይ እና ብዙ የደም መፍሰስ የሚያስከትል በሽታ መከሰቱን አስታውቃለች። የዓለም ጤና ድርጅት የዩጋንዳ ጽህፈት ቤት ትላንት ቅዳሜ በኤክስ ማኅበራዊ ድረገጽ ላይ ዘግይቶ እንዳስታወቀው፤ ሚኒስትሩ ባለፈው ማክሰኞ “በሙላጎ ሆስፒታል ውስጥ የአራት ዓመት ተኩል ዓመት ሕፃን በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ አለፏል” ማለቱን ሪፖርት አድርጓል። ሙላንጎ የኢቦላ ህክምና ሪፈራሎች የሚመጡበት በሀገሪቱ ያለ ብቸኛ ብሔራዊ ሆስፒታል ነው። ሚኒስቴሩ በዚህ ዓመት በየካቲት ወር በእንክብካቤ ላይ ያሉ ስምንቱ የኢቦላ ታማሚዎች ታክመው ሲወጡ፤ በተጨማሪም 265 የሚሆኑና ከእነሱ ጋር ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦች  በካምፓላ እና በሌሎች ሁለት ከተሞች ጥብቅ ማቆያ ውስጥ መቆየታቸውን አስታውቋል። የኢቦላ ምልክቶች ትኩሳት፣ ራስ ምታት እና የጡንቻ ህመም ሲሆኑ፤ ቫይረሱ የሚተላለፈው ከተበከሉ የሰውነት ፈሳሾች እና አካላት ጋር በሚደረግ ንክኪ ነው።

እስራኤል በጋዛ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ የአሜሪካን ዕቅድ ስትደግፍ ሀማስ ተቃውሟል

የእስራኤል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፤ በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የተደረሰው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ሊያበቃ የሰዓታት ጊዜ በቀሩት ወቅት፤ የፕሬዝዳን�
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በጋዛ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ የአሜሪካን ዕቅድ ስትደግፍ ሀማስ ተቃውሟል

የእስራኤል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፤ በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የተደረሰው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ሊያበቃ የሰዓታት ጊዜ በቀሩት ወቅት፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ልዑክ የሆኑት ስቲቭ ዊትኮፍ፤ በረመዳን እና በፋሲካ የጾም ወቅት በጋዛ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ያቀረቡትን ሀሳብ ሀገራቸው መቀበሏን  እሁድ ማለዳ አስታውቋል። ዊትኮፍ ባቀረቡት ዕቅድ መሰረትም በመጀመሪያው ቀን በጋዛ በህይወትም ያሉት እና ከሞቱትም ታጋቾች ግማሾቹ እንደሚለቀቁ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት የገለጸ ሲሆን፥ ቀሪዎቹ ታጋቾችም ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኋላ እንደሚለቀቁ ገልጿል። ዊትኮፍ በቋሚ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመነጋገር ተጨማሪ ጊዜ እንደሚያስፈልግ በመረዳታቸው፤ አሁን ያለውን የተኩስ አቁም ለማራዘም ሀሳብ አቅርበዋል ሲል የኔታኒያሁ ጽህፈት ቤት አስታውቋል። በዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው የሐማስ ቡድን ቃል አቀባይ ሀዜም ቃሴም ከቅዳሜ  ዕለት ቀደም ብሎ ቡድኑ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያ ምዕራፍ መራዘሙን ውድቅ ማድረጉን ቢገልጹም የዊትኮፍ እቅድን በግልፅ አልጠቀሱም። እስራኤል በዊትኮፍ እቅድ ላይ ሀማስ ከተስማማ ወዲያውኑ ድርድር ታካሂዳለች ሲል የኔታኒያሁ ቢሮ አስታውቋል። “በስምምነቱ መሰረት እስራኤል ከ42ኛው ቀን በኋላ ድርድሩ ውጤታማ እንዳልሆነ ከተሰማት ወደ ጦርነት መመለስ ትችላለች”  በማለት የኔታኒያሁ ጽህፈት ቤት ሀማስ ስምምነቱን ጥሷል ሲል ከሷል። ሁለቱም ወገኖች አንዱ ሌላኛውን ስምምነቱን ጥሷል በሚል ሲከሱ ቆይተዋል። ስለድርድሩ የሚያውቁ ሁለት የፍልስጤም ባለሥልጣናት ለሮይተርስ እንደተናገሩት እስራኤል ወደ ሁለተኛው የስምምነት ምዕራፍ ለመግባትም ሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ ድርድር ለመጀመር ፈቃደኛ አልሆነችም ብለዋል። በምትኩ፣ እስራኤል ሳምንታቶቹን በማራዘም ለተራዘመው ለእያንዳንዱ ሳምንት በርካታ ታጋቾችን እና አካላት እንዲለቀቁላት ጠይቃለች። ቅዳሜ ዕለት የሀማስ ታጠቂ ክንፍ የእስራኤል ታጋቾች አሁንም በጋዛ በእስር ላይ እንደሚገኙ የሚያሳይ ቪዲዮ የለጠፈ ሲሆን፤  የተቀሩት ታጋቾች ሊፈቱ የሚችሉት በጎርጎርሳውያኑ ጥር 19 የተጀመረው የተኩስ አቁም ስምምነት ሲጠናቀቅ ብቻ መሆኑን አፅንዖት ሰጥቷል። የተኩስ አቁም ንግግሮች በቅርቡ በካይሮ ቢደረጉም ስምምነት ላይ ሳይደረስ ተጠናቀዋል። በተያያዘ ዜና ዛሬ እሁድ እስራኤል ሀማስ በቋፍ ላይ ያለውን የተኩስ አቁም የማይቀበል ከሆነ ወደ ጋዛ ሰርጥ የሚገቡ ምርቶችና ሸቀጦችን እንደምትገድብ እና “ተጨማሪ መዘዞች” እንደሚከተሉ አስታውቃለች። ሀማስ እስራኤል ጫፍ ላይ ያለውን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማደናቀፍ እየሞከረች ነው በማለት የከሰሰ ሲሆን፤  ዕርዳታውን ለማቆም የወሰነችው ውሳኔም “ርካሽ ዘረፋ፣ የጦር ወንጀል እና ግልጽ ጥቃት” ነው ብሏል።

የዓድዋ ድል በዓል ሰሎዳ ተራራ ላይ ተከበረ

ኢትዮጵያውያን የአገራቸውን ነጻነት ለማስከበር ለመጀመሪያ ጊዜ “ብሔራዊ ሆነው” የተነሡበትና በኅብረት ተዋግተው ያሸነፉበት፣ 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በትግ
የአሜሪካ ድምፅ

የዓድዋ ድል በዓል ሰሎዳ ተራራ ላይ ተከበረ

ኢትዮጵያውያን የአገራቸውን ነጻነት ለማስከበር ለመጀመሪያ ጊዜ “ብሔራዊ ሆነው” የተነሡበትና በኅብረት ተዋግተው ያሸነፉበት፣ 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በትግራይ ክልል በሶሎዳ ተራራ ላይ ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ተከበረ።  በበዓሉ አከባበር ላይ የተገኙት፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ምኒስትር ዴኤ'ታ እንደገና አበበ፣ የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያ እና ጭቁን ሕዝቦች ዐዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንደነበር አስታውሰዋል።    በየዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ በድምቀት የሚዘከረው የዓድዋ ድል፣ መከበር የጀመረው ጦርነቱ ከተደረገበት 1888 ዓ.ም. ከሰባት ዓመት በኋላ ነው፡፡ ዛሬ በሶሎዳ ተራራ ላይ በተከበረው በዓል ላይ፣ በጦርነቱ ጊዜ  ኢትዮጵያውያን  በሕብር አድርገውት የነበረውን ተሳትፎ የሚያስታውሱ የኪነጥበብ ሥራዎች ቀርበዋል። የትግራይ ክልል ባህልና ቱሪዘም ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አፅብሃ ገብረእግዚአብሄር፣ የዓድዋ ድል በዓል ለሰላም፣ አንድነት እና ብሩህ ተስፋ፣ በሚል መሪ ሐሳብ በመከበር ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 

ከትረምፕ እና ዜለንስኪ የተጋጋለ እሰጥ አገባ በኋላ የአውሮፓ መሪዎች ከዩክሬን ጎን ቆመዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስሊ ውይይት ወደ ተጋጋለ እሰጥ አገባ ከተቀየረ እና ትረምፕ ዜለንስኪን
የአሜሪካ ድምፅ

ከትረምፕ እና ዜለንስኪ የተጋጋለ እሰጥ አገባ በኋላ የአውሮፓ መሪዎች ከዩክሬን ጎን ቆመዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ እና የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስሊ ውይይት ወደ ተጋጋለ እሰጥ አገባ ከተቀየረ እና ትረምፕ ዜለንስኪን «አክብሮት የጎደለው» ሲሉ ከተናገሯቸው በኋላ በመላ አህጉሪቱ የሚገኙ የአውሮፓ መሪዎች ከዩክሬን ጎን ቆመዋል። የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኃላፊ ካጃ ካላስ ፣ «አኹን ነጻው ዓለም አዲስ መሪ እንደሚያስፈልገው ግልጽ ኾኗል» ብለዋል። በዚኹ በማኅበራዊ ሚዲያ ኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጹሑፍ፣ «ዩክሬን የአውሮፓ ነች፣ ከዩክሬን ጎን እንቆማለን» ብለዋል። የጀርመን ቻንስለር ኦላፍ ሾልዝ «ዩክሬን በጀርመን ላይ መተማመን ትችላለች -  በአውሮፓም ላይ እንዲኹ» በማለት  ኤክስ ላይ ሲጽፉ፣  የስፔን ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ደግሞ «ዩክሬን-  ስፔን ከጎንሽ ትቆማለች” ብለዋል።   የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ቱስክ  »ውድ ዜለንስኪ እና ውድ የዩክሬን ጓደኞቻችን ፣ ብቻህን አይደለህም« ሲሉ በኤክስ ላይ ጽፈዋል። የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን በበኩላቸው ለፖርቹጋል ጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ »አጥቂዋ ሩሲያ ነች። ተጠቂው የዩክሬን ሕዝብ ነው” ብለዋል።   የፊንላንድ፣ ኔዘርላንድስ፣ ቼክ ሪፐብሊክ እና ኖርዌይን ጨምሮ ሌሎች የአውሮፓ መሪዎችም ለዩክሬን ድጋፋቸውን ለመስጠት በማኅበራዊ ገጾቻቸው ላይ ጽፈዋል።  ኖርዌይም በማኅበራዊ ሚዲያ ለዩክሬን ድጋፏን ገልጻለች። ሆኖም ዩክሬንን የደገፉት ሁሉም የአውሮፓ መሪዎች  አይደሉም፣ ለኪቭ የሚሰጠውን ርዳታ ለረዥም ጊዜ ሲቃወሙ የቆዩት  የሃንጋሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን፣ ምንም እንኳን ሁኔታውን ለሌሎች ለመቀበል ቢከብዳቸውም ፕሬዝደንት ትረምፕ ለሰላም የቆሙ ናቸው። እናመሰግናለን ፕሬዝደንት!” ብለው ጽፈዋል።

ኬሪ ሌክ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ ልዩ አማካሪ ኾኑ

ፖለቲከኛ እና የቀድሞ ጋዜጠኛ የነበሩት ኬሪ ሌክ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ (ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም.) አማካሪ ኾነው መሾማቸውን ተቋሙ ፣ ሐሙስ የካ�
የአሜሪካ ድምፅ

ኬሪ ሌክ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ ልዩ አማካሪ ኾኑ

ፖለቲከኛ እና የቀድሞ ጋዜጠኛ የነበሩት ኬሪ ሌክ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ (ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም.) አማካሪ ኾነው መሾማቸውን ተቋሙ ፣ ሐሙስ የካቲት፣ 20 ቀን 2017 ዓ.ም አስታወቀ። ላለፉት 30 ዓመታት በጋዜጠኝነት ያገለገሉት ኬሪ ሌክ፣ በመንግሥት ለሚደገፈውና ዓለም አቀፍ ሥርጭት ላለው አሜሪካ ድምፅ በዲሬክተርነት እንዲሾሙ መታጨታቸውን፣ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም አስታውቀው ነበር። ኾኖም የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲን (ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም.) በዋና ሥራ አስፈፃሚነት እንዲመሩ በትረምፕ የተመረጡት፣ ወግ አጥባቂ ሐሳቦች አራማጅ እና ጸሐፊው ኤል ብሬንት ቦዜል ሹመት፤ የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት (ሴኔት)ማረጋገጫ በመጠባበቅ ላይ በመኾኑ የኬሪ ሌክ ሹመት አጓቶታል። ሚዲያ ኤጀንሲንው፣ የተለያዩ እህትማማች ተቋማት ኃላፊዎችን መሾም ወይም ማሰናበትን ጨምሮ ከዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋራ አብሮ የሚሠራ፣ ከሁለቱ ፓርቲዎች የተዋቀረ ቦርድ እስኪሰየም በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። የኤጀንሲው የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አማንዳ ቤኔት፣ ሥልጣናቸውን ከለቀቁ በኋላ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኾነው በማገልገል ላይ የሚገኙት ሮማን ናፖሊ፣ ሌክ በልዩ አማካሪነት መቀላቀላቸውን ለተቋሙ ሠራተኞች በላኩት ኢሜል አስታውቀዋል። “ከሁለት ዐስርት ዓመታት በላይ በታላላቅ ብዙኅን መገናኛ ውስጥ በዘጋቢነት እና ዜና አቅራቢነት ያገለገሉት ሌክ፣ በብሮድካስት ጋዜጠኝነት ውስጥ ብዙ ልምድ አላቸው” በማለት ናፖሊ አክለዋል። ናፖሊ የሌክን ስኬት በማጉላትም፣ ከዚኽ ቀደም ለኹለት የአሜሪካ ፕሬዝደንቶች ቃለ መጠየቅ ማድረጋቸውን እና በዓለም አቀፍ ዘገባዎች ምክኒያት ሁለት ጊዜ የኤሚ ሽልማት መቀበላቸውን፣ ጠቅሰዋል። «ኬሪ የትረምፕ አስተዳደር ከፍተኛ አማካሪ እንደመኾናቸው፣ የሚዲያ ኤጀንሲውን፣ የእህትማማች ተቋማቱን እና የፈንዱን ሥራ ለማቀላጠፍ፣ የሚያስፈልጉትን ፖሊሲዎች እና ስልቶች ተግባራዊ ለማድረግ ያግዛሉ»ሲሉ ናፖሊ በኢሜል መልዕክታቸው ጠቅሰዋል። የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ (ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም.)፣ ከ420 ሚሊዮን በላይ የሚኾኑ ዓለም አቀፍ አድማጮችና ተመልካቾችን ያላቸው፣ በዜና ዘገባ እና ቅድመ ምርመራ ወይም ሳንሱርን በመዋጋት ላይ ትኩረታቸውን አድርገው የሚሠሩ በርካታ ተቋማትን ይቆጣጠራል። በዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም. ሥር የሚገኙ እነዚኽ እህትማማች ድርጅቶች፣ የአሜሪካ ድምፅ፣ የኩባ ብሮድካስቲንግ ቢሮ (Cuba Broadcasting) እና ለትርፍ ያልተቋቋመው የነፃ አውሮፓ ራዲዮ ወይም ራዲዮ ሊበርቲ (Free Europe/Radio Liberty)፣ የነፃ እሥያ ራዲዮ(Radio Free Asia)፣ የመካከለኛው ምሥራቅ ብሮድካስቲንግ መረብ እና የኦፕን ቴክኖሎጂ ፈንድ እና የፍሮንት ላይን ፈንድን ናቸው። የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ኤጀንሲ (ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም.)፣ የሕዝብ ጉዳዮች ክፍል የኬሪ ሌክን ሹመት በተመለከተ ለአሜሪካ ድምፅ ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም። «ፋየርዎል» በመባል የሚታወቀው የኢዲቶሪያሉ ገለልተኝነት መጠበቂያ፣ ዩ.ኤስ.ኤ.ጂ.ኤም በሚያስተዳድራቸው ብዙኅን መገናኛ የጋዜጠኝነት ሥራ ውጤት ላይ ጣልቃ እንዳይገባ ይከለክላል። ሌክ በዓመታዊው የወግ አጥባቂ አቀንቃኞች የፖለቲካ ጉባኤ ላይ በሰጡት አስተያየት የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ሚዲያ የቀረበበትን ትችት በንግግራቸው ዳሰዋል፡፡ ሌክ ለታዳሚው እንደ ቪኦኤ ዲሬክተር የዜና ተቋሙ “ትክክለኛ እና ታማኝ ዘገባዎችን” ማዘጋጀቱ ላይ ትኩረት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። ሌክ አክለው ፣ “የፊታችን ሰኞ 83 ዓመት የሚኾነው ቪኦኤ አሜሪካን ታሪክ ለዓለም ሲያቀርብ ቆይቷል። አንዳንድ ጊዜ በዜና ሽፋኑ አስደናቂ ሲኾን በሌሎች ወቅቶች ደግሞ አሳዛኝ ነበር” ብለዋል፡፡ አያይዘውም “እኛ የምንዋጋው የመረጃ ጦርነት ነው፤ በመሆኑም ከእውነት የተሻለ መሳሪያ የለም፣ እናም ቪኦኤ ይህ መሳሪያ ሊሆን ይችላል ብዬ አምናለሁ” በማለት ተናግረዋል፡፡ የዜና ጣቢያው እንዲዘጋ ከጠየቁት መካከል የትራምፕ ልዩ አማካሪ ኢላን መስክ ይገኙበታል። ይሁን እንጂ ሌክ “የትራምፕ ቴሌቭዥን አንሆንም” በማለት የተናገሩ ሲኾን፤ “ሆኖም ግን ዲጂታል ኬብል ቴሌቭዥን እንደማንኾን ግን እርግጠኛ ነው” ብለዋል፡፡ አክለውም “ትረምፕን ምክኒያታዊ ባልኾነ መልኩ መተቸትን ከሲ.ኤን.ኤን፣ ኤም.ኤስ.ኤም.ቢ.ሲ፣ 60 ደቂቃ፣ ዘ ዋሺንግተን ፖስት እና ከኒውዮርክ ታይምስ ልታገኙ ትችላላቹ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ኬሪ ሌክ በኮቪድ 19 ወረርሽኙ ወቅት የተሳሳተ መረጃ ነው ብለው ባመኑት መረጃ ምክንያት ከአሪዞና የዜና ጣቢያ ሥራቸውን ለቀዋል። በኋላም ለአሪዞና ሀገረ ገዥነት ተወዳድረ ያልተሳካላቸው ሲኾን ሽንፈታቸውን ባለመቀበል ክስ መስርተዋል። በመቀጠልም ለግዛቱ ሴናተርነት ያደረጉት ውድድርም አልተሳካላቸውም።

የትራምፕ እና የዜለንስኪ የዋይት ሐውስ ውይይት ወደ ተጋጋለ የቃል ልውውጥ ተቀየረ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ ጋራ በዋይት ሐውስ ያደረጉት እና አሜሪካ ከዩክሬን ልዩ ማዕድናት ማግኘ�
የአሜሪካ ድምፅ

የትራምፕ እና የዜለንስኪ የዋይት ሐውስ ውይይት ወደ ተጋጋለ የቃል ልውውጥ ተቀየረ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ ጋራ በዋይት ሐውስ ያደረጉት እና አሜሪካ ከዩክሬን ልዩ ማዕድናት ማግኘት የሚያስችላት ስምምነት ላይ ለመድረስ ያለመችበት ውይይት ወደ ተጋጋለ ኃይለ ቃል ተቀይሮ፤ ትራምፕ «ስምምነት ላይ ትደርሳለህ አለዛ እኛ እንወጣለን» ሲሉ ለዜለንስኪን ነግረዋቸዋል። ስብሰባውን ተከትሎ ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክትም «ስምምነቱ ተዘርዟል» ሲሉ አስታውቀዋል። ትራምፕ በጹሑፋቸው «የአሜሪካ ተሳትፎ የሚቀጥል ከኾነ ፕሬዝደንት ዜለንስኪ ለሰላም ዝግጁ እንደማይሆን ወስኛለሁ። ምክንያቱም የኛ ተሳትፎ ለድርድር ትልቅ ጥቅም እንደሚሰጠው ያምናል» ሲሉ ገልጸዋል። «ዩናይትድ ስቴትስን እና የፕሬዝደንቱን ኦቫል ኦፊስ' አላከበረም። ለሰላም ዝግጁ ሲኾን መመለስ ይችላል» ብለዋል ፕሬዝደንቱ። “ኦቫል ኦፊስ” በተሰኘው የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት ውስጥ በርካታ አሜሪካውያን እና ዩክሬናውያን ጋዜጠኞች የተከታተሉት የተጋጋለ የቃላት ልውውጥ ወደ ኃይለ ቃል የተለወጠው ወደ 40ኛው ደቂቃ አካባቢ ዘለንስኪ ሩሲያ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2014 ዓ.ም ክሬሚያን መውረሯን ባነሱበት ወቅት ነው። የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንት ጄዲ ቫንስ ወዲያውኑ ዜለንስኪን «የፕሮፓጋንዳ» ወሬዎችን መጠቀሚያ በማድረግ ተችተዋቸዋል። ቫንስ «ኦቫል ኦፊስ ውስጥ ኾኖ በአሜሪካ ሚዲያ ፊት ይህን ዐይነት ክስ ማንሳት ንቀት ነው» ነው ሲሉ ዜለንስኪን ተናግረዋቸዋል። ቫንስ እና ትራምፕ የዩክሬኑ መሪ ዋሽንግተን ለሀገራቸው ላደረገቸው ርዳታ አመስጋኝ አለመኾናቸውን ገልፀውም ወቅሰዋቸዋል። ዜለንስኪ ምላሽ ለመስጠት ቢሞክሩም ትራምፕ «ለመደራደሪያ የሚሆን አቅም እና ሥልጣን የለህም» በማለት አቋርጠዋቸው «በሚሊየን በሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ቁማር ትጫወታለህ። ከሦስተኛ ዓለም ጦርነት ጋራ ቁማር እየተጫወትክ ነው» ብለዋቸዋል። ዜለንስኪ በታቀደው መሠረት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሳይሳተፉ ቀደም ብለው ከዋይት ሐውስ ወጥተዋል። ውይይቱ በድንገት ከተጠናቀቀ በኋላ የዩክሬኑ መሪ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለአሜሪካ ሕዝብና መንግሥት መልዕት አስፍረዋል። ኤክስ በተሰኘው የማኅበራዊ ገጽ ላይ «አመሰግናለኹ አሜሪካ» ሲሉ የጻፉት ዜለንስኪ፣ « የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት፣ የምክር ቤት አባላትንና የአሜሪካን ሕዝብ እናመሰግናለን። ዩክሬን ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላም ትፈልጋለች ፣ ያንን ለማግኘትም በሚገባ እየሠራን ነው» ብለዋል። የማዕድን ስምምነት ውይይቱ ከመጀመሩ በፊት ትራምፕ ከዜለንስኪ ጋራ ስምምነቱን ለመፈራረም መቃረባቸውን ገልጸው ነበር። ብዙም ምቾት እንዳልተሰማቸው ለሚያስታውቁት ዜለንስኪም «በጣም ፍትሃዊ የሆነ ስምምነት ነው ያለን፣ እናም ገብተን ለመቆፈር፣ ለመሥራት እና እነዛን ብርቅ የመሬት ማዕድናት ለማግኘት በጉጉት እንጠብቃለን » ብለዋቸው ነበር። ስምምነቱ ከጦርነቱ በኃላ ዩክሬንን መልሶ ለመገንባት የሚውል የጋራ ባለቤትነት እና አስተዳደር ድንጋጌዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ ዩክሬን ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የምታገኘውን 50 ከመቶ የሀገሪቱን ገቢ ለዚህ ትመድባለች። ትራምፕ የማዕድን ስምምነቱን፣ ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ የምታደርገው ጦርነት ካበቃ በኋላ በዩክሬን ውስጥ ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሰላም አስከባሪ ኃይሎች ለሚሰጡት የደህኅነት ማስተማመኛ፣ እንደ «ዋስትና» አድርገው ይገልጹታል። የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ግን ስምምነቱ እንዳልተፈረመ ገልጸዋል።

የትራምፕ እና የዜለንስኪ የዋይት ሐውስ ውይይት ወደ ኃይለ ቃል ልውውጥ ተቀየረ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ ጋራ በዋይት ሐውስ ያደረጉት እና አሜሪካ ከዩክሬን ልዩ ማዕድናት ማግኘ�
የአሜሪካ ድምፅ

የትራምፕ እና የዜለንስኪ የዋይት ሐውስ ውይይት ወደ ኃይለ ቃል ልውውጥ ተቀየረ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዜለንስኪ ጋራ በዋይት ሐውስ ያደረጉት እና አሜሪካ ከዩክሬን ልዩ ማዕድናት ማግኘት የሚያስችላት ስምምነት ላይ ለመድረስ ያለመችበት ውይይት ወደ ተጋጋለ ኃይለ ቃል ተቀይሮ፤ ትራምፕ «ስምምነት ላይ ትደርሳለህ አለዛ እኛ እንወጣለን» ሲሉ ለዜለንስኪን ነግረዋቸዋል።   ስብሰባውን ተከትሎ ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክትም «ስምምነቱ ተዘርዟል» ሲሉ አስታውቀዋል። ትራምፕ በጹሑፋቸው «የአሜሪካ ተሳትፎ የሚቀጥል ከኾነ ፕሬዝደንት ዜለንስኪ ለሰላም ዝግጁ እንደማይሆን ወስኛለሁ። ምክንያቱም የኛ ተሳትፎ ለድርድር ትልቅ ጥቅም እንደሚሰጠው ያምናል» ሲሉ ገልጸዋል። «ዩናይትድ ስቴትስን እና የፕሬዝደንቱን ኦቫል ኦፊስ' አላከበረም። ለሰላም ዝግጁ ሲኾን መመለስ ይችላል» ብለዋል ፕሬዝደንቱ። “ኦቫል ኦፊስ” በተሰኘው የፕሬዝደንቱ  ጽሕፈት ቤት  ውስጥ በርካታ አሜሪካውያን እና ዩክሬናውያን ጋዜጠኞች የተከታተሉት የተጋጋለ የቃላት ልውውጥ ወደ ኃይለ ቃል የተለወጠው ወደ 40ኛው ደቂቃ አካባቢ ዘለንስኪ ሩሲያ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2014 ዓ.ም ክሬሚያን መውረሯን ባነሱበት ወቅት ነው።   የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንት ጄዲ ቫንስ ወዲያውኑ ዜለንስኪን «የፕሮፓጋንዳ» ወሬዎችን መጠቀሚያ በማድረግ ተችተዋቸዋል። ቫንስ «ኦቫል ኦፊስ ውስጥ ኾኖ በአሜሪካ ሚዲያ ፊት ይህን ዐይነት ክስ ማንሳት ንቀት ነው» ነው ሲሉ ዜለንስኪን ተናግረዋቸዋል። ቫንስ እና ትራምፕ የዩክሬኑ መሪ ዋሽንግተን ለሀገራቸው ላደረገቸው ርዳታ አመስጋኝ አለመኾናቸውን ገልፀውም ወቅሰዋቸዋል። ዜለንስኪ ምላሽ ለመስጠት ቢሞክሩም ትራምፕ «ለመደራደሪያ የሚሆን አቅም እና ሥልጣን የለህም» በማለት አቋርጠዋቸው «በሚሊየን በሚቆጠሩ ሰዎች ህይወት ቁማር ትጫወታለህ። ከሦስተኛ ዓለም ጦርነት ጋራ ቁማር እየተጫወትክ ነው» ብለዋቸዋል። ዜለንስኪ በታቀደው መሠረት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሳይሳተፉ ቀደም ብለው ከዋይት ሐውስ ወጥተዋል። ውይይቱ በድንገት ከተጠናቀቀ በኋላ የዩክሬኑ መሪ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለአሜሪካ ሕዝብና መንግሥት መልዕት አስፍረዋል። ኤክስ በተሰኘው የማኅበራዊ ገጽ ላይ «አመሰግናለኹ አሜሪካ» ሲሉ የጻፉት ዜለንስኪ፣ « የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት፣ የምክር ቤት አባላትንና የአሜሪካን ሕዝብ እናመሰግናለን። ዩክሬን ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላም ትፈልጋለች ፣ ያንን ለማግኘትም በሚገባ እየሠራን ነው» ብለዋል።    የማዕድን ስምምነት ውይይቱ  ከመጀመሩ በፊት ትራምፕ ከዜለንስኪ ጋራ ስምምነቱን ለመፈራረም መቃረባቸውን ገልጸው ነበር። ብዙም ምቾት እንዳልተሰማቸው ለሚያስታውቁት ዜለንስኪም «በጣም ፍትሃዊ የሆነ ስምምነት ነው ያለን፣ እናም ገብተን ለመቆፈር፣ ለመሥራት እና እነዛን ብርቅ የመሬት ማዕድናት ለማግኘት በጉጉት እንጠብቃለን » ብለዋቸው ነበር። ስምምነቱ ከጦርነቱ በኃላ ዩክሬንን መልሶ ለመገንባት የሚውል የጋራ ባለቤትነት እና አስተዳደር ድንጋጌዎችን የሚያካትት ሲሆን፣ ዩክሬን ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የምታገኘውን 50 ከመቶ የሀገሪቱን ገቢ ለዚህ ትመድባለች። ትራምፕ የማዕድን ስምምነቱን፣ ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ የምታደርገው ጦርነት ካበቃ በኋላ በዩክሬን ውስጥ ለሚሰማሩ የአውሮፓ ሰላም አስከባሪ ኃይሎች ለሚሰጡት የደህኅነት ማስተማመኛ፣ እንደ «ዋስትና» አድርገው ይገልጹታል። የዋይት ሐውስ ቃል አቀባይ ግን ስምምነቱ እንዳልተፈረመ ገልጸዋል።   

በኢትዮጵያ እና በኬንያ የድንበር ላይ ግጭትን ተከትሎ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር አካባቢ በተዋሳኞቹ የዳሰነች ወረዳ እና የቱርካና ወረዳ አርብቶ ዐደሮች መካከል የተከሠተውን ግጭት ተከትሎ፣ የዳሰነች ወረዳ አ
የአሜሪካ ድምፅ

በኢትዮጵያ እና በኬንያ የድንበር ላይ ግጭትን ተከትሎ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ እና በኬንያ ድንበር አካባቢ በተዋሳኞቹ የዳሰነች ወረዳ እና የቱርካና ወረዳ አርብቶ ዐደሮች መካከል የተከሠተውን ግጭት ተከትሎ፣ የዳሰነች ወረዳ አርብቶ አደሮች ሲአስ ከሚባል መንደራቸው መፈናቀላቸውን፣ የወረዳው አስተዳደሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለአሜሪካ ደምፅ በስልክ አስታውቀዋል። በደኅንነት ሰጋት ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁን በዳሰነች ወረዳ የሲአስ ቀበሌ ነዋሪ፣ በስምንት ቀበሌዎች የሚኖሩ የዳሰነች ማኅበረሰብ ነዋሪዎች እንደተፈናቀሉና በአምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደምትገኘው ደብረሞስ ቀበሌ እንደሸሹ፣ በስልክ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። በግጭቱ የአጎታቸው እና የአክስታቸው ልጅ እንደተገደለባቸው ከዚኽ ቀደም የተናገሩት፣ አሰጪ ሎካሊባ የተባሉ ዐርብቶ አደር፣ እርሳቸውን ጨምሮ የቀበሌያቸው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን አስረድተዋል። ግጭቱ ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም. አንሥቶ፣ አንዱ ወገን የሌላውን የዓሣ ማሥገሪያ መረብ በመሰራረቅ መቀስቀሱን ያስታወሱት የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ፣ ግጭቱ ሰኞ የካቲት 17 ቀን በመባባሱ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል። የኬንያ ባለሥልጣናት «ድንበር ተሻጋሪ» ሲሉ በገለጹት ግጭት ከ20 በላይ ለሚደርሱ ኬንያውያን መጥፋታቸውን አስታውቀዋል። የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪው ከኢትዮጵያ በኩል 13 ሰዎች መሞታቸውንና ሦስት ሰዎች መጎዳታቸውን ተናግረዋል። ተጎራባች የኾኑት አርብቶ ዐደሮቹ፣ ሁለቱ አገሮች የሚዋሰኑበትን ድንበር በሚያቋርጠው ቱርካና ሐይቅ ላይ በጀልባቸው ኾነው የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን የገለጹት የዳሰነች ወረዳ የኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሓላፊ አቶ ብዙአየኹ ከበደ፣ በኬንያ በኩል ጠፍተዋል የተባሉት ሰዎች በሕይወት ስለመትረፋቸው የታወቀ ነገር እንደሌለ አመልክተዋል። በኢትዮጵያ በኩል ተገድለዋል ከተባሉት 13 አርብቶ ዐደሮች መካከልም፣ የአንድ ሰው አስከሬን ብቻ መገኘቱንና የሌሎቹን መሞት ያረጋገጡት፣ ከቤተሰቦቻቸው በተሰጣቸው መረጃ መሠረት እንደኾነ፣ ሓላፊው ተናግረዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሓላፊ አቶ ወገነ ብዙነህ፣ ከኹለቱም ወገን ዐርብቶ አደሮቹ መጥፋታቸው ከመገለፁ ውጪ አስክሬን ባለመገኘቱ በቁጥር መናገር እንደሚቸግር ተናገርዋል። ከባለሥልጣናቱ ውይይት በኋላ በተደረገ የሟቾች አስከሬን ፍለጋ፣ ሁለቱ መገኘታቸውን የገለጹት ሓላፊው፣ ከሁለቱም ማኅበረሰቦች በኩል የሰው ሕይወት መጥፋቱን አረጋግጠዋል። የኬንያ የደኅንነት ጉዳይ አዋቂ የኾኑት ሪቻርድ ቱታ፣ በናይሮቢ የአሜሪካ ድምፅ ዘይነብ ሰዒድ ጋራ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፣ በተፈጥሮ ሀብቶች አጠቃቀም የተነሣ ለሚከሠቱ ግጭቶች ከሥር መሠረታቸው የጋራ መፍትሔ መስጠት፣ እንዲሁም በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እንዲወርድ መሥራት ያስፈልጋል፤ ብለዋል። የደኅንነት ጉዳይ ባለሞያው፣ ሰሞነኛውን የድንበር ላይ ግጭት፣ «አልፎ አልፎ የሚከሠት» ሲሉ ቢገልጹትም፣ በቱርካና እና በዳሰነች ማኅበረሰቦች መካከል፣ ውሱን በኾነው የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ረገድ ያለው ፉክክር፣ ለግጭቱ እያደር ማገርሸት አደጋ እንደሚደቅን አልሸሸጉም፡፡ “አኹን ከኹሉም በላይ የሚያስፈልገው፣ ሁለቱ ተጎራባች ሀገራት የችግሩን ምንጭ ከሥር መሠረቱ መመልከት ይኖርባቸዋል፡፡ የሀብት ውሱንነት እስካለ ድረስ ግጭት ዳግመኛ አይቀሰቀስም እያልኹ አይደለም። በዋናነት ማከናወን የሚያስፈልገው፣ ክፍተቶቹ ምን እንደኾኑ መለየትና ከዚያም የግጭቱን የማገርሸት ዕድል ለመቀነስ የሚረዳ ዕቅድ መተግበር ነው፡፡” ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋራ በምትዋሰንበት ድንበር ላይ ከፍተኛ የጥበቃ ኀይል ማስፈሯን፣ አሶሺዬትድ ፕሬስ የአገሪቱን የውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኪፕቹምባ ሙርኮመን ጠቅሶ ዘግቧል። የኬንያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኪፕቹምባ ሙርኮመን፣ የጠፉትን ሰዎች ለማግኘት ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋራ በመተባበር እየሠሩ መኾኑን ገልጸዋል። በኬንያ የቱርካና አውራጃ አስተዳዳሪ ዠርሚያ ሎሞሩካይ በበኩላቸው፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ ከኢትዮጵያ የመጡ ያሏቸው ዓሣ አሥጋሪዎች በኦሞ ወንዝ ላይ ከኬንያ የቱርካና ጎሣ አባላት ጋራ እሑድ ዕለት መጋጨታቸውን አውስተው፣ 15 ጀልባዎች ጠፍተዋል፤ ብለዋል። በሁለቱ ተጎራባች ሀገራት ድንበር አካባቢ የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ፣ ኬንያ፣ ተጨማሪ የፖሊስ ተጠባባቂዎችን ቀጥራ የነበረ ሲኾን፣ የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ሙርኮመን፣ ኬንያ ወደ ውስጥ የሚገቡ ሰዎች ሁሉ የሚፈተሹበትን የድንበር ኬላ አቋቋማለች፤ ብለዋል። የዳሰነች ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ታደለ፣ ኬንያ ወታደሮቿን በተሽከርካሪዎች እና በሄሊኮፕተሮች እያጓጓዘች ወደ ድንበር ማስጠጋቷንም፣ አቶ ታደለ ገልጸዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሓላፊ አቶ ወገነ ብዙነህ፣ ከዳሰነች ወረዳ አርብቶ ዐደሮች እና በኬንያ ቱርካና ካውንቲ ባለሥልጣናት ጋራ መወያየታቸውን አስታውቀው፣ በዚኽም የችግሩን መነሻ ለይቶ ዘላቂ መፍትሔ በማፈላለግ፣ የሁለቱን አገሮች አርብቶ ዐደሮች ሰላማዊ ግንኙነት በማስቀጠልና ሰው የመግደል ወንጀል የፈጸሙ ሰዎች በሕግ በሚጠየቁበት ኹኔታ ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን ዘርዝረዋል። የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትም ያለው ኹኔታ ከባድ መኾኑን አልሸሸጉም፡፡ የኬንያ ባለሥልጣናት በድንበሩ ላይ የጸጥታ ጥበቃቸውን አጠናክረዋል፡፡ የጸጥታ ጉዳይ አዋቂው ሪቻርድ ቱታ ታዲያ፣ ለችግሩ መፍትሔ ለማምጣት ሁለቱ ሀገራት፥ የጋራ የሀብት አስተዳደር መርሐ ግብሮችን ሥራ ላይ እንዲያውሉ ይመክራሉ፡፡ ከነዚህም መካከል አንዱ የጋራ የዓሣ ማሥገሪያ ቀጣና ማካለል እንደኾነ ጠቁመዋል። “እነዚኽ የተፈጥሮ ሀብቶች፣ አብዛኞቹ የማኅበረሰቡ አባላት ለኑሯቸው የሚጠቀሙባቸው ናቸው፡፡ ሀብታቱ ደግሞ ድንበር ተሻጋሪ እንጂ በሀገራቱ ወሰን ውስጥ ብቻ ተካለው የሚገኙ አይደሉም፡፡ ስለዚኽም የውኃ ሀብት፣ ለም የግጦሽ መሬት የመሳሰሉትን የተለያዩ ሀገራትን ድንበር የሚሻገሩ ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ዘዴን መቀየስ ያስፈልጋል። ምክንያቱም በድንበሮቹ አዋሳኝ አካባቢዎች ባሉት ማኅበረሰቦች መካከል እዚኽም እዚያም የሚከሠቱት አብዛኞቹ ግጭቶች መንሥኤአቸው ከጋራ ሀብቶች አጠቃቀም ጋራ የተያያዙ ናቸው፡፡” የኬንያ ባለሥልጣናት፣ ልዩ ስሙ ቶዶጋኒው በተባለው ስፍራ ለተከሠተው ሰሞነኛ ግጭት፣ ፈጣን ምላሽ አልሰጡም፤ በሚሉ ኬንያውያን በኩል ነቀፋ ተሰንዝሮባቸዋል፡፡ የኬኒያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ለትችቱ በሰጠው ምላሽ፣ ርምጃው የዘገየው ከኢትዮጵያ በኩል በአግባቡ መረጃ ስላልደረሰን ነው፤ ብሏል፡፡ ማይክል ሙቺሪ የኬኒያ ፖሊስ ቃል አቀባይ ናቸው፡፡ “ይህ ሁለቱን አገሮች የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡ በኬንያ የጸጥታ ተቋማት እና በኢትዮጵያ ባለሥልጣናት መካከል ያለ ነገር ነው፡፡ ግጭቱ ደርሷል በተባለበት ስፍራ ደርሰው ሪፖርታቸውን እስኪያቀርቡልን ድረስ እየተጠባበቅን ነው፡፡” የኬንያ መንግሥት ተጨማሪ የጸጥታ ኀይል በድንበር አካባቢ እያሰፈረ ነው፤ የዐርብቶ አደሮቹ መፈናቀል የተከሰተውም ከስጋት ነው የሚሉ አስተያየቶች ከተፈናቃዮቹ ተሰንዝሯል። ይኽንኑ በተመለከተ የተጠየቁት አቶ ወገነ፣ ኢትዮጵያ እና ኬንያ በጸጥታ እና በጋራ ልማት የሁለትዮሽ እና ስልታዊ ግኑኝነት ያላቸው፣ የወዳጅነት እንጂ የባላንጣነት ታሪክ የሌላቸው በመኾኑ፣ ብዙ የሚያሰጋ ነገር የለም፤ የፌዴራል መንግሥትም ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል ላይ ነው፤ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። የጠፉትን ዓሣ አሥጋሪዎች ለማግኘት፣ እኹንም ፍለጋው እንደቀጠለ መኾኑን፣ የሁለቱም አገሮች ባለሥልጣናት ገልጸዋል። ከግጭቱ በኋላ በስጋት ከአካባቢያቸው መፈናቀላቸው የገለጹት ዐርብቶ አደሮች ፣ ከረጂ ድርጅቶችም ኾነ ከመንግሥት እስከ አኹን የደረሰ ሰብአዊ ድጋፍ እንደሌለ ተናግረዋል። የተፈናቀሉ ዜጎች ዕለታዊ ቀለብ እያገኙ ያሉት ከተጠለሉበት ቀበሌ ነዋሪዎች እንደኾነ አመልክተዋል። ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም. አንሥቶ፣ ለሕይወታቸው ሰግተው ሲሸሹ ነበሩ ከተባሉ አርብቶ ዐደሮች ውስጥ፣ ወደ ቀዬአቸው የተመለሱ አለመኖራቸውን ያነሡት አስተያየት ሰጪው፣ ኾኖም ተፈናቃዮቹ የኢትዮጵያ እና የኬንያ ድንበር የመጨረሻ አዋሳኝ ወደ ኾነው ቀበሌያቸው መመለስ እንደሚሹ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ እና በኬንያ ዓሣ አሥጋሪዎች መካከል፣ በተፈጠረ የድንበር ላይ ግጭት፣ ከኢትዮጵያ በኩል 13፣ ከኬንያ ደግሞ 22 ሰዎች የደረሱበት አለመታወቁን፣ የአሜሪካ ድምፅ የአካባቢውን ነዋሪዎች እና ባለሥልጣናቱን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ ይታወሳል።    

የኮሪደር ልማቱ የአካል ጉዳተኞችን ለሥራ አጥነት ዳርጓል ተባለ

በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት፣ አካል ጉዳተኞችን ለሥራ አጥነት እየዳረገ ነው ሲል የከተማዋ የአካል ጉዳተኞች ማኅበር አስታወቀ፡፡ ለአሜሪ�
የአሜሪካ ድምፅ

የኮሪደር ልማቱ የአካል ጉዳተኞችን ለሥራ አጥነት ዳርጓል ተባለ

በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት፣ አካል ጉዳተኞችን ለሥራ አጥነት እየዳረገ ነው ሲል የከተማዋ የአካል ጉዳተኞች ማኅበር አስታወቀ፡፡ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ አካል ጉዳተኞችም የመስሪያ ቦታችን በመፍረሱ ለችግር ተዳርገናል ብለዋል፡፡ የከተማዋ አስተዳደር በበኩሉ የኮሪደር ልማቱ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ነው ይላል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሚያንማር ወደ ታይላንድ የገቡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው እንደሚመልሳቸው አስታወቀ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ዛሬ ዐርብ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ እስካሁን 246 ኢትዮጵያውያን ከሚያንማ�
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሚያንማር ወደ ታይላንድ የገቡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው እንደሚመልሳቸው አስታወቀ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ዛሬ ዐርብ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ እስካሁን 246 ኢትዮጵያውያን ከሚያንማር ታይላንድ መግባታቸውን ገልጸው፣ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት ከሕንድ ኒውዴልሂ የልዑካን ቡድን ተልኮ ከታይላንድ ኢትዮጵያውያኑን መመለስ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡ ከሚያንማር ወደ ታይላንድ ተመልሰው በካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም፣ መንግሥት ወደ አገራቸው እንዲመልሳቸው በጉጉት በመጠባበቅ ላይ መኾናቸውን ተናግረዋል። ከአጋቾች እጅ ነጻ ወጥተው በሚያንማር ወታደራዊ ካምፕ እንደሚገኙ የነገሩን ደግሞ ወደ ታይላንድ መሻገርን በተስፋ እየተጠባበቁ እንደኾነ ገልጸዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ትረምፕ እና መስክ በመንግሥት ወጪ ቅነሳቸው ላይ የሚቀርብባቸውን ትችት ተከላክለዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሁለተኛውን የአስተዳደራቸውን ዘመን ከጀመሩ ወዲህ ረቡዕ ዕለት ባካሄዱት የመጀመሪያ የካቢኔ አባላት ስብሰባ አ�
የአሜሪካ ድምፅ

ትረምፕ እና መስክ በመንግሥት ወጪ ቅነሳቸው ላይ የሚቀርብባቸውን ትችት ተከላክለዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ሁለተኛውን የአስተዳደራቸውን ዘመን ከጀመሩ ወዲህ ረቡዕ ዕለት ባካሄዱት የመጀመሪያ የካቢኔ አባላት ስብሰባ አስተዳደራቸው በፊዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ብክነት ለማስወገድ እና የሠራተኛ ኃይሉን ለመቀነስ እየወሰደ ባለው ርምጃ ላይ የሚቀርቡ ትችቶችን ተከላክለዋል። የአሜሪካ ድምጿ ቬሮኒካ ባልዴራስ ኢግሊሲያስ የትረምፕ አስተዳደር ርምጃ ያሳደረውን አንድምታ እንዲሁም ከሥራ የተባረሩ ሠራተኞች እና የዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪዎች የሚያሰሟቸውን ተቃውሞዎች በሚመለከት ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በዩክሬን ጉዳይ ቢለያዩም፣ የእንግሊዝ ጠቅላይ ምኒስትር ስታርመር ከትራምፕ ጋራ ኅብረት መፍጠር ይፈልጋሉ

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ጋራ ባደረጉት ውይይት፤ በዩክሬን እና በሩሲያ መካከል የሚካሄደውን ጦርነ�
የአሜሪካ ድምፅ

በዩክሬን ጉዳይ ቢለያዩም፣ የእንግሊዝ ጠቅላይ ምኒስትር ስታርመር ከትራምፕ ጋራ ኅብረት መፍጠር ይፈልጋሉ

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ጋራ ባደረጉት ውይይት፤ በዩክሬን እና በሩሲያ መካከል የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም፣ ኪቭን ያሳተፈ እና በአውሮፓ ሰላም አስከባሪ ኃይሎች የሚደገፍ ስምምነት ላይ ለመድረስ መወሰናቸውን አስታወቁ። ትላንት ሐሙስ በዋይት ሐውስ ያካሄዱትን ስብሰባ ተከትሎ ስታርመር በሰጡት መግለጫ እቅዱ «ዩክሬን ተግባራዊ የምታደርገው እና ፑቲን እንዳይመለስ በሚያስችል ኅይል የሚደገፍ ጠንካራ እና ፍትሃዊ የሆነ ሰላም ማምጣት» መሆኑን ተናግረዋል። የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሰኞ ዕለት ከትራምፕ ጋራ በዋይት ሐውስ በነበራቸው ውይይት፣ “አጥቂውን የሚሸልም ስምምነት ሰላም ሊያመጣ አይችልም” ሲሉ ከተናገሩት ጋራ የሚመሳሰል አስተያየት የሰጡት ስታርመር፣ አጥቂዋ ደግሞ ሩሲያ መሆኗን አፅንዖት ሰጥተው አመልክተዋል። ስታርመር አክለው ከሌሎች የአውሮፓ መሪዎች ጋራ በቅርበት ለመሥራት ቃል የገቡ ሲኾን፣ እንግሊዝ ከአጋሮቿ ጋራ በመኾን የሰላም አስከባሪ ኃይሎችን ለማሰማራት ዝግጁ መኾኗንም አስታውቀዋል። ትራምፕ በበሉላቸው፣ ስታርትመር እንደቅድመ ሁኔታ ያስቀመጡትን፣ ዩናይትድ ስቴትስ የአውሮፓ ሰላም አስከባሪ ኅይሎችን የመደገፍ ሚና ጨምሮ፣ ምንም ዐይነት የፀጥታ ዋስትና ለመስጠት ቃል ከመግባት ተቆጥበዋል። «ስምምነት ላይ እስከምንደርስ ድረስ ስለሰላም ማስከበር ማውራት ደስ አይለኝም» ሲሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተናገሩት ትራምፕ «የመጥፎ ዕድል ምልክት ማሳየት አልፈልግም» ብለዋል። ትራምፕ በንግግራቸው የደኅንነት ድጋፉን የሚሰጡት፣ አሜሪካ የዩክሬንን ልዩ ማዕድናት ማግኘት የሚያስችላት እና የጆ ባይደን አስተዳደር የሀገሪቱን ጦርንት ለመደገፍ ያወጡትን ገንዘብ እንደሚያስመልሱ የሚያረጋግጥ ስምምነት ላይ ከደረሱ ብቻ ሊሆን እነደሚችል ጠቁመዋል።  

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሶማሊያ ጉብኝት አደረጉ

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ በቱርክ ፕሬዝደንት ረሽፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የኹለቱ ሀገ�
የአሜሪካ ድምፅ

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሶማሊያ ጉብኝት አደረጉ

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ በቱርክ ፕሬዝደንት ረሽፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የኹለቱ ሀገራት ግንኙነት እየተሻሻለ ባለበት ወቅት፣ ወደ ሞቃዲሾ ያቀኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድና በሌሎች የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋዱ ላይ ለይፋዊ ጉብኝት ሞቃዲሹ እንደደረሱ፣ የአል ሻባብ እንደኾነ የተገመተ በርካታ ዙር የሞርታር ተኩስ ወደ አውሮፕላን ማረፊያው አቅጣጫ መከፈቱን በደኅንነት ስጋት ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ቢያንስ አንዱ የሞርታር ተኩስ በአውሮፕላን ማረፊያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኝ ጋራዥ ውስጥ ማረፉን ደግሞ ስሙ ያልተጠቀሰ የተቋሙ ባልደረባ ገልጿል። የሞርታር ጥቃቱን ተከትሎ የደረስ ጉዳት እንደሌለም ታውቋል። በሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ፕሬዝደንታዊ ቤተ መንግሥት ተወስደው ሁለቱ ወገኖች ውይይት አድርገዋል። ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ሞቃዲሹ የገቡት ዐቢይ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል። ሁለቱ ወገኖች ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ሲካሄዱ የቆዩ ተከታታይ ግንኙነቶች ቀጣይ መኾኑን ጠቅሰው፣ በኹለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደነበረበት የመመለሱን ሂደት ይበልጥ ያጠናክራል ሲሉ አክለዋል። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የባሕር ሠፈር በሊዝ ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ በኹለቱ ወገኖች መካከል የነበረው ግንኙነት ባለፈው አንድ ዓመት ሻክሮ ቆይቷል። ጉብኝቱ፣ 2ሺሕ 500 የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ ለማካተት የኹለቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናት በቅርቡ መስማማታቸውን ተከትሎ የተደረገ ነው። በኹለቱ ሀገራት መካከል ባለው ወታደራዊ ስምምነት መሠረትም፣ በአፍሪካ ኅብረት ከሚሳተፉት ውጪ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደሮችንም በሶማሊያ ታሰማራለች፡፡ መሪዎቹ በከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ስምምነት ላይ መደረሱን በመልካም መቀበላቸውን ባወጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል። ሁለቱ መሪዎች በተጨማሪም “በተጠናከረ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብር መተማመንን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል” ሲል የጋራ መግለጫው አክሏል። ዲፕሎማሲያዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብርን በማሳደግ መተማመንን መገንባት እንደሚያስፈልግ ኹለቱ መሪዎች አጽንኦት መስጠታቸውንም የጋራ መግለጫው አመልክቷል። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ሁለቱ መሪዎች ከዚህ ቀደም ካደረጓቸው ውይይቶች የቀጠለ ሰፋ ያለ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቋል። ውይይታቸው «በሰላም እና ፀጥታ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ እና በጋራ ሊሠሩ በሚችሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ ያተኮረ ነበር » ብሏል።    

ትራምፕ በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ ዐዳዲስ ቀረጦች ሊጥሉ ነው

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በእቅዳቸው መሰረት በመጪው ሳምንት ከካናዳ እና ከሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ቀረጥ እንደሚጥሉ አስታ�
የአሜሪካ ድምፅ

ትራምፕ በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ ዐዳዲስ ቀረጦች ሊጥሉ ነው

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በእቅዳቸው መሰረት በመጪው ሳምንት ከካናዳ እና ከሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ቀረጥ እንደሚጥሉ አስታወቁ። ትራምፕ ይህን ውሳኔያቸውን የሚተገብሩት ሁለቱ ጎረቤት ሀገራት አሁንም ወደ አሜሪካ የሚገቡትን የአደንዛዥ ዕፅ ፍሰት ለመግታት በቂ ጥረት አላደረጉም በማለት ነው። ትራምፕ አክለው በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ቻይና ላይ ከጣሉት 10 ከመቶ ቀረጥ በተጨማሪ ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ ሌላ 10 በመቶ ቀረጥ እንደሚጥሉ ትሩዝ በተሰኘው የማኅበራዊ ሚድያቸው ላይ አስታውቀዋል። ቻይና የመጀመሪያውን የትራምፕ ቀረጥ ተከትላ ከአሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ ተመሳሳይ ቀረጥ ጥላ ነበር። «አሁንም ከሜክሲኮ እና ካናዳ አደንዛዥ ዕፆች ወደ ሀገራችን እየጎረፉ ነው» ያሉት ትራምፕ «ከነዚህ መድኃኒቶች ውስጥ አብዛኞቹ በቻይና ተመርተው የሚቀርቡ ፈንተነል ናቸው» ብለዋል። ትራምፕ በቅርብ አጋሮቻቸው ካናዳ እና ሜክሲኮ ላይ ቀረጥ እንደሚጥሉ ያስታወቁት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ቢሆንም፣ የሜክሲኮ ፕሬዝደንት ክላውዲያ ሼንበም አደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን ለመቆጣጠር 10 ሺሕ ወታደሮችን ወደ ሀገራቸው ሰሜናዊ ድንበር እንደሚልኩ መናገራቸውን ተከትሎ ውሳኔያቸውን አዘግይተዋል። የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶም ጉዳዩን ለመፍታት «የፈንተነል ተቆጣጣሪ» እንደሚሰይሙ ተናግረው ነበር። 80 ከመቶ የውጭ ንግዳቸውን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የሚልኩት ሼንበም በዚህ ሳምንት መጀመሪያ፣ ከአሜሪካ ጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ እየጠበቁ መኾኑን እና ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻሉ ግን ሜክሲኮ በአሜሪካ ምርቶች ላይ ተመሳሳይ ቀረጥ እንደምትጥል አስታውቀው ነበር።  

በደባርቅ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ 16 ሰዎች ሞቱ

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ፣ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ በደረሰ የመኪና አደጋ የ16 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
የአሜሪካ ድምፅ

በደባርቅ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ 16 ሰዎች ሞቱ

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ፣ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ በደረሰ የመኪና አደጋ የ16 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ትምህርት እና ሥልጠና ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር ይበልጣል መርሻ፣ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ በስልክ እንደገለጹት፣ በዕለቱ ተሽከርካሪው፥ ከበየዳ ወደ ደባርቅ ወረዳ ሰዎችንና እህል ጭኖ በመጓዝ ላይ እያለ፣ ከረፋዱ 3፡30 ገደማ፣ ልዩ ስሙ “አበርጊና” በተባለ ቦታ ላይ ተገልብጦ 16 ተሳፋሪዎች ሲሞቱ፣ በ35ቱ ላይ ቀላል እና ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሷል። በዐማራ ክልል የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ትምህርት እና ሥልጠና ክፍል ሓላፊ ኢንስፔክተር ይበልጣል መርሻ፣ ዛሬ ኀሙስ ለአሜሪካ ድምፅ በስልክ እንደገለጹት፣ ከትላንት በስቲያ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ከረፋዱ 3:30 ገደማ፣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት-11591 የኾነ፣ በተለምዶ ካሶኒ እየተባለ የሚጠራ የደረቅ ጭነት መኪና፣ ከበየዳ ወደ ደባርቅ ከተማ እየተጓዘ ሳለ፣ ልዩ ስሙ አበጊና በተባለው ስፍራ ላይ በመገልበጡ በተሳፋሪዎች ላይ የምት እና የመቁሰል አደጋ መድረሱን ተናግረዋል። ከ16ቱ ሟቾች መካከል አራቱ ተፈናቃዮች ናቸው፤ ያሉት ኢንስፔክተር ይበልጣል፣ የጭነት መኪናው አሽከርካሪ እስከ አኹን በቁጥጥር ሥር እንዳልዋለ ተናግረዋል። ከአደጋው ከተረፉት ተሳፋሪዎች አንዱ እንደኾነ የሚናገረው ዮሐንስ ምትኬ፣ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ሳቢያ ከትግራይ ክልል በ2013 ዓ.ም. ተፈናቅሎ በደባርቅ ወረዳ ከማኅበረሰቡ ጋራ ተቀላቅሎ እንደሚኖር ጠቅሶ፣ ወደ በረሓ ለሥራ ፍለጋ እየተጓዘ እንደነበር ገልጿል። ለዚኽም፣ «ከአበጊና» ቀበሌ ከእርሱ ጋራ 18 ተፈናቃዮች በተሽከርካሪው መሳፈራቸውን አውስቶ፣ አንድ ኪሎ ሜትር እንኳን ሳይርቅ አደጋው መድረሱን አስረድቷል። ዮሐንስ አደጋው በእጁ ላይ ባደረሰበት ጉዳት፣ በደባርቅ ሆስፒታል በሕክምና እየተረዳ እንደሚገኝ አስታውቆ፣ አብረውት ከተሳፈሩት ውስጥ ሕይወታቸው ያለፈ እንዳሉም ገልጿል። በቅርቡ የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በደባርቅ ወረዳ ከማኅበረሰቡ ጋራ ተቀላቅለው ከሚኖሩት መካከል የተፈናቃዮች ማኅበር ምክትል ሊቀ መንበር የኾኑት መሪጌታ ጠበቃው ወልደ ገብርኤል፣ ከ2015 ዓ.ም. ወዲህ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ርዳታ ስለሚሰጣቸው አብዛኛዎቹ ለቀን ሥራ ከቦታ ወደ ቦታ እንደሚንቀሳቀሱ ገልጸዋል። ከትላንት በስቲያው የመኪና አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው 18 ተፈናቃዮች ግን፣ የዓለም ባንክ በአበጊና ብር እና ምግብ ይሰጣል፤ ለሥራ ያደራጃል፤ የሚል መረጃ ሰምተው እንደተጓዙና በስፍራው ከደረሱ በኋላ ርዳታ እንደማይሰጥ ሲረዱ ለሥራ ፍለጋ ወደ በረሓ ለመሔድ ዐቅደው እየተመለሱ እንደነበር፣ የማኅበሩ ምክትል ሊቀ መንበር መሪጌታ ጠበቃው አብራርተዋል። በደባርቅ ወረዳ፣ ከሁለት ሺሕ በላይ የጦርነት ተፈናቃዮች ከማኅበረሰቡ ጋራ ተቀላቅለው ይገኛሉ።  

በምሥራቅ ኮንጎ ፍንዳታ 11 ሰዎች ሞቱ

በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ምሥራቃዊ ክፍል የአማጺው ኤም 23 መሪዎችና ነዋሪዎች ሰልፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ በተከሰተ ፍንዳታ 11 ሰዎች ሲሞቱ 65 የሚሆኑ ተጎድተ�
የአሜሪካ ድምፅ

በምሥራቅ ኮንጎ ፍንዳታ 11 ሰዎች ሞቱ

በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ምሥራቃዊ ክፍል የአማጺው ኤም 23 መሪዎችና ነዋሪዎች ሰልፍ ማድረጋቸውን ተከትሎ በተከሰተ ፍንዳታ 11 ሰዎች ሲሞቱ 65 የሚሆኑ ተጎድተዋል። በማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች የተጋሩ ፎቶዎች እና ቪዲዮዎች በርካታ ሰዎች ሲሸሹ እና በደም የተለወሱ አስከሬኖችም መንገድ ላይ ወድቀው አሳይተዋል። ፍንዳታዎቹ በተከሰቱበት ወቅት የኤም 23 መሪዎች በማዕከላዊ ቡካቩ ከተማ ከነዋሪዎች ጋራ ውይይት በማድረግ ላይ ነበሩ። ፍንዳታው “የሽብር ሥራ እና በሕገ ወጥ መንገድ በኮንጎ በሚገኝ የውጪ ጦር የተፈጸመ ነው” ሲሉ የኮንጎ ፕሬዝደንት ፊሊክስ ቺሴኬዲ ክስ አሰምተዋል። ኤም 23 በበኩሉ «የኮንጎ ባለሥልጣናት ፍዳታውን አቀናብረዋል» ሲል ከሷል። “የኪንሻሳው አገዛዝ ሲቪሎችን ለማጥፋት ተነስቷል” ሲልም አክሏል።

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሶማሊያ ጉብኝት አደረጉ  

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ በቱርክ ፕሬዝደንት ረሽፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የኹለቱ ሀገ�
የአሜሪካ ድምፅ

ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሶማሊያ ጉብኝት አደረጉ  

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ባለፈው ታኅሣሥ ወር መጀመሪያ በቱርክ ፕሬዝደንት ረሽፕ ታይፕ ኤርዶዋን አሸማጋይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ የኹለቱ ሀገራት ግንኙነት እየተሻሻለ ባለበት ወቅት፣ ወደ ሞቃዲሾ ያቀኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድና በሌሎች የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ረፋዱ ላይ ለይፋዊ ጉብኝት ሞቃዲሹ እንደደረሱ፣ የአል ሻባብ እንደኾነ የተገመተ በርካታ ዙር የሞርታር ተኩስ ወደ አውሮፕላን ማረፊያው አቅጣጫ መከፈቱን በደኅንነት ስጋት ምክንያት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ቢያንስ አንዱ የሞርታር ተኩስ በአውሮፕላን ማረፊያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኝ ጋራዥ ውስጥ ማረፉን ደግሞ ስሙ ያልተጠቀሰ የተቋሙ ባልደረባ ገልጿል። የሞርታር ጥቃቱን ተከትሎ የደረስ ጉዳት እንደሌለም ታውቋል። በሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼኽ መሐሙድ አቀባበል የተደረገላቸው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወደ ፕሬዝደንታዊ ቤተ መንግሥት ተወስደው ሁለቱ ወገኖች ውይይት አድርገዋል። ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ሞቃዲሹ የገቡት ዐቢይ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል። ሁለቱ ወገኖች ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝት ባለፉት ጥቂት ወራት ሲካሄዱ የቆዩ ተከታታይ ግንኙነቶች ቀጣይ መኾኑን ጠቅሰው፣ በኹለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደነበረበት የመመለሱን ሂደት ይበልጥ ያጠናክራል ሲሉ አክለዋል ። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የባሕር ሠፈር በሊዝ ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሎ በኹለቱ ወገኖች መካከል የነበረው ግንኙነት ባለፈው አንድ ዓመት ሻክሮ ቆይቷል። ጉብኝቱ፣ 2ሺሕ 500 የኢትዮጵያ ወታደሮችን በአፍሪካ ኅብረት ልዑክ ውስጥ ለማካተት የኹለቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናት በቅርቡ መስማማታቸውን ተከትሎ የተደረገ ነው። በኹለቱ ሀገራት መካከል ባለው ወታደራዊ ስምምነት መሠረትም፣ በአፍሪካ ኅብረት ከሚሳተፉት ውጪ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደሮችንም በሶማሊያ ታሰማራለች፡፡ መሪዎቹ በከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ስምምነት ላይ መደረሱን በመልካም መቀበላቸውን ባወጡት የጋራ መግለጫ አስታውቀዋል። ሁለቱ መሪዎች በተጨማሪም “በተጠናከረ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብር መተማመንን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል” ሲል የጋራ መግለጫው አክሏል። ዲፕሎማሲያዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትብብርን በማሳደግ መተማመንን መገንባት እንደሚያስፈልግ ኹለቱ መሪዎች አጽንኦት መስጠታቸውንም የጋራ መግለጫው አመልክቷል። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስትር ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ሁለቱ መሪዎች ከዚህ ቀደም ካደረጓቸው ውይይቶች የቀጠለ ሰፋ ያለ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቋል። ውይይታቸው «በሰላም እና ፀጥታ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ እና በጋራ ሊሠሩ በሚችሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ ያተኮረ ነበር » ብሏል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በተቃዋሚዎች የቀረበውን የሽግግር መንግሥት ጥያቄ ውድቅ አደረገ

ሰሞኑን በአዲሰ አበባ ከተማ ለአራት ቀናት የቆየ ውይይት ያካሄዱት ተቃዋሚዎቹ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁሉን አካ�
የአሜሪካ ድምፅ

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በተቃዋሚዎች የቀረበውን የሽግግር መንግሥት ጥያቄ ውድቅ አደረገ

ሰሞኑን በአዲሰ አበባ ከተማ ለአራት ቀናት የቆየ ውይይት ያካሄዱት ተቃዋሚዎቹ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁሉን አካታች የኦሮሚያ ክልል የሽግግር መንግሥት እንዲመሰረት እንደሚሠሩ ገልጸዋል። “ሐሳቡ የቀረበው ምርጫ ከመካሄዱ በፊት ሰላም ለማምጣት የጋራ መንግሥት ስለ ሚያሰፈልግ ነው” ሲሉ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር መረራ ጉዲና ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል። “የኢትዮጵያ መንግሥት በሕገ መንግሥቱ መሠረት በምርጫ የተቋቋመ ነው” ያሉት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ቃል አቀባይ ኃይሉ አዱኛ በበኩላቸው፣ የፓርቲዎቹ መግለጫ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ምላሽ ሰጥተዋል።   የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት፣ ባወጣው መግለጫ፣ በኦነግና በኦፌኮ የተጠራውን ጉባኤ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋራ አብሮ የሚሄድ ፕሮጀክት ነው በማለት አውግዟል። ተቃዋሚዎቹ የኦሮሞ ነጻነት ግንቀባር (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ለአራት ቀናት በተካሄደው ጉባኤ ላይ ለግጭት መነሻ የሚኾኑ የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ ችግሮችንም አንስተው መነጋገራቸውን የኦፌኮ ሊቀመንበር ተናግረዋል። ይሄንኑ መነሻ አድርገው መግለጫ ያወጡት የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ ግንባርና ሌሎች በሶማሌ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ተቃውሞ አቅርበዋል። ኦፌኮና ኦነግ፣ ድሬዳዋ እና ሞያሌን ጨምሮ በአንዳንድ ግዛቶች ላይ ይገባኛል ጥያቄ ማንሳታቸውን የጠቀሱት ፓርቲዎቹ፣ አካሔዱ የፌዴራል ሕገ መንግሥቱን እና በተለያዩ ብሔረሰቦች መካከል ያለውን በሰላም አብሮ የመኖር መርህ ይፃረራል በማለት አውግዘዋል። በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሰጡት የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ ሐሳባቸው ጥያቄዎች በድርድርና በንግግር እንዲፈቱ ማድረግ መሆኑን አብራርተዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የአንጥረኛነት ፈተና በትግራይ

በትግራይ ክልል በባህላዊ የብረታብረት መገልገያ ዕቃዎች እና ጌጣጌጦች ሥራ ላይ የተሰማሩ የጥበበ እድ ሞያተኞች፣ እየደረሰብን ነው ባሉት ማኅበራዊ መገለልና ጥ
የአሜሪካ ድምፅ

የአንጥረኛነት ፈተና በትግራይ

በትግራይ ክልል በባህላዊ የብረታብረት መገልገያ ዕቃዎች እና ጌጣጌጦች ሥራ ላይ የተሰማሩ የጥበበ እድ ሞያተኞች፣ እየደረሰብን ነው ባሉት ማኅበራዊ መገለልና ጥቃት የተነሣ፣ ልጆቻቸው ከትምህርት ገበታ እየራቁ መኾናቸው በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።  በየጊዜው እየከፋ መምጣቱን በገለጹት ጥቃት ለተፈናቃይነት መዳረጋቸውን የተናገሩት የእጅ ጥበብ ሞያተኞቹ፣ «አስነዋሪ» ሲሉ በገለጹት አኳኋን ግድያ የተፈጸመባቸው የቤተሰቦቻቸው አባላት መኖራቸውን ለአሜሪካ ድምፅ አስረድተዋል። መብቶቻቸውን በሕግ ለማስከበር ጥረት ቢያደርጉም «ምስክር አቅርቡ» በሚል ፍትሕ ለማግኘት አለመቻላቸውን ሞያተኞቹ አመልክተዋል። «መምህራን፣ ካህናት እና ፖሊስ አመለካከታቸው ቢስተካከል እኛም እንደ ሰው እንኖር ነበር፤” ሲሉም መፍትሔው የአመለካከት ለውጥ እንደኾነ ጠቁመዋል። የእጅ ባለሞያዎቹ ይደርስብናል ያሉትን በደል ለመከላከልና ሲበደሉም ፍትሕ ርትዕ እንዲያገኙ የሚያግዝ፦ »የትግራይ የእደ ጥበብ ባለሞያዎች ማኅበር" የተሰኘ የመብቶች ተሟጋች ማቋቋማቸውንም አክለው አስታውቀዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የካናዳ የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች ስጋት ፈጥሯል

ከአውሮፓ እስከ ሰሜን አሜሪካ፣ ሀገራት የኢሚግሬሽን ፖሊሲያቸውን እያጠናከሩ ነው። ከዓለም ሀገራት ለስደተኞች መልካም አቀባበል በማድረግ የምትታወቀው ካናዳ
የአሜሪካ ድምፅ

የካናዳ የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች ስጋት ፈጥሯል

ከአውሮፓ እስከ ሰሜን አሜሪካ፣ ሀገራት የኢሚግሬሽን ፖሊሲያቸውን እያጠናከሩ ነው። ከዓለም ሀገራት ለስደተኞች መልካም አቀባበል በማድረግ የምትታወቀው ካናዳም ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ለውጦችን ይፋ አድርጋለች። ማሻሻያዎቹ ይበልጥ እየጠበቁ የሄዱትን ዓለም አቀፍ የኢሚግሬሽን ፖሊሲዎች የሚያንፀባርቁ መሆናቸውም ተመልክቷል። አርዙማ ኮምፓኦሬ ከካልጋሪ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የአዲስ አበባ “የኮሪደር ልማት” አወዛጋቢ ውጤቶች የነዋሪዎች አስተያየት

በአዲስ አበባ የተመረጡ አካባቢዎች፣ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በመከናወን ላይ ናቸው። ፕሮጄክቶቹ፣ የተሽከርካሪ እና የእግረኛ መንገዶችን፣ ልዩ የብስክሌ�
የአሜሪካ ድምፅ

የአዲስ አበባ “የኮሪደር ልማት” አወዛጋቢ ውጤቶች የነዋሪዎች አስተያየት

በአዲስ አበባ የተመረጡ አካባቢዎች፣ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በመከናወን ላይ ናቸው። ፕሮጄክቶቹ፣ የተሽከርካሪ እና የእግረኛ መንገዶችን፣ ልዩ የብስክሌት መንገዶችንና ሌሎችም የመሠረተ ልማት ውጤቶችን አስገኝተዋል፡፡ በሌላ በኩል፣ የርእሰ መዲናዋ የረዥም ጊዜ ነዋሪዎች መፈናቀልና በመንገዶቹ ዳር ላይ ያሉ የንግድ ተቋማት መፍረስ፣ ከፕሮጀክቶቹ አወዛጋቢ ውጤቶች መካከል ኾነው ቀጥለዋል፡፡ በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችም፣ መሰል “የኮሪደር ልማት” ፕሮጀክቶች ትግበራ፣ ተመሳሳይ ውጤቶችን እያስከተሉ በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በአሜሪካ የዶሮ እንፍሉዌንዛን ለመዋጋት 1 ቢሊዮን ዶላር ተመደበ

የአእዋፍ እንፍልዌንዛ ባለፉት ሦስት ዓመታት በአሜሪካ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮዎችን በመግደሉና ከፍተኛ የእንቁላል እጥረት በመከሰቱ መንግሥት በሽታውን ለመዋ
የአሜሪካ ድምፅ

በአሜሪካ የዶሮ እንፍሉዌንዛን ለመዋጋት 1 ቢሊዮን ዶላር ተመደበ

የአእዋፍ እንፍልዌንዛ ባለፉት ሦስት ዓመታት በአሜሪካ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮዎችን በመግደሉና ከፍተኛ የእንቁላል እጥረት በመከሰቱ መንግሥት በሽታውን ለመዋጋትና ከውጪ እንቁላል ለማስገባት 1 ቢሊዮን ዶላር መመደቡን የሀገሪቱ የግብርና ምኒስትር አስታውቀዋል። ባለፉት ሦስት ዓመታት በተከሰተው የአእዋፍ እንፍሉዌንዛ 166 ሚሊዮን ዶሮዎች መሞታቸውን የአሜሪካው የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በሽታው አንድ ሺሕ የሚሆኑ የወተት ላሞችንና 70 የሚሆኑ ሰዎችንም ማጥቃቱ ታውቋል። ባለፈው ዓመት አንድ ሰው በበሽታው ሞቷል። አምስት ሚሊዮን ዶላር ለአርቢዎች ነፃ የዶሮ ምርመራ ለማድረግ እንዲሁም 400 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ በበሽታው የተያዙ ዶሮዎቻቸውን ለመግደል ለሚሹ አርቢዎች እንደተመደበ የግብርና ምኒስትሩ ብሩክ ሮሊንድ አስታውቀዋል። ገንዘቡ በባለሀብቱ ኢላን መስክ በተመራው ቡድን በቅርቡ ከግብርና ሚኒስቴሩ ላይ ከተቀነስው በጀት ላይ እንደሚገኝም ታውቋል። ወደ ውጪ የሚላከውን እንቁላል በመቀነስና ከውጪ የሚገባውን በመጨመር በእንቁላል ገበያ ላይ የሚታየውን ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ዋጋ ለመቀነስ አስተዳደሩ ማቀዱም ተመልክቷል።

ዩክሬይን የተደቀነባት ድምጽ አልባው ትግል ፡- ውጊያ ያንገፈገፋቸው ወታደሮቿ የአዕምሮ ጤና ቀውስ

ለሦስት ዓመታት ያለማቋረጥ ጦርነት የተካሄደባት ዩክሬን የአዕምሮ ጤና ቀውስ ተደቅኖባታል፣ ሆስፒታሎቿ  በጭንቀት፣ በድብርት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ በማለ
የአሜሪካ ድምፅ

ዩክሬይን የተደቀነባት ድምጽ አልባው ትግል ፡- ውጊያ ያንገፈገፋቸው ወታደሮቿ የአዕምሮ ጤና ቀውስ

ለሦስት ዓመታት ያለማቋረጥ ጦርነት የተካሄደባት ዩክሬን የአዕምሮ ጤና ቀውስ ተደቅኖባታል፣ ሆስፒታሎቿ  በጭንቀት፣ በድብርት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ በማለፍ በሚከሰት የአዕምሮ ቀውስ በሚሰቃዩ ወታደሮች ተጨናንቀዋል። ዶክተሮችም እነዚህ በገሃድ የማይታዩ ድብቅ  ቁስሎች ለብዙ ዐሥርት ዓመታት ተቆራኝተዋት ሊቆዩ እንደሚችሉ  ይናገራሉ። ያን ቦቻት በምዕራብ ዩክሬን ከምትገኘው ኤልቪቭ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 

ደቡብ አፍሪካ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ አስወጣች

ደቡብ አፍሪካ 127 የሚኾኑ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ አስወጥታለች፡፡ አራቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው መኾኑም ታውቋል። ወታደሮቹ ከሁለት ዓመታ
የአሜሪካ ድምፅ

ደቡብ አፍሪካ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ አስወጣች

ደቡብ አፍሪካ 127 የሚኾኑ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ አስወጥታለች፡፡ አራቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው መኾኑም ታውቋል። ወታደሮቹ ከሁለት ዓመታት በፊት የ16 ሀገራት ጥምር በሆነው በደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ ወይም ሳድክ ኅይል ውስጥ ታቅፈው፣ በሩዋንዳ ከሚደገፈው ኤም 23 ጋራ በመፋለም ላይ ያለውን የኮንጎ መንግሥት ለመደገፍ የተሠማሩ ነበሩ። ሃያ አንዱ ወታደሮች ትላንት ማክሰኞ የተመለሱ ሲሆን፣ 106 የሚሆኑት ደግሞ ዛሬ ረቡዕ ተመልሰው ደቡብ አፍሪካ ወታደሮቿን በሙሉ አስወጥታ አጠናቃለች፡፡ የተጎዱት ወታደሮች ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ፣ ከተመለሱት ውስጥ አንዳንዶቹ የሥነ ልቦና ሕክምና እንደሚያስፈልጋቸውም ታውቋል። የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ባለፈው ጥር የተገደሉ 14 ወታደሮችን አስከሬን እንድታስመልስ በሃገሪቱ ውስጥ ጫና በርትቶበት ነበር። ደቡብ አፍሪካ በአጠቃላይ አንድ ሺሕ የሚሆኑ ወታደሮችን ወደ ኮንጎ እንዳሰማራች ሪፖርቶችና ትንተናዎች ቢያመለከቱም፣ ባለሥልታናት ግን ትክክለኛውን ቁጥር አልገለጹም።

በደቡብ ኦሞ ዞን አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆች ወለደች  

በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ የአይሎሀ ቀበሌ ነዋሪ የኾነችው ወይዘሮ ማርታ ታከለ  በአንድ  ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም መገላገሏ ተገለጸ፡፡ የወይዘሮ ማርታ �
የአሜሪካ ድምፅ

በደቡብ ኦሞ ዞን አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆች ወለደች  

በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ የአይሎሀ ቀበሌ ነዋሪ የኾነችው ወይዘሮ ማርታ ታከለ  በአንድ  ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም መገላገሏ ተገለጸ፡፡ የወይዘሮ ማርታ ባለቤት አቶ አንጅሎ አዲሱ በስልክ ለአሜሪካ ድምፅ እንደገለጸው የ29 ዓመቷ ባለቤቱ በድንገት ምጥ መጥቶባት ሆስፒታል ከገባች በኋላ ለሰዓታት በምጥ መውለድ ባለመቻሏ በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል በቀዶ ህክምና አራቱንም ልጆች ተገላግላለች።  የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና ዳይሬክተር ፣ ዶክተር ቢንያም አስራት፣ ወይዘሮ ማርታ ታከለ ከፀነሰች ከሦስት ወሯ ጀምሮ በሆስፒታሉ የእርግዝና ክትትል ስታደርግ እንደነበረ አመልክተው በእርግዝናዋ ወቅት በውስጥ አካላት መመርመሪያ  በአልትራሳውንድ  የታየው የሦስት ልጆች ጽንስ ቢሆንም በቀዶ ህክምናው አራት ልጆች እንደወለደች ገልጸዋል፡፡ የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና ዳይሬክተር ፣ ዶክተር ቢንያም አስራት፣ ሕጻናቱ ከተወለዱ በኋላ ያነሱትን ፎቶ አጋርተውናል።  ባለቤቱ ቋሚ ሥራ እና ገቢ የሌላት የቤት እመቤት እንደሆነች እና እርሱም ቤተሠቡን የሚያስተዳድረው  በጉልበት ሥራ በሚያገኘው የቀን ገቢ መሆኑን  የአራት ዓመት ወንድ ልጅ እንዳላቸው የገለጸው አቶ አንጀሎ አሁን ደግሞ “በአንድ ጊዜ የአራት ልጆች አባት መኾኔ ቢያስደስተኝም እንዴት እንደማሳድጋቸው ግራ ገብቶኛል” ሲል ስጋቱን አጋርቷል።  "እስካሁንም  የምንኖረው በፈጣሪ ርዳታና እና ባለቤቴ በቀን ሞያተኝነት በምታገኘው ገቢ እየተደጎምን ነው “ ሲል አክሏል። ሁለት ሴት እና ሁለት ወንድ ሕፃናቱ የተወለዱት  ዘጠኝ ወራቸውን ሞልተው እንደኾነም ሐኪሙ  አመልክተዋል። ሦስቱ ሕጻናት ክብደታቸው1 ነጥብ 8 ፣  1ነጥብ 9፣ እና  1ነጥብ 8 ኪሎ ግራም  ሲኾኑ የአራተኛው ልጅ ክብደት አንድ ኪሎ ብቻ መኾኑን የገለጹት ዶክተር ቢንያም  ለጊዜው ጨቅላ ሕጻናት በሙቀት ማቆያ ውስጥ እንዲቆይ ከተደረገ በኋላ  ዛሬ ወደ እናቱ ተመልሷል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ጨቅላ ሕጻናቱም እናታቸውም በሙሉ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የሕክምና ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል፡፡   ከአሁን በፊት በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታሉ አንዲት እናት ሦስት ልጆችን መገላገሏን አስታውሰው በሆስፒታሉ  በአንድ ጊዜ አራት ልጆች ሲወለዱ የአሁኑ የመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ በሶማሊያ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ ነገ ሐሙስ በሶማሊያ ጉብኝት በማድረግ ከሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ ጋራ እንደሚወያዩ ከሶማሊያ ከመንግ�
የአሜሪካ ድምፅ

ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ በሶማሊያ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ ነገ ሐሙስ በሶማሊያ ጉብኝት በማድረግ ከሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ ጋራ እንደሚወያዩ ከሶማሊያ ከመንግሥት ምንጮች መረጃውን ማግኘቱን ኤኤፍፒ አመልክቷል። ሁለቱ ሀገራት የሻከረውን ግንኙነታቸውን ለማደስ በመሞከር ላይ ባሉበት ወቅት የሚካሄደው ጉብኝት “በአንካራ የተፈጸመውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግና ለማጠናቀቅ ከሚደረጉ ሰፊ ጥረቶች አንዱ እንደሆነ” ዘገባው አመልክቷል። “በጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ የሚመራ ከፍተኛ የባለሥልጣኖች ቡድን ነገ ሞቃዲሹ እንደሚደርስ ይጠበቃል” ሲሉ ለፕሬዝደንታዊ ቤተ መንግሥቱ ቅርብ የሆኑና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጭ መናገራቸውን ኤኤፍፒ በዘገባው አመልቷልክ። ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራስ ገዝ ከሆነችው ሶማሊላንድ ጋራ ባለፈው ዓመት የባሕር ዳርቻ በሊዝ ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሟን ተከትሉ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ውጥረት ሰፍኖ ነበር። የአንካራውን ስምምነት ተከትሎ ግን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ሙሉ ለሙሉ ወደነበረበት እንደሚመልሱ አስታውቀዋል።

የአሜሪካ ምክርቤት አፈ ጉባኤ በጀት ለማሳለፍ የሚያችል በቂ የሪፐብሊካን ድምፅ አገኙ

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ማይክ ጆንሰን ማክሰኞ ምሽት ድምፅ የሚሰጥበትን የበጀት ረቂቅ ለማሳለፍ የሚያስችል 217 ድምፅ አሰባስበዋል። ይህም ዲሞ�
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ ምክርቤት አፈ ጉባኤ በጀት ለማሳለፍ የሚያችል በቂ የሪፐብሊካን ድምፅ አገኙ

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ማይክ ጆንሰን ማክሰኞ ምሽት ድምፅ የሚሰጥበትን የበጀት ረቂቅ ለማሳለፍ የሚያስችል 217 ድምፅ አሰባስበዋል። ይህም ዲሞክራቶች «ግዴለሽነት» ሲሉ የሚጠሩትን  የሪፐብሊካን ፓርቲ የግብር እና የመንግሥት ወጪ ቅነሳ ጥረት ለማሳካት የሚያግዛቸው መሆኑም ተመልክቷል። «ከፊታችን ጠንካራ ሥራ ቢጠብቀንም፣ ቅድሚያ ለአሜሪካ የሚለውን አጀንዳችንን ግን እናሳካለን» ሲሉ ለጋዜጠኞች አስተያየታቸውን የሰጡት ጆንሰን «የተወሰነውን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም እናሳካለን። ይህ የሂደት ቀዳሚው ክፍል ብቻ ነው» ብለዋል። ጆንሰን እና ሌሎች የምክርቤቱ ሪፐብሊካን አመራሮች ባወጡት መግለጫ ዋና ግባቸው «ድንበር ጥበቃን የሚያጠናክር፣ ለቤተሰቦች እና ሥራ ፈጣሪዎች ታክስን የሚቀንስ፣ አሜሪካ በኃይል ምርት የነበራትን የበላይነት የሚመልስ፣ አሜሪካ በዓለም መድረክ ላይ ያላትን አቋም የሚያጠናክር እና መንግሥት ለአሜሪካውያን የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን» የሚያደርግ ሕግ ማፅደቅ እንደሆነ ገልጸዋል። የምክር ቤቱ የዲሞክራት ፓርቲ መሪ ሃኪም ጄፍሪስ በበኩላቸው ሪፐብሊካኖች ለቀድሞ ወታደሮች ይሰጡ የነበሩ ጥቅማጥቅሞችን እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎች ይደረግ የነበረውን የምግብ ርዳታ እንዲሁም የጤና አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት እየሠሩ ነው ብለዋል። ጄፍሪስ አክለው «የሪፐብሊካኖቹ የበጀት እቅድ ለሀብታሞቹ፣ ደህና ኑሮ ላላቸው እና ከነሱ ጋራ ለተሳሰሩት እስከ 4.5 ትሪሊየን ዶላን የሚደርስ ግብር ቀንሶ ሠራተኛ አሜሪካውያን እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው አሜሪካውያን እንዲከፍሉ የሚያደርግ ነው» ሲሉ ለጋዜጠኞች አብራርተዋል።   ከድምፅ አሰጣጡ ሂደት በፊት በርካታ ሪፐብሊካን የምክር ቤቱ አባላት ባካሄዱት ስብሰባም፣ የግብር ቅነሳው የሚተገበርበት መንገድ እና ለአሜሪካ መራጮች ድጋፍ የሚያደርጉ የድጎማ ፕሮግራሞች ሳይነኩ የአሜሪካን ከፍተኛ ወጪ መቀነስ የሚቻልበት መንገድ እንደሚያሳስባቸው ገልጸዋል። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ሕግ አውጪዎቹ «ትልቅ እና ውብ» ሲሉ የጠሩትን እና የሀገር ውስጥ ፖሊሲዎቻቸው አካል የሆነውን ረቂቅ ሕግ እንዲያፀድቁ ጠይቀዋል።

የሱዳን ወታደራዊ አውሮፕላን ተከስክሶ 46 ሰዎች ሞቱ

በሱዳን ዋና የመዲናዋ መንትያ ከተማ ኦምዱርማን ወታደራዊ አየር ማረፊያ አቅራቢያ በሚገኝ የመኖሪያ መንደር አካባቢ፤ የጦር አውሮፕላን ተከስክሶ 46 ሰዎች መሞታ�
የአሜሪካ ድምፅ

የሱዳን ወታደራዊ አውሮፕላን ተከስክሶ 46 ሰዎች ሞቱ

በሱዳን ዋና የመዲናዋ መንትያ ከተማ ኦምዱርማን ወታደራዊ አየር ማረፊያ አቅራቢያ በሚገኝ የመኖሪያ መንደር አካባቢ፤ የጦር አውሮፕላን ተከስክሶ 46 ሰዎች መሞታቸውን፤ የኻርቱም የመንግሥት ብዙኀን መገናኛ ቢሮ የገለጸ ሲሆን ከሟቾቹ መካከል አንድ ከፍተኛ የጦር አዛዥ እንደሚገኙ የወታደራዊ ምንጮች ዘግበዋል። አደጋው የደረሰው ትላንት ማክሰኞ ማምሻውን በሰሜናዊ ኦምዱርማን በዋዲ ሲዳይና ወታደራዊ አየር ማረፊያ አቅራቢያ ነው። የሱዳን ጦር በአደጋው ብዙ ወታደራዊ አባላት እና ሲቪሎች መሞታቸውን ቢገልጽም ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል። አውሮፕላኑ የተከሰከሰው በቴክኒክ ችግር ሊሆን እንደሚችል ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል። የሱዳን መገናኛ ጽሕፈት ቤትም በአደጋው ዐስር ሰዎች ቆስለዋል ብሏል። ከሟቾቹ መካከል ከዚህ ቀደም በመላው ኻርቱም የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዥ ሆነው ያገለገሉት የኻርቱም ሜጀር ጄነራል ባህር አሕመድ እንደሚገኙበት የወታደራዊ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ዳኛ ትራምፕ ኤፒ የዜና ተቋም ከዋይት ሃውስ እንዳይዘግብ የጣሉትን ገደብ አፀና

ዋሽንግተን — አሶሽየትድ ፕሬስ (ኤፒ) የዜና ተቋም በዘገባዎቹ የሜክሲኮ ባህረሰላጤ የሚለውን ስያሜ መጠቀም በመቀጠሉ በዋይት ሀውስ ተገኝቶ እንዳይዘግብ በፕሬ
የአሜሪካ ድምፅ

የዩናይትድ ስቴትስ ዳኛ ትራምፕ ኤፒ የዜና ተቋም ከዋይት ሃውስ እንዳይዘግብ የጣሉትን ገደብ አፀና

ዋሽንግተን — አሶሽየትድ ፕሬስ (ኤፒ) የዜና ተቋም በዘገባዎቹ የሜክሲኮ ባህረሰላጤ የሚለውን ስያሜ መጠቀም በመቀጠሉ በዋይት ሀውስ ተገኝቶ እንዳይዘግብ በፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የተጣለበት ገደብ እንዲነሳለት ያቀረበው ጥያቄ በአንድ ፌደራል ዳኛ ውድቅ ተደረገ። በፕሬዝደንት ትራምፕ የተሰየሙት የዩናይትድ ስቴትስ ፍርድ ቤት ዳኛ ትሬቨር ሚክፋደን፣ ኤፒ የፍርድ ሂደቱ እስኪጠናቀቅ« ኦቫል ኦፊስ» በተሰኘው የፕሬዝደንቱ ጽሕፈት ቤት ፣ በፕሬዝደንቱ አውሮፕላን (ኤር ፎርስ ዋን) እና ሌሎች በዋይት ሀውስ የሚከናወኑ ዝግጅቶች ላይ ተገኝቶ የመዘገብ መብቱ እንዲመለስ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል። ሚክፋደን በውሳኔያቸው ፕሬዝዳንቱ «ግላዊ በኾኑ አካባቢዎች» ላይ የጣሉት ገደብ፣ ከዚህ ቀደም ፍርድቤቶች የመንግሥት ባለሥልጣናት በጋዜጠኞች ላይ የተጣሉትን ገደቦችን ካነሱባቸው ሁኔታዎች የተለየ ነው ብለዋል። በፍርድ ሂደቱ ላይም «ኤፒ ለስኬት የሚያበቃ ሁኔታ አሳይቷል ማለት አልችልም» ብለዋል። ዳኛው አክለው ዋይት ሀውስ በኤፒ የዜና ሽፋን ምክንያት አድሎ መፈፀሙን ተናግረዋል። ችግር የሚፈጥር ሁኔታ መሆኑንም ገልጸዋል። የዳኛውን ውሳኔ ተከትሎ ዋይት ሀውስ ባወጣው መግለጫ «የዩናይትድ ስቴትስን ፕሬዝደንት በቢሮዋቸው እና በአውሮፕላናቸው ተገኝቶ መጠየቅ ለጋዜጠኞች የተሰጠ ልዩ መብት እንጂ ሕጋዊ ግዴታ አይደለም» ብሏል። የኤፒ ቃል አቀባይ በበኩላቸው የዜና ተቋሙ «ለፕሬስ እና ለሕዝብ ያለመንግሥት አፀፋ በነፃነት የመናገር መብት መቆሙን እንደሚቀጥል» ገልጸዋል። ኤፒ ባለፈው ሳምንት አርብ በሦስት ከፍተኛ የትራምፕ ረዳቶች ላይ ክስ የመሰረተው፤ ዘጋቢዎቹ በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ተገኝተው እንዳይዘግቡ የተላለፈው ውሳኔ በዩናይትድ ስቴትስ ሕገ መንግስት የመጀመሪያ የማሻሻያ አንቀፅ ላይ የተደነገገውን በመጣስ፣ መንግሥት በዜና ዘገባ ውስጥ የሚጠቀመውን ቋንቋ የሚያስገድድ እና የንግግር መብትን የሚገድብ ነው በማለት ነው። የኤፒ ጠበቃ ቻርስ ቶቢን በችሎት ቀርበው ባስረዱበት ወቅትም «ሕገ መንግሥቱ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንትም ኾኑ ሌላ የመንግሥት ባለሥልጣን ጋዜጠኞችንንም ኾነ ሌላ አካል፣ የመንግሥትን ቋንቋ በመጠቀም ዜና እንዲዘግቡ ከማድረግ ይከለክላል» ብለዋል። የትራምፕ አስተዳደር ጠበቆች በበኩላቸ ኤፒ «ፕሬዝዳንቱ ጋራ የመግባት ልዩ የሚዲያ ፈቃድ» የማግኘት ሕገ መንግሥታዊ መብት የለውም ሲሉ ተከራክረዋል። ትራምፕ ባለፈው ወር የሜክሲኮ ባህረሰላጤ የአሜሪካ ባህረሰላጤ በሚለው ስምን እንዲተካ ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ አስተላልፈው የነበረ ሲሆን፣ ኤፒ የትራምፕን ውሳኔ በመጥቀስ የባህረሰላጤውን የቆየ ስም መጠቀም እንደሚቀጥል ገልጿል። በምላሹ የኤፒ ጋዜጠኞች በዋይት ሀውስ ተገኝተው እንዳይዘግቡ እገዳ ተጥሎባቸዋል።

ትረምፕ ከፈረንሳዩ መሪ ጋር በዩክሬን ዕጣ ፈንታ ላይ ተወያዩ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በዩክሬን የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም፣ ከዩክሬን እና ከሩሲያ ጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተና�
የአሜሪካ ድምፅ

ትረምፕ ከፈረንሳዩ መሪ ጋር በዩክሬን ዕጣ ፈንታ ላይ ተወያዩ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በዩክሬን የሚካሄደውን ጦርነት ለማስቆም፣ ከዩክሬን እና ከሩሲያ ጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተናገሩ። ትራምፕ ይህን ያሉት ትላንት ከፈረንሳዩ መሪ ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በዋይት ኃውስ ተገናኝተው ስብሰባዎችን ከአካሄዱ እና አውሮፓ ትልቅ ሚና እንዲኖራት ከአሳሰቡ በኋላ ነው። ፓሪስ በበኩሏ ከሞስኮ ተጨማሪ ማረጋገጫዎችን ትፈልጋለች። የአሜሪካ ድምጿ አኒታ ፓውል ከዋይት ሀውስ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የመከላከያ ምኒስትሩ የኤታማዦር ሹሞቹ ሰብሳቢ ከሥራቸው የተባረሩበትን ምክንያት አስረዱ

የአሜሪካው የመከላከያ ምኒስትር ፒት ሄግሴት፣ የኤታማዦር ሹሞች ቡድን ሰብሳቢ የሆኑት ሲ ኪው ብራውን ከሥራቸው የተባረሩበትን ምክንያት ባለፈው ሳምንት መጨረ�
የአሜሪካ ድምፅ

የመከላከያ ምኒስትሩ የኤታማዦር ሹሞቹ ሰብሳቢ ከሥራቸው የተባረሩበትን ምክንያት አስረዱ

የአሜሪካው የመከላከያ ምኒስትር ፒት ሄግሴት፣ የኤታማዦር ሹሞች ቡድን ሰብሳቢ የሆኑት ሲ ኪው ብራውን ከሥራቸው የተባረሩበትን ምክንያት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ አስረድተዋል። ባለፈው ዓርብ ነበር ፕሬዝደንት ትረሞፕ የኤታማዦር ሹሞቹን ሰብሳቢ ከሥራቸው ማንሳታቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ ያስታወቁት፡፡ የቪኦኤ የፔንታገን ዘጋቢ ካርላ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የኢትዮጵያን የታዳሽ ኀይል ሀብት ወደ ዶላር የሚቀይረው የቢትኮይን አሠሣ 

በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉን የክሪፕቶ ከረንሲ መገበያያ ዓይነቶች መካከል አንዱ የኾነውን የቢትኮይን ማይኒንግ ወይም በግርድፍ ትርጉሙ በይ
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮጵያን የታዳሽ ኀይል ሀብት ወደ ዶላር የሚቀይረው የቢትኮይን አሠሣ 

በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉን የክሪፕቶ ከረንሲ መገበያያ ዓይነቶች መካከል አንዱ የኾነውን የቢትኮይን ማይኒንግ ወይም በግርድፍ ትርጉሙ በይነ መረብ አሠሣ (ፍለጋ) በመጀመር ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ኾነች።አገሪቱ፣ ባለፉት 15 ዓመታት በገነባቻቸው የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኀይል ማመንጫ ግድቦች አማካይነት ከፍተኛ የኀይል አቅርቦት ቢኖራትም፤ የኤሌክትሪክ ኀይሉን ለተጠቃሚው ሕዝብ እና ለሚፈለገው ግልጋሎት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ዐቅም አለመገንባቷን ባለሞያዎች ይናገራሉ። ይህን ክፍተት በመጠቀም፣ ከ22 በላይ የሚደርሱ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ተቋማት፣ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኀይል አቅርቦት የሚሻውን የቢትኮይን ማይኒንግ ወይም በይነ መረባዊ አሠሣ ሥራ ጀምረዋል። ከዚኽም ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ከዘርፉ 55 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። የያዝነው የ2017 ዓ.ም ሲጠናቀቅ ደግሞ፣ 123 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንደምታገኝ፣ የዓለም አቀፍ የገበያ ትንተና ገጽ የኾነው Nasdaq ትንበያ ይጠቁማል። በኢትዮጵያ፣ በክሪፕቶ ከረንሲ ዓይነቶች ለመገበያየት፣ አኹንም ድረስ የሕግ ማሕቀፍ ስላልተበጀለት ክልክል ቢኾንም፣ ቢትኮይንን ፈልጎ የማግኘት ሥራ ላይ መሰማራት ለሚፈልጉ ፈቃድ መስጠት ተጀምሯል። ይኹን እንጂ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማትን የኀይል ፍላጎት በተፈላጊው መጠን ሟሟላት ስለመቻሉ ጥርጣሬዎች ይነሣሉ። በጎርጎርሳውያኑ የዘመን አቆጣጠር በ2008፣ ሳቶቺ ናካሞቶ በሚል የብዕር ስም በሚታወቅ የቴክኖሎጂ  ባለሞያ የተፈለሰፈው ቢት ኮይን፣ ሰዎች በማናቸውም ሰዓት፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል፣ ያለባንክ እና ያለምንም የገንዘብ መተመኛ ለመገበያየት የሚያስችል ሲኾን፣ በበይነ መረብ ላይ ባለቤቱ በሚመሠርተው የምስጢር ቁልፍ ብቻ የሚንቀሳቀስ ነው። መሥራቹ ሳታቺ ናካሞቶ፣ በቁጥር የተወሰኑ ቢትኮይኖችን፣ ኮድ ባላቸው ቁልፎች በመቆለፍ ሰዎች አሥሠው በማግኘት እንዲጠቀሙባቸው ለቋል።  በኢትዮጵያ ፈቃድ አውጥተው የቢትኮይን ማይኒንግ ወይም ፍለጋ ከጀመሩ ተቋማት መካከል ቀዳሚ የሆነው፣ QRB ላብስ ተቋም መሥራች ነሞ ሥምረት፣ አገሪቱ የምታመርተውን የኤሌክትሪክ ኀይል አቅርቦት ተደራሽ የሚያደርግ መሠረተ ልማት አለመኖሩን ጠቅሶ፣ በቢትኮይን አሠሣ፥ በግድቦቹ የሚባክነውን የኤሌክትሪክ ኀይል አገሪቱ ወደ ዶላር እንድትለውጥ ያግዛል፤ ይላል። በአኹን ሰዓት አንድ ቢትኮይን፣ በዓለም ገበያ ላይ እስከ 90ሺሕ የዩናይትድ ስቴትስ ዶላር ይተመናል። ይኹን እንጂ፣ አንድን ቢትኮይን አሥሦ ለማግኘት 155 ሺሕ ኪሎዋት የሚኾን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ያስፈልጋል። ይህ አኀዝ በኢትዮጵያ 1ሺሕ33 መኖሪያ ቤቶችን ለማብራት ያስችላል። እ.ኤ.አ በ2023፣ 50ሺሕ 294 ኪሎ ቶን የኤሌክትሪክ ኀይል  መጠቀሟን፣ ኢንተር ዳታ የተሰኘ ተቋም ድረ ገጽ አመላክቷል። በዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ማዕከል በኾነው ሲልከን ቫሊ ባለሞያ የኾነው ቃል ካሳ፣ በኢትዮጵያ ክርፕቶ ከረንሲ እና የቢትኮይን አሠሣ ምን እንደ ኾኑ፣ ወጣቶች እና ፖሊስ አውጭዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ይሠራል። ለብዙዎች በቀላሉ ለመረዳት የሚያዳግተውን ፅንሰ ሐሳብ ለአሜሪካ ድምፅ አብራርቷል። ኢታን ቬራ፣ መቀመጫውን በሲያትል ዋሺንግተን ያደረገውና ኢትዮጵያን ጨምሮ በልዩ ልዩ የዓለም ክፍሎች፣ ለቢት ኮይን አምራች ተቋማት የሶፍትዌር እና የማሽን አቅርቦትን የሚያመቻቸው የሉግዘር ቴክ ባልደረባ ነው፤ በኢትዮጵያ ከሚገኙ አሣሽ ድርጅቶችም ጋራ አብሮ ይሠራል። ኢትዮጵያ በታዳሽ ኀይል ማመንጨት ኀይሏ ተመራጭ ኾናለች፤ ይላል። ኢታን ቬራ፣ ቢትኮይን፥ የአገሪቱን ሕዝብ የኀይል አቅርቦት እየተሻማ ይኾን እንደኾን፣ በአሜሪካ ድምፅ ለቀረበለት ጥያቄ፤ በኢትዮጵያ  የሚመነጨው ኀይል በተገቢው መንገድ ለማኅበረሰቡ ተደራሽ አለመኾኑን ጠቅሶ፣ በቢትኮይን ፍለጋ ላይ የተሰማሩ ተቋማት የኀይል መጠኑ ሳይባክን አገሪቱ ገቢ እንድታገኝ በማስቻል እያገዙ ነው፤ ይላል። አብዛኛዎቹ በቢት ኮይን አሠሣ እና ዝላይ የተሰማሩ ተቋማት፣ ድርጅቶቻቸውንና ማሽኖቻቸውን በኀይል አመንጪ ግድቦች አቅራቢያ እንደሚተክሉ ኢታን ቬራ ይናገራል። በአንድ እና በሁለት ሰው የሚሠራውና እምብዛም የሥራ ዕድል ፈጠራ ዐቅም የሌለው የቢት ኮይን አሠሣ ሥራ፣ አገሪቱ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ በማድረግ ስኬታማ ኾኗል። አገሪቱ፣ ባለፈው ዓመት ብቻ 55 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ስታደርግ፤ የያዝነው የ2017 ዓ.ም ሲጠናቀቅ 123 ሚሊየን ዶላር ገቢ እንደምታገኝ፣ የዓለም አቀፍ የገበያ ትንተና ገጽ የኾነው Nasdaq ተንብይዋል። ይኹን እንጂ፣ ማሽኖችን በማስገባት እና ከተቋማት ጋራ ሥራን በማሳለጥ፣ ተግዳሮቶች እና መጓተቶች እንደነበሩ፣ የQRB ላብስ መሥራች ነሞ ሥምረት ተናግሯል። የለግዘር-ቴክ ሥራ አስፈጻሚ ኢታን ቬራም፣ አገሪቱ ሥራውን ለማሳለጥ የሚረዳ የፌደራል እና የክልል ፖሊሲዎች ማዘጋጀት እንደሚያስፈልጋት ጠቁሟል። በሌላ በኩል፣ በኢትዮጵያ ፈቃድ አውጥቶ ቢትኮይን መፈለግ የሚቻል ሲኾን፣ ቢትኮይንን ጨምሮ በሌሎች የክሪፕቶ ከረንሲ ዓይነቶች መገበያየት ግን ሕገ ወጥ እንደኾነ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. ባረቀቀው ሰነድ ላይ አስታውቋል። ይህ ውሳኔ፣ የማኅበረሰቡን ግንዛቤ እና ክሪፕቶ ከረሲን የሚያካትት ባለመኾኑ፣ «ለኅብረተሰቡ ደኅንነት የተወሰደ ርምጃ ነው፤» የሚለው ቃል ካሳ፣ ይኹን እንጂ ማኀበረሰቡም ኾነ የመንግሥት አካላት ስለ ጉዳዩ ማወቅና ከዘመኑ ጋራ ለመራመድ ዝግጁ መኾን ይጠበቅባቸዋል፤ ይላል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት፣ በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሥልጣናት የእጅ ስልክ ላይ በመደወልና በጽሑፍ መልእክት ለቃለ መጠይቅ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። በተመሳሳይ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኀይል አገልግሎት ድርጅት፣ ከቢትኮይን ገቢ የሚደረገው የውጭ ምንዛሬ(ዶላር) ፍሰት፣ ተገቢው የኀይል አቅርቦት መስመር ዝርጋታ ላይ ስለመዋሉ፣ እንዲሁም ሥራውን ለመሥራት ወደ ሀገር ለገቡ ተቋማት የማኅበረሰቡን የኀይል አቅርቦት ፍላጎት ባልተሻማ መልኩ ለማቅረብ እያደረጓቸው ስላሉ እንቅስቃሴዎች ጥያቄ ብናቀርብም፣ የኮምዩኒኬሽንስ ድሬክተር ሞገስ መኮንን፣ ከዚኽ ጉዳይ ጋራ በተያያዘ በቅርቡ ቀጣይ ሪፖርት እስኪወጣ ድረስ በጉዳዩ ላይ ቃለ መጠይቅ እንደማይሰጡ ገልጸውልናል።

Get more results via ClueGoal