በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ህይወት የቀየረው የባህርዳሩ ግሬስ ማዕከል
newsare.net
ከ20 አመት በፊት በአማራ ክልል፣ ባህርዳር ከተማ ውስጥ የተመሰረተው ግሬስ ፋውንዴሽን ማዕከል አሳዳጊ አልባ ኾነው ተጥለው የተገኙ ጨቅላ ህፃናትን ሰብስቦ በማሳበሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ህይወት የቀየረው የባህርዳሩ ግሬስ ማዕከል
ከ20 አመት በፊት በአማራ ክልል፣ ባህርዳር ከተማ ውስጥ የተመሰረተው ግሬስ ፋውንዴሽን ማዕከል አሳዳጊ አልባ ኾነው ተጥለው የተገኙ ጨቅላ ህፃናትን ሰብስቦ በማሳደግ እና የቀን ስራ እየሰሩ ኑሯቸውን ለሚገፉ እናቶች ልጆቻቸውን በመያዝ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። የዚህ ተቋም መስራች አሜሪካዊቷ ሜርሲ ኤሪክሰን ስትሆን ምህረት በሚለው ስሟ ኢትዮጵያዊ ስሟ ትታወቃለች። በዚህ ተቋም ስራዋ አማካኝነት ከተዋወቀችው የትዳር አጋሯ ሰፊነው ብርሃን ጋር በመሆን በገነቡት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ከ800 በላይ ልጆችን ተቀብለው እያስተማሩ ነው። ስመኝሽ የቆየ ከምህረት እና ሰፊነው ጋር ያደረገችውን ቆይታ ከተያያዘው ቪዲዮ ያገኛሉ። Read more