Ethiopia



ወጣቶችና የአካባቢያቸው ሰላም

ጦርነት፣ ግጭት አለመረጋጋት እና ሰላም ማጣት በወጣቶች ህይወት ላይ ምን ዐይነት ተፅዕኖ እንደፈጠረ የወጣቶችን አስተያየት ጠይቀናል። ምላሻቸውን ከተያያዘው

የወጣቶች የሰላምና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄ   

መንግሥት፣ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚታዩትን አለመረጋጋቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ወጣቶች ጥሪ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ በ
የአሜሪካ ድምፅ

የወጣቶች የሰላምና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጥያቄ   

መንግሥት፣ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚታዩትን አለመረጋጋቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ወጣቶች ጥሪ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ በተካሔደ ሀገር አቀፍ የወጣቶች መድረክ ላይ የተሳተፉ ወጣቶች፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት አስተያየት፣ በሀገሪቱ የሚታዩት ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ወጣቱ በነፃነት እንዳይሠራ እያደረጉት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ወጣቶቹ፣ መንግሥት ለእነዚህ ችግሮች መፍትሔ እንዲሰጥ እና የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተቃሚነት እንዲያረጋግጥም ጠይቀዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

አካል ጉዳተኛ መኾኑ ለሌሎች መደገፊያ ከመሥራት አላገደውም

ከልጅነቱ ጀምሮ አንድ እግሩ አልታዘዝ ያለው መለስ እዮብ፣ አካል ጉዳተኛ መኾኑ ሌሎች  መደገፊያ ያጡ አካል ጉዳተኛ ኢትዮጵያውያን ከመርዳት አላገደውም። ከብዙ
የአሜሪካ ድምፅ

አካል ጉዳተኛ መኾኑ ለሌሎች መደገፊያ ከመሥራት አላገደውም

ከልጅነቱ ጀምሮ አንድ እግሩ አልታዘዝ ያለው መለስ እዮብ፣ አካል ጉዳተኛ መኾኑ ሌሎች  መደገፊያ ያጡ አካል ጉዳተኛ ኢትዮጵያውያን ከመርዳት አላገደውም። ከብዙ ዓመታት በፊት አንድ መንግሥታዊ ያልኾነ ድርጅት በሰጠው ክራንች ድጋፍ ያደገው መለስ፣ አንድ ቀን ድጋፉ በመሰበሩ ወድቆ ዳግም ተጎድቶ እንደነበር ያስታውሳል። በወቅቱ የነበረው ሁኔታም ለሌሎች በተመሳሳይ ችግር ውስጥ ለሚያልፉ ሰዎች ድጋፍ ማድረግ የሚያስችል አዲስ ነገር ማቋቋም እንዳለበት እንደወሰነ ገልጿል። ሆስፒታል ተቀጥሮ በመሥራት ያገኘውን ገንዘብ አጠራቅሞና፣ ከጓደኞቹ ያገኘውን ጨምሮ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ድጋፍ መስጠት መጀመሩን አስታውቋል። ] በዚህ ዙሪያ የተሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

አዲስ አበባ ላይ የታየው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል

ዓመታዊው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል ጥር 23 በአዲስ አበባ ከተማ ተከፍቶ፣ በዛ ያሉ ፊልሞች ታይተዋል። በዝነኛው የቼክ ሪፓብሊክ አትሌት ኤሚል ዛቶፔክ ሕይወት ላ
የአሜሪካ ድምፅ

አዲስ አበባ ላይ የታየው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል

ዓመታዊው የአውሮፓ ፊልም ፌስቲቫል ጥር 23 በአዲስ አበባ ከተማ ተከፍቶ፣ በዛ ያሉ ፊልሞች ታይተዋል። በዝነኛው የቼክ ሪፓብሊክ አትሌት ኤሚል ዛቶፔክ ሕይወት ላይ ያተኮረው ዛቶፔክ ፊልም በመክፈቻው ዕለት ለዕይታ ሲበቃ፣ በአጠቃላይ ሁለት ተጋባዥ የኢትዮጵያ ፊልሞችን ጨምሮ 28 ፊልሞች ለእይታ እንደሚበቁ ታውቋል፡፡ ፊልሞች “ሰዎች እርስ በርስ እንዲተዋወቁ የማድረግ አቅም አላቸው” ያሉት በአፍሪካ ኅብረት የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሃቪየር ኒኞ ፔሬዝ፣ የፌስቲቫሉ ዓላማም ሰዎችን ይበልጥ በማቀራረብ መተባበርን ማጎልበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በዚህ ዙሪያ የተሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር የማዕድን ዘርፉን ለማልማት ብርቱ ፍላጎት አለው

በአፍሪካ የማዕድን ዘርፍ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ባለፈው ሳምንት ደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ኬፕ ታውን ውስጥ ተካሂዷል። ለአራት ቀናት የተካሄደው ጉባኤ በአመዛኙ ያተ
የአሜሪካ ድምፅ

የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር የማዕድን ዘርፉን ለማልማት ብርቱ ፍላጎት አለው

በአፍሪካ የማዕድን ዘርፍ ላይ ያተኮረ ጉባኤ ባለፈው ሳምንት ደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ኬፕ ታውን ውስጥ ተካሂዷል። ለአራት ቀናት የተካሄደው ጉባኤ በአመዛኙ ያተኮረው የትረምፕ አስተዳደር የውጭ ርዳታ ፖሊሲ በውል ባልለየበት ሁኒታ አሜሪካ በአፍሪካ የማዕድን ዘርፍ ምን ዓይነት ተሳትፎ ታደርጋለች በሚለው ላይ ነበር፡፡ በስፍራው ተገኝታ ጉባኤውን የተከታተለችው ቪኪ ስታርክ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ሳልማን ሩሽዲን በስለት ለመግደል የሞከረው ግለሰብ የፍርድ ቤት ሂደት ጀመረ

ደራሲ ሳልማን ሩሽዲን ኒው ዮርክ ውስጥ በተካሄደ በአንድ ትምህርታዊ ስብሰባ ላይ ሳለ በቢላ ወግቶ ለመግደል የሞከረው ግለሰብ የፍርድ ቤት ሂደት ዛሬ ሲጀመር፣ የ
የአሜሪካ ድምፅ

ሳልማን ሩሽዲን በስለት ለመግደል የሞከረው ግለሰብ የፍርድ ቤት ሂደት ጀመረ

ደራሲ ሳልማን ሩሽዲን ኒው ዮርክ ውስጥ በተካሄደ በአንድ ትምህርታዊ ስብሰባ ላይ ሳለ በቢላ ወግቶ ለመግደል የሞከረው ግለሰብ የፍርድ ቤት ሂደት ዛሬ ሲጀመር፣ የከሳሽ ጠበቆች የመክፈቻ ክርክራቸውን ማሰማት ጀምረዋል። ሩሽዲ በፍርድ ቤቱ እንዲመሰክር የሚጠበቅ ሲሆን፣ በመግደል ሙከራ ከተከሰሰው ሃዲ ማታር ጋራ ከጥቃቱ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት ይገናኛል ተብሏል። ከሁለት ዓመታት በፊት በኒው ዮርክ በተዘጋጀና ደራሲያን ደኅንነታቸውን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው ባተኮረ  ስብሰባ ላይ በመናገር ላይ ሳለ ነበር ሃዲ ማታር ወደ መድረኩ በመሄድ ሩሽዲን ከ12 ጊዜ በላይ በበርካታ የሰውነቱ ክፍሎች ላይ በቢላ የወጋው። ጥቃቱ ሩሽዲን በከፊል ማያት የተሳነው እንዲኾን ሲያደርግ አንድ እጁ ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። ትውልዱ ከህንድ የሆነውና የአሜሪካና የእንግሊዝ ጥምር ዜግነት ያለው ሩሽዲ፣ በጥቃቱ ላይ ያተኮረ ግለ ታሪክ መጽሓፍ ባለፈው ዓመት አሳትሟል።   ሩሽዲ በእ.አ.አ 1989 ያሳተመውና “ሳታኒክ ቨርስስ” የተሰኘው መጽሐፍ እስልምናን የሚያንቋሽሽ ነው በሚል በበርካታ የሃይማኖቱ ተከታዮች ይወገዛል። የኢራኑ አያቶላ ኾሚኒም ሩሽዲ እንዲገደል ፋትዋ አውጥተው ነበር። ኢራን ትዕዛዙን እንደማትፈጽም መግለጿን ተከትሎ ለረጅም ጊዜ ተደብቆ የነበረው ሩሽዲ እንደልብ መዘዋወር ጀምሮ ነበር።

“ደራሮ” የምስጋና በዓል በጌዴኦ

ጥር ወር ደቡባዊ ኢትዮጵያ ለሚገኙ የጌዴኦ ብሔረሰብ አባላት የመኸር ምርታቸውን የሚሰበስቡበትና፣ አሮጌ ያሉትን ዓመት “አዲስ” ብለው የሚቀበሉበት ዓመታዊ በ
የአሜሪካ ድምፅ

“ደራሮ” የምስጋና በዓል በጌዴኦ

ጥር ወር ደቡባዊ ኢትዮጵያ ለሚገኙ የጌዴኦ ብሔረሰብ አባላት የመኸር ምርታቸውን የሚሰበስቡበትና፣ አሮጌ ያሉትን ዓመት “አዲስ” ብለው የሚቀበሉበት ዓመታዊ በዓላቸውን ነው። ይኽን ጊዜ የመረጡትና የሰየሙትም በአካባቢው ደምቃ በምትወጣው “ደራሮ” አበባ ምክኒያት ነው።  ቅዳሜ ዕለት በዲላ ከተማ የተከበረው በዓል ይዘት ምን እንደሚመስል ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 

ፊላደልፊያ ኤግልስ ቡድን ካንሳስ ቺፍስን ቡድን በመርታት  «የሱፐር ቦል» አሸናፊ ኾነ

የፊላደልፊያ ኢግልስ ቡድን የካንሳስ ቺፍስ ቡድን ላይ የበላይነትን በመቀዳጀት የዘንድሮው የአሜሪካ እግር ኳስ ሊጎች የፍጻሜ ጨዋታ «ሱፐር ቦል» አሸናፊ
የአሜሪካ ድምፅ

ፊላደልፊያ ኤግልስ ቡድን ካንሳስ ቺፍስን ቡድን በመርታት  «የሱፐር ቦል» አሸናፊ ኾነ

የፊላደልፊያ ኢግልስ ቡድን የካንሳስ ቺፍስ ቡድን ላይ የበላይነትን በመቀዳጀት የዘንድሮው የአሜሪካ እግር ኳስ ሊጎች የፍጻሜ ጨዋታ «ሱፐር ቦል» አሸናፊ ኾነ። አሸናፊው ቡድን ያለፈው ዓመት ቻምፒዮንተ ፎካካሪውን የረታው 40-22 በኾነ ውጤት ነው። የካንሳስ ቺፍ ቡድን ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት የአሜሪካ ብሔራዊ ሊግ አሸናፊ ይሆናል በሚል ተስፋ ከተፎካካሪው ቡድን በመጠኑ የላቀ ግምት ተሰጥቶት ነበር። ይሁንና ኒው ኦርሌየንስ ከተማ ሲዛርስ ሱፐርደም ውስጥ በተካሄደው ጨዋታ የፊላደልፊያ ኤግልስ ተጫዎቾች 34 ነጥቦችን እስካስቆጠሩበት ሦስተኛው የጨዋታው ምዕራፍ ድረስ የካንሳስ ቺፍስ ተጫዎቾች አንድም ነጥብ እንዳያስቆጥሩ ማድረግ ችለዋል። የፊላደልፊያ ኤግልስ አጥቂ መስመር ተጨዋች ጄለን ኸርትስ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተሰይሟል። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጨዋታውን በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲኾን ፣ በሥልጣን ዘመኑ «ሱፐር ቦል» ጨዋታን በስፍራው ተገኝቶ የተመለከተ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነዋል። ከጨዋታው በፊት ፕሬዝደንቱ ባሰራጩት የፕሬስ መግለጫ ላይ «እግር ኳስ የአሜሪካ እጅግ ተወዳጅ ስፖርት ነው። ለዚህም መልካም ምክንያቶች አሉ። የብሔራዊ አንድነት ስሜትን ያጎለብታል፣ ቤተሰቦችን፣ ጓደኞችን እና ደጋፊዎችን አንድ ላይ በማሰባሰብ ማኅበረሰቦችን ያጠናክራል» ብለዋል። «ይህ ዓመታዊ ልማድ ልዩነቶቻችንን የሚሻገር እና ወታደራዊ አገልግሎት ጓዶቻችን፣ ሕግ አስከባሪ መኮንኖች እና ቅድሚያ ምላሽ ሰጪዎች በጀግንነት የሚጠብቁትን የቤተሰብ፣ የእምነት እና የነጻነት የጋራ አርበኛ እሴቶቻችንን ያሳያል» ሲሉም አክለዋል። «ሱፐር ቦል» በሚል የሚጠራው የአሜሪካ እግር ኳስ ሊግ የውድድር ዘመን የፍጻሜ ምሽት ከ120 ሚሊየን ሰዎች እንደተመለከቱት የተገመተ ሲሆን ፣ በዚህ ጨዋታ ወቅት የ30 ሴኮንድ ርዝመት ያለው ማስታወቂያ ለማስነገር የሚከፈለው 8 ሚሊየን ዶላር በክብረ ወሰንነት ተመዝግቧል። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት፣ በአውሮፓዊያኑ አዲስ ዓመት ኒው ኦርሊንስ በሚገኘው በርበን ጎዳና ላይ በተፈጸመ የሽብር ጥቃት፣ በከባድ መኪና ተዳምጠው ለተገደሉት እና ለቆሰሉ ዜጎች እንዲሁም የመጀመሪያ ምላሽ ሰጪዎች የመታሰቢያ ሥነ ስርዐት ተከናውኗል።

በሊቢያ 28 ፍልሰተኞች በጅምላ ተቀብረው ተገኙ

በሊቢያ ደቡብ ምሥራቅ ኩፍራ በተባለ አውራጃ የ28 ፍለሰተኞች አስከሬን በአንድ ሥፍራ ተቀብሮ መገኘቱን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ሥፍራው ፍልሰተኞቹ ታግተው
የአሜሪካ ድምፅ

በሊቢያ 28 ፍልሰተኞች በጅምላ ተቀብረው ተገኙ

በሊቢያ ደቡብ ምሥራቅ ኩፍራ በተባለ አውራጃ የ28 ፍለሰተኞች አስከሬን በአንድ ሥፍራ ተቀብሮ መገኘቱን ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ሥፍራው ፍልሰተኞቹ ታግተው ሰቆቃ ሲፈጸምባቸው የነበረ መሆኑም ተመልክቷል። ፍልሰተኞቹ ከሰሃራ በታች ካሉ ሃገራት የሄዱ እንደኾነም ታውቋል። የሃገሪቱ የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ቢሮ እንዳስታወቀው የመቃብር ሥፍራው የተገኘው የሕገ ወጥ ዝውውር ሰለባ የሆኑ ፍልሰተኞች  ታግተው ሰቆቃ የሚፈጸምባቸው ሥፍራዎች ላይ ባደረጉት አሰሳ ነው። ከሰሃራ በታች ካሉ ሃገራት የሄዱና ታግተው ሰቆቃ ሲፈጸምባቸው የነበሩ ሰባ ስድስት ፍልሰተኞችን ነጻ ማውጣታቸውንም ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። አንድ ሊቢያዊና ሁለት የሌሎች ሃገራት ዜጎች መያዛቸውም ተመልክቷል። የሃገሪቱ የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ካወጣው መግለጫ ጋራ የተያያዘው ፎቶግራፍ፣ ነጻ የውጡት ፍልሰተኞች ገርጥተው፣ በፊታቸውና በሌሎችም የሰውነት ክፍሎቻቸው ላይ ጠባሳ እንዳለባቸው አሳይቷል። በእ.አ.አ 2011 በሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት ሀገራት ደጋፊነት በተነሳው አመጽ፣ የረጅም ጊዜ መሪው ሞአመር ጋዳፊ ከሥልጣን ከተወገዱ ወዲህ ሊቢያ ከሁከት አልተለየችም።

የአሜሪካ የጸረ ኤች አይ ቪ ድጋፍ ጉዳይ በደቡብ አፍሪካ የፈጠረው ስጋት

ዩናይትድ ስቴትስ አብዛኛው የውጭ ርዳታ ለሦስት ወራት እንዲቋረጥ ያደረገችውን ውሳኔ ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ኤች አይ ቪ በደማቸው ያሉ ሰዎችን የሚረዱ ድር
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ የጸረ ኤች አይ ቪ ድጋፍ ጉዳይ በደቡብ አፍሪካ የፈጠረው ስጋት

ዩናይትድ ስቴትስ አብዛኛው የውጭ ርዳታ ለሦስት ወራት እንዲቋረጥ ያደረገችውን ውሳኔ ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ኤች አይ ቪ በደማቸው ያሉ ሰዎችን የሚረዱ ድርጅቶች ምን እንደሚያደርጉ ግራ ተጋብተዋል። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር «ነፍስ አድን» የርዳታ ሥራዎች እንደሚቀጥሉ አስታውቋል። ይሁን እንጂ ቀደም ብለው ሥራቸውን ያቆሙ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በመቀጠል ምን ማድረግ እንዳለባቸው በግልጽ እንደማያውቁ ይናገራሉ። በዓመታት የተመዘገቡ ክንዋኔዎች ሊቀለበሱ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላቸውም ይገልጻሉ። ኬት ባርትሌት ከጆሀንስበርግ ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

እስራኤል ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቀው እንዲወጡ ለማስቻል እንዲያቅዱ ጦሯን አዘዘች

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ውድመት የደረሰበት የጋዛ ክልል የሚተዳደርበትን አስመልክቶ ያቀረቡትን ሐሳብ ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቀው እንዲወጡ ለማስቻል እንዲያቅዱ ጦሯን አዘዘች

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ውድመት የደረሰበት የጋዛ ክልል የሚተዳደርበትን አስመልክቶ ያቀረቡትን ሐሳብ ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ፍልስጤማውያን ከጋዛ ሰርጥ እንዲወጡ የሚያስችል እቅድ እንዲያወጣ ሰራዊቱን አዟል። የመከላከያ ሚንስቴር እስራኤል ካትስ ትላንት ሃሙስ ሲናገሩ፡ «የእስራኤል መከላከያ ኃይሎች የጋዛ ነዋሪዎች በፈቃዳቸው አካባቢውን ለቀው መሄድ የሚያስችላቸው እቅድ እንዲያዘጋጅ መመሪያ ሰጥቻለሁ» ብለዋል። ካትዝ እቅዱ «የመውጫ መንገድ እና የየብስ ማቋረጫ፤ እንዲሁም በባህር እና በአየር ለመጓጓዝ የሚያስችሉ አማራጮች ዝግጅት ያካትታል» ብለዋል።  የመከላከያ ሚንስትሩ አክለውም፤ የጋዛ ነዋሪዎች በጦርነቱ ወቅት በሃማስ ታጣቂዎች ላይ በተነጣጠሩት የእስራኤል የምድር ጦር እና የአየር ድብደባዎች የተጎዳውን አካባቢ ለቀው እንዲወጡ ትረምፕ የያዙት “ቆራጥ እቅድ” ያሉትን በደስታ መቀበላቸውን ተናግረዋል።  ትረምፕ በበኩላቸው ትላንት ሃሙስ በሰጡት አስተያየት እስራኤል ከሃማስ ጋር ያካሄደችው ጦርነት ካበቃ በኋላ የጋዛ ሰርጥን ለዩናይትድ ስቴትስ አሳልፋ መስጠት አለባት፤ ምንም አይነት የአሜሪካ ወታደር በዚያ ማሰማራትም አያስፈልግም ብለዋል። የሜዲትራኒያንን ባህር የሚያዋስነው አካባቢ ያለውን ጠባቡን የጋዛ ሰርጥ ዩናይትድ ስቴትስ በባለቤትነት እንድታስተዳድረው ያላቸውን ፍላጎት አስመልክቶ ‘ትሩዝ ሶሻል’ በተባለው የማሕበራዊ ግንኙነት መድረካቸው ላይ ያሰፈሩት ትረምፕ፤ በእርሳቸውም እቅድ መሠረት ቁጥራቸው ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ፍልስጤማውያን “አዳዲስ እና ዘመናዊ ቤቶች ባሉባቸው ለደህንነታቸው አስተማማኝ በሆኑ እና ይበልጥም በተዋቡ፣ በክልሉ በሚገኙ አካባቢዎች ውስጥ ገና ድሮ እንዲሰፍሩ የሚያስችል ነው” ብለዋል። ትረምፕ የሚሉት ሥፍራ እዚያው ጋዛ ውስጥ ይሁን እስካሁን ሃሳቡን ባልተቀበሉ ሆነ ሌሎች ሃገራት ዝርዝር አልሰጡም። «በእርግጥ ደስተኛ የመሆን፣ ደህንነታቸው የመረረጋጋጥ እና ነጻ የመሆን እድል ይኖራቸዋል» ሲሉ ጽፈዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሃማስ በትላንትናው እለት ሁሉም ፍልስጤማውያን አንጃዎች ትረምፕ ጋዛን ለመቆጣጠር ያቀረቡትን ሃሳብ በመቃወም ተባብረው እንዲሰሩ ጥሪ አቅርቧል። “ችግሩን ይበልጥ አያባብሱ” - ጉቴሬዥ ‘ችግሩን አናባብስ’ ሲሉ ያሳሰቡትን የመንግሥታቱን ድርጅት ዋና ጸሐፊ ጨምሮ፣ የትረምፕ የጋዛ ውጥን ከዓለም ዙሪያ መጠነ ሠፊ ነቀፌታ ገጥሞታል። «መፍትሄ ፍለጋ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ በማውጣት ችግሩን ይበልጥ ማባባስ የለብንም» ያሉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶንዮ ጉቴሬሽ «ለመሰረታዊው ዓለም አቀፍ ሕጎች ከበሬታ መቆም ያስፈልጋል። ከማንኛውም አይነት የዘር ማጽዳት ድርጊትም መራቅ አስፈላጊ ነው» ብለዋል። አንድን ሕዝብ ከሚኖርበት አካባቢ በኃይል ወደ ሌላ ሥፍራ ማዛወር በዓለም አቀፍ ሕግ በጥብቅ የተከለከለ እና ከዘር ማጽዳት ሊቆጠር የሚችል ድርጊት ነው። የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ዋልተር ሽታይንማየርም ከትላንት በስቲያ ረቡዕ በሰጡት አስተያየት፤ የትራምፕ ዕቅዶች “በአንዳንድ ወገኖች ላይ ጥልቅ ጭንቀት እና አልፎ ተርፎም የመሸበር ስሜት ጭምር ሊቀሰቅሱ የሚችሉ” እናም “በአለም አቀፍ ኅግ ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው” ብለዋል። 22 አባላት ያሉት የአረብ ሊግ በበኩሉ የትራምፕ እቅድ «አለመረጋጋት ሊያስከትል የሚችል» እና ‘የፍልስጤምን ሀገር የመሆን እድልም የማያቃና” ብሎታል። የብሪታንያው ጠቅላይ ሚንስትር ኪር ስታርመርም በተመሳሳይ፤ ፍልስጤማውያን “ወደ ቤታቸው መመለስ ይችሉ ዘንድ መፈቀድ አለበት” ብለዋል። ቀያቸውን መልሰው እንዲገነቡ ሊፈቀድላቸው፤ እኛም በመልሶ ግንባታው እና ‘የሁለት ሃገር መፍትሔ በሚባለው ዕቅድ አብረናቸው ልሆን ይገባል’ ብለዋል። ትረምፕ የጋዛ ባለቤት ስለመሆን የሰነዘሩትን ይህን ሃሳብ ተከትሎም አውስትራሊያ፣ ቻይና፣ ጀርመን፣ አየርላንድ፣ ሩሲያ፣ ሳውዲ አረቢያ እና ስፔን፤ ሁለቱ አገሮች እስራኤል እና ፍልስጤም እንደ ሃገር ጎን ለጎን በሰላም የሚኖሩበትን መንገድ ለመፍጠር የታለመውን ‘የሁለት ሀገራት መፍትሄ’ የተባለ እቅድ መደገፋቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የፍልስጤማውያኑ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስም ‘የመንግስታቱ ድርጅት የፍልስጤምን ህዝብ እና የማይገሰሱ መብቶቹን እንዲያስጠብቅ’ የሚል ጥሪ አሰምተዋል። ትራምፕ ሊያደርጉ ያቀዱት “አለም አቀፍ ህግን በእጅጉ የሚጥስ ነው” ሲሉም ኮንነዋል።

የጅቡቲ መንግሥት በአፋር ክልል ሲያሩ ቀበሌ በድሮን አድርሶታል በተባለው ጥቃት መጎዳታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

የጅቡቲ መንግሥት በአፋር ክልል ሲያሩ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ በድሮን አድርሶታል ያለውን ጥቃት  በጥብቅ እንደሚያወግዙ በአፋር ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲዎ
የአሜሪካ ድምፅ

የጅቡቲ መንግሥት በአፋር ክልል ሲያሩ ቀበሌ በድሮን አድርሶታል በተባለው ጥቃት መጎዳታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ

የጅቡቲ መንግሥት በአፋር ክልል ሲያሩ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ በድሮን አድርሶታል ያለውን ጥቃት  በጥብቅ እንደሚያወግዙ በአፋር ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲዎች አስታወቁ፡፡ የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር እና የአፋር ለዴሞክራሲ እና ፍትሕ ፓርቲ በአወጡት መግለጫ፣ «ድርጊቱ ሰላማዊ ሰዎችን ዒላማ ያደረገ እንዲሁም የሀገር ሉአላዊነትን የተዳፈረ ነው» ሲሉ ወንጅለውታል፡፡ በጥቃቱ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን ዘጠኝ የሚኾኑት ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው መግለጫውን ካወጡት ተፎካካሪ ፓርቲዎች አንደኛው ለአሜሪካ ድምጽ አስታውቋል። በሆስፒታሉ ውስጥ በድሮን ጥቃቱ ጉዳት ደርሶባቸው ህክምና በማግኘት ላይ መሆናቸውን የነገሩን የሲያሩ ቀበሌ ነዋሪዋ ወ/ሮ መሬም መሐመድ ጥቃቱ በድንገት መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ የወ/ሮ መሬም እህትን ጨምሮ ሌሎችም መገደላቸውን የተጎጅዋ ቤተሰብ እንደሆኑ የገለጹልን አብደላ መሐመድ ጠቁመዋል፡፡ በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱት የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር እና የአፋር ለዴሞክራሲ እና ፍትሕ ፓርቲ ትናንት ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም በአወጡት የጋራ መግለጫ የጅቡቲ መንግሥት በአፋር ክልል ኤሊ ደአር ወረዳ ሲያሩ በተባለው ቀበሌ ላይ ፈጽሞታል ያሉትን የድሮን ጥቃት አውግዘዋል፡፡ በአፋር ክልል የሚገኘው የዱብቲ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር ሁሴን አደን በጥቃቱ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታል የመጡና ህክምና በማግኘት ላይ የሚገኙ መኖራቸውን አረጋግጠዋል፡፡  የጅቡቲ የጸጥታ ኃይሎች በበኩላቸው “አሸባሪዎች” ብለው በገለጹት አማጺ ቡድን ላይ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ ባደረጉት የድሮን ድብደባ ስምንት የቡድኑ አባላትን እና ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሲቪሎችን መግደላቸውን ባለሥልጣናቱ እሑድ ዕለት  አስታውቀዋል። አዶራታ በተባለና ከኢትዮጵያ ድንበር ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ስፍራ የድሮን ጥቃቱ እንደተፈጸመ የጅቡቲ የመከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ አመልክቷል። “ስምንት አሸባሪዎች ተገድለዋል” ያለው መግለጫ፣ “ነገር ግን የሃገሪቱ ሲቪል ዜጎችም ሕይወታቸውን አጥተዋል” ብሏል።

የአራት አስርታት የሙዚቃ ዓለም ጉዞ .. የዘፈን ግጥሞች ደራሲው ያየህይራድ አላምረው ሲታወስ

ከሰባዎቹ አጋማሽ ጀምሮ ለበርካታ ዕውቅ ድምጻውያን ሥራዎቹን ሰጥቷል። ከኩኩ ሰብስቤ እስከ አስቴር አወቅ እና ጥላሁን ገሰሰ ቁጥራቸው የበዛ ድምጻውያን ድንቅ
የአሜሪካ ድምፅ

የአራት አስርታት የሙዚቃ ዓለም ጉዞ .. የዘፈን ግጥሞች ደራሲው ያየህይራድ አላምረው ሲታወስ

ከሰባዎቹ አጋማሽ ጀምሮ ለበርካታ ዕውቅ ድምጻውያን ሥራዎቹን ሰጥቷል። ከኩኩ ሰብስቤ እስከ አስቴር አወቅ እና ጥላሁን ገሰሰ ቁጥራቸው የበዛ ድምጻውያን ድንቅ የሙዚቃ ድርሰቶቹን ተጫውተዋል። ታዋቂው የዘፈን ግጥሞች ደራሲ እና ፕሮዲዩሰር ያየህይራድ አላምረው። ሕይወት እና ሥራውን ለመዘከር የተሰናዳውን ቅንብር ከዚህ ይከታተሉ።

«በዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ፕሮግራም መሥሪያ ቤት የተደረጉትን ለውጦች በመቃወም እንታገላለን» ዲሞክራቶች

በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የዲሞክራቲክ ፓርቲ አመራር አባላት፣ የትረምፕ አስተዳደር የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ፕሮግራም መሥሪያ ቤትን (ዩኤስ
የአሜሪካ ድምፅ

«በዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ፕሮግራም መሥሪያ ቤት የተደረጉትን ለውጦች በመቃወም እንታገላለን» ዲሞክራቶች

በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የዲሞክራቲክ ፓርቲ አመራር አባላት፣ የትረምፕ አስተዳደር የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ፕሮግራም መሥሪያ ቤትን (ዩኤስኤአይዲ) በመሳሰሉ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ይዞታ እና አሰራር ላይ እያደረገ ያለውን ለውጥ፣ በመንግሥቱ በጀት ዕቅድ ዙሪያ ከፕሬዝዳንቱ ጋር በሚደረጉ ድርድሮች ወቅት እንደሚጠቀሙበት በመግለጽ አስጠነቀቁ። የአሜሪካ ድምጿ የምክር ቤት ጉዳዮች ዘጋቢ ካትሪን ጂፕሰን ያደረሰችው ዘገባ ነው።

የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች የፀሎት እና የሰላም ጥሪ አቀረቡ 

ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት የሰላም እጦት እንድትወጣ የሃይማኖት አባቶች የፀሎት እና የሰላም ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት አባቶቹ፣ ዛሬ በአዲስ አበባ በተካሔደ
የአሜሪካ ድምፅ

የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች የፀሎት እና የሰላም ጥሪ አቀረቡ 

ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት የሰላም እጦት እንድትወጣ የሃይማኖት አባቶች የፀሎት እና የሰላም ጥሪ አቅርበዋል። የሃይማኖት አባቶቹ፣ ዛሬ በአዲስ አበባ በተካሔደ ዝግጅት ላይ ለተፋላሚ ሃይሎች የሰላም ጥሪ ያቀረቡ ሲኾን፣ የፀሎት አዋጅም አውጀዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሲቪል እና የሙያ ማኅበራት ኮንግረስ አዘጋጅነት ሐሙስ ጥር 29 ቀን በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ በተካሔደ አገራዊ የፀሎት እና የሰላም ጥሪ ዝግጅት ላይ የተገኙ የልዩ ልዩ ቤተ እምነቶች አባቶች ፀሎት ካደረጉ በኋላ ለምዕመናን እና ለተፋላሚ ወገኖች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ

የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ ዕድሜ ጋብቻን ለማስቆም አሁንም የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ የገለፀው የኢትዮጵያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒሰቴር፣ ከተባበሩት
የአሜሪካ ድምፅ

ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ

የሴት ልጅ ግርዛትና ያለ ዕድሜ ጋብቻን ለማስቆም አሁንም የተቀናጀ ስራ እንደሚያስፈልግ የገለፀው የኢትዮጵያ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒሰቴር፣ ከተባበሩት መንግሥታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር ያዘጋጃቸውን ሰነዶች ዛሬ ይፋ አድርጓል ። ጥር 29 ቀን 2017 ዓ/ም ይፋ የተደረጉት ብሔራዊ የዕቅድ ሰነዶች ችግሩን እ.አ. አ. እሰከ 2030 ለመፍታት ያስችላሉ የተባሉ ናቸው። የተፈጥሮ አደጋዎች እና ግጭቶች ታዳጊ ሴቶችን ለተጠቀሱት ችግሮች እያጋለጡ መሆኑን የተናገሩት፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ምኒሰትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ «ትልቁ ነገር ሰላም ላይ መስራት ነው» ብለዋል። ድርጊቶቹ ሰብዓዊ ቀውስ በሌለበት ሁኔታ ውስጥም እየተፈጸሙ ናቸው ያሉት በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ተጠባባቂ ተወካይ ማሪኮ ካጎሺማ፣ ሰነዶቹ የግንዛቤ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያግዙ ጠቅሰዋል።

ከግድያ ሙከራዎች በኋላ ወደ ሃይማኖት መቅረባቸውን ትረምፕ ተናገሩ

ዛሬ በዓመታዊው ‘ብሔራዊ የፀሎትና የቁርስ ሥነ ሥርዐት’ ላይ የተገኙት የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ ከተፈጸመባቸው ሁለት የግድያ ሙከራዎች በኋላ
የአሜሪካ ድምፅ

ከግድያ ሙከራዎች በኋላ ወደ ሃይማኖት መቅረባቸውን ትረምፕ ተናገሩ

ዛሬ በዓመታዊው ‘ብሔራዊ የፀሎትና የቁርስ ሥነ ሥርዐት’ ላይ የተገኙት የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ፣ ከተፈጸመባቸው ሁለት የግድያ ሙከራዎች በኋላ ከሃይማኖት ጋራ ያላቸው ግንኙነት እንደተቀየረ አስታውቀዋል። አሜሪካዊያን “ፈጣሪን መልሠው በሕይወታቸው ውስጥ ያኑሩ” ሲሉ ጥሪ አድርገዋል ትረምፕ። በካፒቶል የሚካሄደውና የሰባ ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠረው ዓመታዊ የፀሎትና የቁርስ ሥነ ሥርዐት የሁለቱም ፓርቲዎች የምክር ቤት ዓባላት የሚሳተፉበት ሃይማኖታዊ ሥነ ስርዓት ነው። “ከሃይማኖት ውጪ፣ ከእምነት ውጪ ደስተኛ መሆን እንደማይቻል አምናለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል ትረምፕ፡፡ ከግድያ ሙከራዎቹ በኋላ ወደ እግዚያብሄር ይበልጥ እንደቀረቡ ያመለከቱት ትረምፕ፣ ጆሯቸውን በጨረፈው ሙከራ ጸጉራቸው እንዳልተነካ ለዚህም ምስጋና ማቅረባቸውን ሲናገሩ ታዳሚውን ፈገግ አሰኝተዋል። ትረምፕና አስተዳደራቸው ከሃይማኖት መሪዎች ጋራ ግጭት ውስጥ ሲገቡ ከዚህ በፊት ተስተውሏል ያለው የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ፣ በባዕለ ሲመታቸው ቀን በተደረገ የቤተ ክርስቲያን ሥነ ሥርዓት ሰባኪው ማሪያን ቡደስ ለስደተኞችና ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ርህራሄ እንዲያሳዩ መጠየቃቸውን ትረምፕ ተቃውመው እንደነበር አመልክቷል። የካቶሊክ እምነት ተከታይ የሆኑት ምክትል ፕሬዝደንት ጄ ዲ ቫንስ ደግሞ የስደተኞችን ጉዳይ በተመለከተ ተመሳሳይ እምነት ካላቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋራ ሳይስማሙ ቀርተዋል።  

አሜሪካ ለውጪ የምትሰጠውን ርዳታ በማቋረጧ በኢትዮጵያ ከኤችአይቪ ጋራ የሚኖሩ ሰዎችን  እንደሚጎዳ ተመድ አስታወቀ

አሜሪካ የውጪ ርዳታዋን ማቁረጧ በኢትዮጵያ በርካታ የልማት ሥራዎችን፣ በተለይም ደግሞ ከኤችአይቪ ጋራ የሚኖሩ ሰዎችን ለመርዳት የሚደረገውን ጥረት እንደሚጎ
የአሜሪካ ድምፅ

አሜሪካ ለውጪ የምትሰጠውን ርዳታ በማቋረጧ በኢትዮጵያ ከኤችአይቪ ጋራ የሚኖሩ ሰዎችን  እንደሚጎዳ ተመድ አስታወቀ

አሜሪካ የውጪ ርዳታዋን ማቁረጧ በኢትዮጵያ በርካታ የልማት ሥራዎችን፣ በተለይም ደግሞ ከኤችአይቪ ጋራ የሚኖሩ ሰዎችን ለመርዳት የሚደረገውን ጥረት እንደሚጎዳ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤች አይ ቪ ኤድስ ፕሮግራም (ዩኤሴይድስ) አስታውቋል። በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከኤችአይቪ ጋራ የሚኖሩ የ503 ሺሕ ሰዎች በ1ሺሕ 400 ጤና ጣቢያዎች በኩል አንቲሪትሮቫይራል የተሰኘው መድኃኒት እንደሚሰጣቸው የተመዱ የኤድስ ፕሮግራም አስታውቃል። በክልሎች የሚገኙ የጤና ባለሥልጣናት በአሜሪካው ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤሴይድ) እና በአሜሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ ማዕከል (ሲዲሲ) የገንዘብ ድጋፍ የሚሠሩ የጤና ሠራተኞችን እንዲያሰናብቱ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መመሪያ እንደደረሳቸው ለቪኦኤ አስታውቀዋል። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከቪኦኤ አስተያየት እንዲሰጥ ተጠይቆ መልስ አልሰጠም። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ለውጪ ሃገራት የሚሰጥ ርዳት እንዲቋረጥ ማዘዛቸውን ተከትሎ፣ የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤችአይቪን ጨምሮ ሌሎችም ሕይወት አድን ፕሮግራሞችን አሜሪካ መደገፍ እንደሚቀጥል አስታውቆ ነበር። የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ምኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ርዳታ እንደሚቀጥል ቀደም ብለው አስታውቀው የነበረ ሲሆን፣ ቆየት ብለው ደግሞ ደግሞ ሕይወት አድን መድሃኒቶችና የሕክምና አገልግሎቶች እንዲሁም የምግብና የመጠለያ ርዳታዎች እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

ናይጄሪያ በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ እግድ ምክንያት የሚደርሱ ተፅእኖዎችን ለመቅረፍ የሚያስችል ርምጃ ይፋ አደረገች

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለውጪ ሀገራት የሚሰጡ የገንዘብ ድጋፎችን ለ90 ቀናት ማገዳቸውን ተከትሎ፤ የናይጄሪያ ባለሥልጣናት የዩናይትድ ስ
የአሜሪካ ድምፅ

ናይጄሪያ በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ እግድ ምክንያት የሚደርሱ ተፅእኖዎችን ለመቅረፍ የሚያስችል ርምጃ ይፋ አደረገች

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለውጪ ሀገራት የሚሰጡ የገንዘብ ድጋፎችን ለ90 ቀናት ማገዳቸውን ተከትሎ፤ የናይጄሪያ ባለሥልጣናት የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ /ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ/ ድጋፍ ይንቀሳቀሱ ለነበሩ የጤና ፕሮግራሞች የሽግግር እና ዘላቂ እቅድ የሚያዘጋጅ ኮሚቴ አቋቁመዋል። የተለያዩ ሚኒስትሮች የተካተቱበት ኮሚቴም ወሳኝ የኾኑ የጤና ፕሮግራሞች አዲስ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እየሠራ ይገኛል። ቲሞቲ ኦቢየዙ በዚህ ዙሪያ ከአቡጃ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

በስዊድን አንድ ግለሰብ ት/ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ 11 ሞቱ

በስዊድን አንድ ግለሰብ በጎልማሶች ትምህርት ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ ግለሰቡን ጨምሮ 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ ሌሎች አምስት  ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ተጎድተዋ
የአሜሪካ ድምፅ

በስዊድን አንድ ግለሰብ ት/ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ 11 ሞቱ

በስዊድን አንድ ግለሰብ በጎልማሶች ትምህርት ቤት ውስጥ በከፈተው ተኩስ ግለሰቡን ጨምሮ 11 ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ ሌሎች አምስት  ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ተጎድተዋል ተብሏል። ፖሊስ ግለሰቡ ድርጊቱን ለብቻው መፈጸሙን ገልጾ፣ የትምህርት ቤቱ ተማሪ ይሆን እንደሁ ወይም ምን እንዳነሳሳው አላሳወቅም። የጅምላ ግድያው በስዊድን ታሪክ የከፋው እንደሆነ ተነግሯል። ግድያው የተፈጸመው ከስቶክሆልም ወጣ ብሎ በሚገኝና ለጎልማሶች የአንደኛና የሁለተኛ ደርጃ ትምህርት እንዲሁም ለስደተኞችና ለሌሎችም የቋንቋና የሙያ  ትምህርት በሚስጥበት  ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው። ስዊድን ውስጥ በትምህርት ተቋማት በመሣሪያ የሚፈጸም ግድያ እምብዛም አይስተዋልም።

«ዩናይትድ ስቴትስ በጦርነት የዳሸቀቸውን ጋዛን ትይዛለች» ፕሬዝደንት ትረምፕ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በጦርነት የዳሸቀችውን ጋዛን በባለቤትነት እንድትረከብ እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ይህ ሐሳባ
የአሜሪካ ድምፅ

«ዩናይትድ ስቴትስ በጦርነት የዳሸቀቸውን ጋዛን ትይዛለች» ፕሬዝደንት ትረምፕ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በጦርነት የዳሸቀችውን ጋዛን በባለቤትነት እንድትረከብ እንደሚፈልጉ ተናገሩ። ይህ ሐሳባቸው  ታዲያ፤  የጋዛን ነዋሪዎች፣ ዮርዳኖስ እና ግብጽን ጨምሮ በሌሎች ሀገሮች  እንዲሰፍሩ ለማድረግ እቅድ አንዳላቸው ከአሁን ቀደም ከተናገሩትም ገፋ ያለ ነው፡፡ ፕሬዝደንት ትረምፕ ይህንን ሐሳባቸውን የገለጹት ትላንት ማክሰኞ ማታ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን ተቀብለው ባስተናገዱበት ወቅት ነው፡፡  የአሜሪካ ድምጽ የኋይት ሐውስ ዋና ዘጋቢ ፓትሲ ዊዳኩስዋራ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

“አሜሪካ ጋዛን በባለቤትነት መያዝ ትሻለች” ትረምፕ

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ አሜሪካ ጋዛን በባለቤትነት መቆጣጠር እንደምትሻ አስታውቀዋል።  ከዚህ ቀደም ፕሬዝደንቱ ጦርነት ባፈራረሳት ሰርጥ ውስጥ የሚኖሩ ፍ
የአሜሪካ ድምፅ

“አሜሪካ ጋዛን በባለቤትነት መያዝ ትሻለች” ትረምፕ

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ አሜሪካ ጋዛን በባለቤትነት መቆጣጠር እንደምትሻ አስታውቀዋል።  ከዚህ ቀደም ፕሬዝደንቱ ጦርነት ባፈራረሳት ሰርጥ ውስጥ የሚኖሩ ፍልስጤማውያን ወደ ጎረቤት ጆርዳን እና ግብጽ ሄደው እንዲሰፍሩ ሐሳብ አቅርበው ነበር። የፍልስጤም ራስ ገዝ፣ ግብጽ፣ ሳዑዲ አረቢያና ሌሎችም የአሜሪካ ሸሪኮችም ሆነ ወዳጅ ያልሆኑ ሃገራት የትረምፕን ሃሳብ ተቃውመዋል። “ያነጋገርኳቸው ሰዎች በሙሉ አሜሪካ ጋዛን በባለቤትነት ትያዝ የሚለውን ሐሳብ ወደውታል። ድንቅ የሆነውን ሥፍራ በማልማትም በሺሕ የሚቆጠር የሥራ ዕድል ይፈጠራል” ብለዋል ትረምፕ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ምኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋራ በመሆን ዋሽንግተን ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ። ኔታንያሁ በበኩላቸው ዋናው ግባቸው ሐማስ በእስራኤል ላይ ስጋት ማረጋገጥ ቢሆንም፣ “ትረምፕ ደግሞ ግቡን ከፍ አድርገውታል” ብለዋል። “ታሪክን የሚቀይር ይመስለኛል፣ ይህን መንገድ መከተል ጠቃሚ ነው” ሲሉም ተደምጠዋል ኔታንያሁ። በ15 ወራት ጦርነት የፈረሰውን ሥፍራ ለመቆጣጠር ያላቸውን ዕቅድ ዝርዝር ትረምፕ አላሳወቁም። የአሜሪካ ወታደሮችን መላክም ከአማራጮች ዝርዝር ውስጥ አለመውጣቱን ትረምፕ አስታውቀዋል። “አስፈላጊ ከሆነ እናደርገዋለን። ያንን ሥፍራ ይዘን እናለማዋለን” ብለዋል ትረምፕ፡፡

ለኤች አ ይቪ ሕክምና የሚሰጥ ርዳታ እንደማይቋረጥ አሜሪካ አስታወቀች

አሜሪካ ለ90 ቀናት የውጪ ርዳታ እንደሚቋረጥ ብታስታወቅም፣ ‘የፕሬዝደንቱ የኤድስ አስቸኳይ ጊዜ ርዳታ’ ወይም ‘ፔፕፋር’ በሚባል የሚታወቀው ፕሮግራም እንደማ
የአሜሪካ ድምፅ

ለኤች አ ይቪ ሕክምና የሚሰጥ ርዳታ እንደማይቋረጥ አሜሪካ አስታወቀች

አሜሪካ ለ90 ቀናት የውጪ ርዳታ እንደሚቋረጥ ብታስታወቅም፣ ‘የፕሬዝደንቱ የኤድስ አስቸኳይ ጊዜ ርዳታ’ ወይም ‘ፔፕፋር’ በሚባል የሚታወቀው ፕሮግራም እንደማይቋረጥ ታውቋል። ፔፕፋር በዓለም መሪ የሆነ በኤድስ ላይ የሚሠራ ፕሮግራም ሲሆን፣ ሕይወት አድን ፕሮግራሞች እንዲቀጥሉ በመወሰኑ የ90 ቀናት እገዳው እንደማይመለከተው ታውቋል። ፕሬዝደንት ትረምፕ ሥልጣኑን ደግመው በተረከቡ በሰዓታት ውስጥ ነበር “አሜሪካ ትቅደም” ከሚለው የውጪ ፖሊሲያቸው ጋራ የሚጣጣሙ መሆናቸው እስከሚጣራ ለውጪ ሃገራት የሚሰጡ ዕርዳታዎች ለ90 ቀናት እንዲቆሙ ያዘዙት፡፡ የአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ምኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ዕርዳታ እንደሚቀጥል ቀደም ብለው አስታውቀው የነበረ ሲሆን፣ ቆየት ብለው ደግሞ ደግሞ ሕይወት አድን መድሃኒቶችና የሕክምና አገልግሎቶች እንዲሁም የምግብና የመጠለያ ዕርዳታዎች እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። በዓለም በኤች አይ ቪ ከተያዙት ከሁለት ሶስተኛ በላይ ወይም ከ20 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቂዎች በፔፕፋር ፕሮግራም በቀጥታ የሚረዱ መሆኑም ታውቋል።

ከቻይና የሚላኩ ጥቅሎችን ለደንበኞች ማድረሱን እንደሚቀጥል የአሜሪካው የፖስታ አገልግሎት አስታወቀ

የአሜሪካ የፖስታ አገልግሎት ከቻይና እና ከሆንግ ኮንግ የሚላኩ ጥቅሎችን ለጊዜው መቀበል ማቆሙን ትላንት ማክሰኞ አስታውቆ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ባወጣው መግለ
የአሜሪካ ድምፅ

ከቻይና የሚላኩ ጥቅሎችን ለደንበኞች ማድረሱን እንደሚቀጥል የአሜሪካው የፖስታ አገልግሎት አስታወቀ

የአሜሪካ የፖስታ አገልግሎት ከቻይና እና ከሆንግ ኮንግ የሚላኩ ጥቅሎችን ለጊዜው መቀበል ማቆሙን ትላንት ማክሰኞ አስታውቆ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ደግሞ ወደ ደንበኞች የሚላኩ ጥቅሎች መቋረጥ እንዳይከሰት ከጉምሩክና ድንበር ባለሥልጣን ጋራ አዲሱን ታሪፍ ተግባራዊ የሚያደርግበትን መንገድ መላ እንደሚዘይድ አስታውቋል። የፖስታ ቤቱ የማክሰኞ እርምጃ የመጣው እንደ ቴሙ እና ሺኢን የመሰሉ የኢንተርኔት መገበያያዎች አነስተኛ ጥቅሎችን ከቀረጥ ነጻ የሚያስገቡበትን ደንብ ፕሬዝደንት ትረምፕ መሻራቸውን  ተከትሎ ነው። ፕሬዝደንቱ በቻይና ላይ የጣሉት ተጨማሪ 10 በመቶ ታሪፍ ከትላንት ማክሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል። ቀደም ሲል የነበረው ደንብ አሜሪካውያን ከ$800 ዶላር በታች ከውጪ ለሚገዙት ዕቃ ታሪፍ እንዲከፍሉ አያስገድድም። ፕሬዝደንት ትረምፕ ቻይና 10 በመቶ ተጨማሪ ታሪፍ እንድትከፍል እንዲሁም አነስተኛ ጥቅሎችም ታሪፍ እንዲጣልባቸው ያዘዙት፣ የቻይና ሸቀጥ አቅራቢዎች አጋጣሚውን በመጠቀም ፈንትነል የተሰኘውን አደገኛ መድሃኒት መቀመሚያ ኬሚካሎች በሌሎች ሸቀጦች ስም ወደ አሜሪካ ይልካሉ በሚል ነው። በተጨማሪም ቤጂንግ ወደ አሜሪካ የሚላከውን የፈንትነልን ዝውውር አትቆጣጠርም በሚልም ነው።  

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት በመላው ዓለም የሚገኙ ሠራተኞቹን አሰናበተ

የትረምፕ አስተዳደር በመላው ዓለም የሚገኙ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ሠራተኞች ሥራ እንዲያቆሙ አዟል። ላለፉት ስድሳ ዓመታት በመ
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት በመላው ዓለም የሚገኙ ሠራተኞቹን አሰናበተ

የትረምፕ አስተዳደር በመላው ዓለም የሚገኙ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) ሠራተኞች ሥራ እንዲያቆሙ አዟል። ላለፉት ስድሳ ዓመታት በመላው ዓለም ረሃብን በማስወገድ እና ለትምህርት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ በመስጠት የአሜሪካንን ደኅንነት ሲያስጠብቅ የከረመው ድርጅት የመዘጋት ዕጣ ገጥሞታል። የትረምፕ አስተዳደር ለአሜሪካ ዓለም አቀፍ ልማት ድርጅት ሠራተኞች በኢሜይል በላከውና እና በድርጅቱ ድህረ ገጽ ላይ ባሠፈረው መልዕክት ነው ውሳኔውን ያስታወቀው። የትረምፕ አስተዳደር ባለሥልጣኖች እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን ቁጥር እና ሠራተኞችን ለመቀነስ የተቋቋመውንና ‘ዶጅ’ በመባል የሚታወቀውን ቡድን የሚመሩት ኢላን መስክ የዕርዳታ ድርጅቱ ለውጪ ሃገራት የሚያውለውን ገንዘብ እንደ ብክነት እንደሚቆጥሩት ተመልክቷል። ትዕዛዙ ከዓርብ እኩለ ሌሊት በፊት ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ከሚፈለጉ ሠራተኞች ውጪ በመላው ዓለም የሚገኙ ሌሎች የድርጅቱ ሠራተኞች ወደ አሜሪካ ለመመለስ 30 ቀናት ተሰጥቷቸዋል። ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ከሚፈለጉ ኮንትራክተሮች ውጪ ሥራቸውን እንዲያቆሙ እንደሚነገራቸውም ታውቋል። የተቀረው የድርጅቱ ሥራም በአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሥር እንዲጠቃለል እንደሚደረግ ታውቋል። ትረምፕ ለውጪ የሚሰጥ ርዳታ እንዲቆም ማድርጋቸውን ተከትሎ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የድርጅቱ የሀገር ውስጥ ተቀጣሪዎች ተባረው ፕሮግራሞቹም እንዲቆሙ ተደርጓል።

ሜታ መረጃ የማጣራት ስራ ማቋረጡ ስጋት ፈጥሯል

የፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ትሬድ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የሚያስተዳድረው ግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሜታ፤ በማህበራዊ የትስስር ገጾቹ ላይ የሚተላለፉ ሀሰተኛ
የአሜሪካ ድምፅ

ሜታ መረጃ የማጣራት ስራ ማቋረጡ ስጋት ፈጥሯል

የፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ትሬድ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የሚያስተዳድረው ግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሜታ፤ በማህበራዊ የትስስር ገጾቹ ላይ የሚተላለፉ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመቀነስ ከሶስተኛ ወገን ተቋማት ጋር በመተባበር ያካሂድ የነበረውን የመረጃ ማጣራት ስራ ማቋረጡ ሀሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች በስፋት እንዲሰራጭ ያደርጋል ሲሉ ተቺዎች ተናግረውል። በአሁኑ ወቅት ውሳኔው በአሜሪካ ውስጥ ብቻ ተግባራዊ እንደሚደረግ ለአሜሪካ ድምፅ የገለጸው ፌስቡክ በበኩሉ፣ ከአሜሪካ ውጪ ወዳሉ ሀገራት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ተቋሙ የሚኖሩበትን ግዴታዎች በጥንቃቄ እንደሚያጠና ገልጿል። (ዝርዝሩን ከተያያዘው የቪዲዮ ዘገባ ያገኛሉ)

ለጊዜው የተገታው አዲስ ቀረጥ

አሜሪካ በካናዳ እና ሜክሲኮ ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ለመጫን መወሰኗ እና ሁለቱ ሃገራትም በምላሹ ተመሳሳይ ርምጃ እንደሚወስዱ ማስታወቃቸው፣ እንዲሁም ቀድሞውንም
የአሜሪካ ድምፅ

ለጊዜው የተገታው አዲስ ቀረጥ

አሜሪካ በካናዳ እና ሜክሲኮ ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ለመጫን መወሰኗ እና ሁለቱ ሃገራትም በምላሹ ተመሳሳይ ርምጃ እንደሚወስዱ ማስታወቃቸው፣ እንዲሁም ቀድሞውንም በቻይና ላይ ተጭኖ የነበረውን 10 በመቶ ታሪፍ ጨምሮ፣ በዓለም የንግድ ጦርነትና የኢኮኖሚ ቀውስ ይከሰታል የሚል ከፍተኛ ስጋት አሳድሮ ነበር። ፕሬዝደንት ትረምፕ አዲሱ ደንብ ተግባራዊ ከመሆኑ አንድ ቀን ቀደም ብሉ፣ ከካናዳ እና ከሜክሲኮ መሪዎች ጋራ መነጋገራቸውን ተከትሎ፣ ነገሮች ወደነበሩበት የተመለሱ መስለዋል። ትረምፕ ከመሪዎቹ ጋራ ከተነጋገሩ በኋላ ሁኔታዎችን ለማጤን ተጨማሪ 30 ቀናት እንደሚወስዱ አስታውቀዋል። ካናዳን በተመለከተ በሰሜኑ የአሜሪካ ድንበር ላይ ቁጥጥር ለማድረግ መስማማቷን፣ በአሜሪካ የበርካቶችን ሕይወት በመቅጠፍ ላይ ያለውና ፈንትነል የተሰኘው ሱስ አሲያዥ መድኃኒት በሕገ ወጥ መንገድ የሚገባበትን ሁኔታ ለማስቆም፣ ለዚህም 1.3 ቢሊዮን ዶላር በመመደብ እንድሚንቀሳቀሱ የካናዳው ጠቅላይ ምኒስትር ጀስቲን ትሩዶ መስማማታቸውን ትረምፕ አስታውቀዋል። በአዲስ ሄሎኮፕተሮች፣ ቲክኖሎጂ እና የሰው ኅይል በመታገዝና ከአሜሪካ ጋራ በመተባበር የፈንትነል ዝውውርን ለመግታት እንደሚሰሩም ተስማምተዋል። 10 ሺሕ የሚሆን የሰው ኃይል እንደምታሰማራና የፈንትነል ጉዳይ አማካሪ በመሾም ለ24 ሰዓታት ድንበሩን እንደምትቆጣጠር እንዲሁም የአደንዛዥ ዕጽ አዘዋዋሪዎችንም በሽብርተኝነት እንደምትፈርጅ ካናዳ ተስማምታለች ተብሏል፡፡ በተመሳሳይም ከሜክሲኮ ፕሬዝደንት ክላውዲያ ሼይንቦም ጋራ በተደረገው ውይይት፣ 10ሺሕ ወታደሮችን በድንበር ላይ ለማሰማራት ፕሬዝደንቷ መስማማታቸውን እነዚህም ወታደሮች የፈንትለልና የሕገ ወጥ ፍልሰተኞችን ዝውውርን ለመቆጣጠር እንደሚሰሩ ትረምፖ አመልክተዋል። በውይይቶቹም በካናዳ እና ሜክሲኮ ላይ ሊጣል የነበረው 25 በመቶ ታሪፍ፣ እንዲሁም ሃገራቱ በአጸፋው በአሜሪካ ላይ ሊጥሉት የነበረው ተመሳሳይ የታሪፍ መጠን ለጊዜው ለሰላሳ ቀናት ያህል እንዲቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል። በቻይና በኩል ያለው የንግድ ውዝግብና የታሪፍ ጭመራ ግን እንደቀጠለ ነው። ቻይና ለፕሬዝደንት ትረምፕ የታሪፍ እርምጃ አጸፋ ሰጥታለች፡፡ የህም ከአሜሪካ በሚገቡ በርካታ ሸቀጦች ላይ የሚጣል ሲሆን፣ በተለይም በተፈጥሮ ጋዝ ውጤቶች ላይ 15 በመቶ፣ በድፍድፍ ነዳጅ ላይ ደግሞ የ10 በመቶ ታሪፍ እንደምትጭን አስታውቃለች፡፡ አዲሱ የታሪፍ እርምጃም ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ቻይና አስታውቃለች። “የአሜሪካ የታሪፍ ጭማሪ ከዓለም ንግድ ድርጅት ደንቦችን የጣሰ እንደሆነ” ያስታወቀችው ቻይና “በአሜሪካ የሚይታዩ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለፍታት የማይጠቅም” ብቻ ሳይሆን፣ በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚና የንግድ ትብብር የሚጎዳ እንደሆነ ገልጻለች፡፡ በተጨማሪም የአሜሪካንን የታሪፍ ጭማሪ በተመለከተ በዓለም የንግድ ድርጅት መድረክ ላይ እንደምትሞግት ቻይና አስታውቃለች፡፡  

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በትግራዩ ውጥረት ዙሪያ የሰጡት አስተያየት 

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በትግራይ ክልል የፖለቲካ ኃይሎች መካከል በቀጠለው የፖለቲካ ልዩነት ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ አስተያየት ሰጡ። በዛ
የአሜሪካ ድምፅ

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በትግራዩ ውጥረት ዙሪያ የሰጡት አስተያየት 

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በትግራይ ክልል የፖለቲካ ኃይሎች መካከል በቀጠለው የፖለቲካ ልዩነት ዙሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ አስተያየት ሰጡ። በዛሬው ዕለት በፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ "የትግራይ የፖለቲካ መሪዎች እና ልሂቃን የውስጥ ልዩነቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ’ ሲሉ ጥሪ ያሰሙት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ፣ ከሌሎች ክልሎች ይሁን ከፌዴራል መንግሥቱ ጋር የሚነሱ ማናቸውም ልዩነቶች የሃገሪቱ ሕገ መንግሥት በሚያዘው መሠረት ሊፈቱ ይገባል’ ብለዋል። የትግራዩ የፖለቲካ አለመግባባት በቅርቡ አንዳንድ የክልሉ የጦር አዛዦች ድጋፋቸውን ለሕወሐት ሊቀ መንበር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከገለጹ በኋላ ከክልሉ ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ጋራ የገቡት ብርቱ የፖለቲካ ውዝግብ ተባብሶ መቀጠሉ ተዘግቧል። የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ የክልሉ ምክር ቤት  ከተበተነ ከዓመታት በኋላ በትላንትናው ዕለት አማካሪ ምክር ቤት ተመስርቷል። የአማካሪው ምክር ቤት ፕሬዝዳንቱን ከመሰየም በመለስ የክልል ምክር ቤቱን ሥራ እንደሚሠራ ተገልጿል። እርምጃውን የተቃወሙት የሕወሐት መሪ አማካሪ ጉባኤውን ድርጅታቸውን ለመበተን የታለመ ሲሉ ተከራክረዋል። ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ የትግራይ ሕዝብ “የትላንት ቁስሉ ሳይጠግ፣ አሁንም በፍርሃት እና በተሸበረ ሥሜት እንዳለ ነው” ብለዋል።

የትረምፕ አስተዳደር በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ ስለሚጣለው ታሪፍ አስፈላጊነት ማስረዳቱን ቀጥሏል

የትረምፕ አስተዳደር በካናዳ፣ ቻይና እና ሜክሲኮ ላይ ለምን ታሪፍ መጣል አስፈላጊ እንደሆነ በሳምቱ መጨረሻም ክርክሩን ማቅረብ ቀጥሎ ነበር። ሶስቱ ሃገራት የ
የአሜሪካ ድምፅ

የትረምፕ አስተዳደር በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ ስለሚጣለው ታሪፍ አስፈላጊነት ማስረዳቱን ቀጥሏል

የትረምፕ አስተዳደር በካናዳ፣ ቻይና እና ሜክሲኮ ላይ ለምን ታሪፍ መጣል አስፈላጊ እንደሆነ በሳምቱ መጨረሻም ክርክሩን ማቅረብ ቀጥሎ ነበር። ሶስቱ ሃገራት የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስዱ አስታውቀው፣ ነገር ግን ከአሜሪካ ጋር ለመነጋገርና ለመተባበር በራቸው ክፍት እንደሆነ ገልጸዋል። ዛሬ ጠዋት ላይ ደግሞ ዶናልድ ትረምፕ ከካናዳው ጠቅላይ ምኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋራ መነጋገራቸውን አስታውቀዋል። ዶናልድ ትረምፕ “ትሩዝ ሶሻል” በተወሰኘው ማኅበራዊ መድረክ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ እኩለ ቀን ላይም ከትሩዶ ጋራ ለመነጋገር ቀጠሮ እንደያዙ አስታውቀው፣ አዲስ ታሪፍ በካናዳ ላይ የጣሉት በአሜሪካ የበርካቶችን ሕይወት በመቅጠፍ ላይ የሚገኘውን ፈንትነል የተሰኘው ሱስ አሲያዥ መድሃኒት በሕገ ወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ መግባቱን ለመከላከል ካናዳ ተጨማሪ ጥረት እንድታደርግ ጫና ለመፍጠር መሆኑን አስታውቀዋል። ትረምፕ በተጨማሪም ከሜክሲኮ ፕሬዝደንት ክላውዲያ ሼይንባውም ጋራ ለመነጋገር ዕቅድ እንዳላቸው አስታውቀዋል። ቬሮኒካ ባልዴራስ ኤግሌሲያስ የላከችው ዘገባ ነው።

በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ህይወት የቀየረው የባህርዳሩ ግሬስ ማዕከል

ከ20 አመት በፊት በአማራ ክልል፣ ባህርዳር ከተማ ውስጥ የተመሰረተው ግሬስ ፋውንዴሽን ማዕከል አሳዳጊ አልባ ኾነው ተጥለው የተገኙ ጨቅላ ህፃናትን ሰብስቦ በማሳ
የአሜሪካ ድምፅ

በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ህይወት የቀየረው የባህርዳሩ ግሬስ ማዕከል

ከ20 አመት በፊት በአማራ ክልል፣ ባህርዳር ከተማ ውስጥ የተመሰረተው ግሬስ ፋውንዴሽን ማዕከል አሳዳጊ አልባ ኾነው ተጥለው የተገኙ ጨቅላ ህፃናትን ሰብስቦ በማሳደግ እና የቀን ስራ እየሰሩ ኑሯቸውን ለሚገፉ እናቶች ልጆቻቸውን በመያዝ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል። የዚህ ተቋም መስራች አሜሪካዊቷ ሜርሲ ኤሪክሰን ስትሆን ምህረት በሚለው ስሟ ኢትዮጵያዊ ስሟ ትታወቃለች። በዚህ ተቋም ስራዋ አማካኝነት ከተዋወቀችው የትዳር አጋሯ ሰፊነው ብርሃን ጋር በመሆን በገነቡት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ከ800 በላይ ልጆችን ተቀብለው እያስተማሩ ነው። ስመኝሽ የቆየ ከምህረት እና ሰፊነው ጋር ያደረገችውን ቆይታ ከተያያዘው ቪዲዮ ያገኛሉ።

ትረምፕ አዲስ የቀረጥ ክፍያ የጣሉባቸውን የካናዳን እና የሜክሲኮን መሪዎችን ሊነጋገሩ ነው

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከሁለቱ ጎረቤቶቻቸው ካናዳ እና ሜክሲኮ፣ እንዲሁም ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ከጣሉ እና በምላሹ
የአሜሪካ ድምፅ

ትረምፕ አዲስ የቀረጥ ክፍያ የጣሉባቸውን የካናዳን እና የሜክሲኮን መሪዎችን ሊነጋገሩ ነው

የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ከሁለቱ ጎረቤቶቻቸው ካናዳ እና ሜክሲኮ፣ እንዲሁም ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ ቀረጥ ከጣሉ እና በምላሹ ሁለቱ አገሮች በዩናይትድ ስቴትስ ላይ የአጻፋ ቀረጥ መጣላቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ከመሪዎቹ ጋር ለመነጋገር ማቀዳቸውን አመለከቱ። ትረምፕ በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው ከካናዳ እና ሜክሲኮ ጋር ተደራድረው ‘ነጻ-የንግግድ ስምምነት’ ተግባራዊ ቢያደርጉም፤ ከነገ ማክሰኞ አንስቶ ተፈጻሚ የሚሆን አዲስ የሃያ አምስት በመቶ ቀረጥ ሲጥሉባቸው፤ በቻይና ላይ ደግሞ ቀደም ሲል ከተደነገገው በተጨማሪ የአሥር በመቶ ቀረጥ ጥለዋል። ትረምፕ ሕገ-ወጥ ፍልሰትን ለማስቆም እና ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ለብዙዎች ህልፈት ምክኒያት የሆነው ‘ፌንቲኔል’ የተባለ አደገኛ መድሃኒት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ለመከላከል በቂ ጥረት አላደረጉም’ ሲሉ ሦስቱን ሃገራት ከሰዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዶናልድ ትረምፕ ትላንት ዕሁድ ማለዳ ላይ ‘ትሩዝ ሶሻል’ በተባለው የራሳቸው የማኅበራዊ ሚዲያ አውታር ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ በቀረጥ ጭማሪዎቹ የተነሳ አሜሪካውያን ሸማቾች ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ጭማሪ ሊገጥማቸው እንደሚችል አምነዋል። በሌላ በኩል ለፌዴራል መንግሥት ተጨማሪ ቀረጥ የሚከፍሉ የአሜሪካ ኩባንያዎች ከሌሎች ሃገራት ለሚያስገቧቸው የተለያዩ ምርቶች እና ሸቀጦች የሚጠየቁትን ተጨማሪ ወጭ ሙሉውን አለያም የሚበዛውን ወደሸማቹ ያሳፋሉ። “በአዲሱ ቀረጥ የተነሳ ጥቂት ቆንጠጥ የሚያደርግ ሕመም ሊኖር ይችላል?” ሲሉ ትረምፕ ራሳቸው ለሰነዘሩት ጥያቄ ሲመልሱ፡ “አዎን! ምናልባት! ሊኖርም ላይኖርም ይችላል! ነገር ግን አሜሪካን ዳግም ታላቅ እናደርጋለን። እናም ቢከፍሉት የማያስከፋ ዋጋ ይሆናል" ብለዋል።

የመንግስታቱ ድርጅት በኮንጎ ጾታዊ ጥቃት እንደጦር መሳሪያ ጥቅም ላይ ውሏል ሲል አስታወቀ

በምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤም 23 አማፂያን እና በኮንጎ የታጠቁ ወታደሮች መካከል ውጊያው እየተባባሰ በመጣበት ወቅት፤ ተፋላሚዎቹ ወገኖች አስገድ
የአሜሪካ ድምፅ

የመንግስታቱ ድርጅት በኮንጎ ጾታዊ ጥቃት እንደጦር መሳሪያ ጥቅም ላይ ውሏል ሲል አስታወቀ

በምሥራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኤም 23 አማፂያን እና በኮንጎ የታጠቁ ወታደሮች መካከል ውጊያው እየተባባሰ በመጣበት ወቅት፤ ተፋላሚዎቹ ወገኖች አስገድዶ መድፈርን እና ጾታዊ ጥቃትን እንደ ጦርነት መሳሪያ ጥቅም ላይ እያዋሉት መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት ሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ፅህፈት ቤት አስጠንቅቋል። የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዋና ሃላፊ ቮልከር ተርክ ቃል አቀባይ የሆኑት ጀርሚ ላውረንስ ሁኔታው “ከግጭት ጋር ተያይዞ ለብዙ አስርት ዓመታት በኮንጎ ታጣቂዎች እየፈጸሙት ያለ ነገር ነው” ብለዋል፡፡ ከፍተኛ ኮሚሽነሩ በተለይም የቅርብ ጊዜው ግጭት “ከግጭት ጋር የተያያዘውን የጾታ ጥቃት የበለጠ ሊያባብሰው ይችላል” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። በግጭቱ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት፣ የኤም 23 አማፂያን እና ሩዋንዳ በአካባቢው ላለው ቀውስ እርስ በራሳቸው እየተወነንጃጀሉ ነው።

ትራምፕ እና ኔታኒያሁ በጋዛ፣ በኢራን እና በአረብ ሀገራት ጉዳዮች ላይ ሊወያዩ ነው

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የፊታችን ማክሰኞ ከዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር፤ በዋይት ሀውስ ሲገናኙ፤ የኢራን ጥቃት
የአሜሪካ ድምፅ

ትራምፕ እና ኔታኒያሁ በጋዛ፣ በኢራን እና በአረብ ሀገራት ጉዳዮች ላይ ሊወያዩ ነው

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የፊታችን ማክሰኞ ከዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር፤ በዋይት ሀውስ ሲገናኙ፤ የኢራን ጥቃትን በመቃወም፣ ከአረብ ሀገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በማስፋፋት እንዲሁም ሀገራቸው «በሀማስ ላይ ድል» ስለማድረጓ እንደሚወያዩ በዛሬው ዕለት ተናግረዋል ። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሁለት ሳምንት በፊት ለሁለተኛ ጊዜ ለቀጣዩ አራት ዓመታት ሀገሪቱን ለመምራት ሥልጣን ከተረከቡ በኋላ የሚያገኟቸው የመጀመሪያው የውጭ ሀገር መሪ ቀዳሚው ኔታንያሁ ሊሆኑ ነው። ትራምፕ እና ኔታንያሁ የረዥም ጊዜ አጋሮች ሲሆኑ፤ ፕሬዝዳንቱ  የመካከለኛው ምሥራቅ መልዕክተኛውን ስቲቭ ዊትኮፍን ልከው እስራኤል ከሃማስ ጋር በከፈተችው ጦርነት እና በእስረኞች መካከል ያለውን ልውውጥ፤ የስድስት ሳምንት የተኩስ አቁም በማድረግ እንዲያደራድሩም በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል። ምንም እንኳን የሃማስ ታጣቂዎች በእስራኤል ተይዘው የነበሩትን በመቶዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤም እስረኞች ለውጥ 18 ታጋቾችን ነጻ ቢለቁም፣ ሁለተኛው የእርቁ ሂደት ከፍተኛ ተግዳሮት ገጥሞታል። እስራኤል ይህ እንዲሆን አልፈቅድም ብላ ብትናገርም፤  የተኩስ አቁም ስምምነቱ ከተደረገበት ከባለፈው ወር አንስቶ በዩናይትድ ስቴትስ አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው የሃማስ ቡድን ሙሉ ለሙሉ በድጋሚ ጋዛን በቁጥጥሩ ስር ማድረጉን አረጋጧል። ይህን ተከትሎ፤ ጦርነቱ ሙሉ ለሙሉ ሳይቆም እና የእስራኤል ጦር በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ካለው ጠባብ የጋዛ ሰርጥ ክፍል በሙሉ ለቆ ሳይወጣ በሁለተኛው የእርቅ ሂደት ነፃ ሊወጡ የታቀዱ ተጨማሪ ታጋቾችን እንደማይለቅ ሃማስ አስታውቋል። የመጀመሪያው የእርቅ ሂደት የፊታችን መጋቢት መጀመሪያ ላይ ካበቃ በኋላ ጦርነቱን እንዲቀጥሉ ኔታንያሁ ከቀኝ ቀኝ ዘመም አጋሮቻቸው ጫናው አይሎባቸዋል። ይሁን እንጂ በጉዳዩ ላይ ትራምፕ ያላቸው አቋም እስካሁን ግልፅ አይደለም። ምንም እንኳን ትራምፕ የእስራኤል ጠንካራ ደጋፊ ቢሆኑም፤  በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት በመካከለኛው ምሥራቅ ያሉትን ጦርነቶች ለማስቆም እና የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማደራደር ቃል መግባታቸው የሚታወስ ነው።

ዩናይትድ ስቴትስ በሶማሊያ የአይ ኤስ አሸባሪ ቡድን ጠንካራ ይዞታ ላይ ጥቃት ፈጸመች

የዩናይትድ ስቴትስ የጦር አውሮፕላኖች በሶማሊያ የሚገኘውን እስላማዊ መንግሥት በመባል የሚታወቀው የአሸባሪ ቡድን ጋር ተያያዥ ያላቸውን ሽብርተኛ ቡድኖች ይ
የአሜሪካ ድምፅ

ዩናይትድ ስቴትስ በሶማሊያ የአይ ኤስ አሸባሪ ቡድን ጠንካራ ይዞታ ላይ ጥቃት ፈጸመች

የዩናይትድ ስቴትስ የጦር አውሮፕላኖች በሶማሊያ የሚገኘውን እስላማዊ መንግሥት በመባል የሚታወቀው የአሸባሪ ቡድን ጋር ተያያዥ ያላቸውን ሽብርተኛ ቡድኖች ይገኙበታል የተባለውን ተራራማ ምሽግ ላይ ፤ ጥቃት መፈጸማቸውን የሶማሊያ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች አስታውቀዋል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅዳሜ ዕለት በማኅበራዊ ድረ-ገጻቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ጥቃቱ “ከፍተኛ የአይኤስ ጥቃት እና እቅድ አውጪ እንዲሁም አይ ኤስ የመለመላቸው እና የሚመራቸው አሸባሪዎች” ያነጣጠረ ዒላማ ነው ሲሉ ገልጸዋል። «ዩናይትድ ስቴትስን እና አጋሮቻችን የሚያስፈራሩትን እነዚህ አሸባሪዎች  በዋሻ ውስጥ ተደብቀው አግኝተናቸዋል» ብለዋል ትራምፕ። አያይዘውም ጥቃቱ ሲቪሎችን ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳያደርስ አሸባሪዎቹ ይኖሩባቸው የነበሩትን ዋሻዎች  ሙሉ በሙሉ በማውደም ገድለዋል” ብለዋል። የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግ ሴዝ  በሰጡት የተናጥል መግለጫ ፤ ጥቃቱ በሶማሊያ ጎሊስ ተራሮች አካባቢ ላይ ያነጣጠረ ሲሆን «ጥቃቱ አይኤስ በአሜሪካ ዜጎች እና  አጋሮቻችን እንዲሁም ንፁሀን ዜጎችን የሚያሰጉ የሽብር ጥቃቶችን የማሴር እና የማካሄድ አቅሙን አሳንሷል» ብለዋል። ሌሎች የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ጥቃቱ የተፈፀመው ከሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር ነው ቢሉም ትራምፕም ሆነ ሄግ ሴዝ የአይኤስ እቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ዝርዝር አልሰጡም። የፑንትላንድ ጄኔራል አዳን አብዲ ሃሺ  የአየር ጥቃቱ፤ የጎሊስ ተራሮች አካል በሆነው ካል ሚስካድ በተባለው አካባቢ፤  የእስላማዊ መንግስት ታጣቂዎች ላይ በሚገኙባቸው በትንሹ አስር የሚሆኑ ስፍራዎች ላይ ያነጣጠረ ነው ብለዋል። በፑንትላንድ ባሪ ግዛት ቃንዳላ በተሰኘች ትንሽ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ በደህንነት ስጋት ምክንያት ማንነታቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የአካባቢው ነዋሪዎች፤  ለአሜሪካ ድምጽ በሰጡት አስተያየት፤  ከሩቅ የሚነሳ የጭስ እና የእሳት ነበልባል ማየታቸውን እና በትንሹ ሰባት የሚሆኑ ግዙፍ ፍንዳታዎች መስማታቸውን ተናግረዋል። የሶማሊያ ከፊል ራስ ገዝ ግዛት የሆነችው ፑንትላንድ ባለሥልጣናት በማህበራዊ መገናኛቸው፤ ተልዕኮው የተሳካ መሆኑን በመግለጽ  ለዩናይትስ ስቴትስ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።  

ትራምፕ በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና በቻይና ላይ ታሪፍ ጣሉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ቅዳሜ ከካናዳ እና ሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25 ከመቶ ታሪፍ  የጣሉ ሲሆን ከቻይና ወደ ሀገር በሚገቡ
የአሜሪካ ድምፅ

ትራምፕ በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና በቻይና ላይ ታሪፍ ጣሉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ቅዳሜ ከካናዳ እና ሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25 ከመቶ ታሪፍ  የጣሉ ሲሆን ከቻይና ወደ ሀገር በሚገቡ ምርቶች ላይ ደግሞ ቀድሞ ከነበረው 10 ከመቶ ተጨማሪ ታሪፍ እንደሚጥሉ  ዋይት ኃውስ ገልጿል። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት አርብ ዕለት በሰጡት መግለጫ “ካናዳ እና ሜክሲኮ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የአሜሪካ ዜጎችን እየገደለ ያለውን ፌንተኒል የተሰኘ ሃሺሽ ስርጭት እና የህገወጥ ሰደተኞች ወረራ ፈቅደዋል ” በማለት ተናግረዋል። ሌቪት ከእርምጃዎቹ ውስጥ በልዩነት የሚታይ ነገር ይኖር እንደሆን አላስታወቁም። ይሁን እንጂ ቃል አቀባይዋ “እነዚህ በፕሬዝዳንቱ እንደሚደረጉ የተገቡ እና የተፈጸሙ ቃልኪዳኖች  ናቸው« ሲሉ ተናግረዋል። ስለጉዳዪ አርብ ዕለት በጋዜጠኞች የተጠየቁት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ውሳኔውን ለመቀልበስ ሦስቱ ሀገራት ማድረግ የሚችሉት ምንም ነገር እንደሌለ በመግለጽ ታሪፉ »የመደራደሪያ መሳሪያ አይደለም« ብለዋል። ትራምፕ ከትላንት ቅዳሜ አንስቶ የካናዳ ድፍድፍ ዘይት ላይ የአስር ከመቶ ፤ እንዲሁም በሌሎች የካናዳ ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ መጣሉን አስታውቀዋል። ታሪፉ ከፊታችን ማክሰኞ ጥር 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል። በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ከአውሮፓ ህብረት በሚወጡ ምርቶች ላይ “ፍፁም” ታሪፍ ሊጥሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። በጉዳዩ ላይ ተሰናባቹ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ሀገራቸው ምላሽ እንደምትሰጥ ገልጸዋል። »እነዚህን ታሪፎች ለማስቀረት  ጠንክረን እየሰራን ነው፣ ነገር ግን ዩናይትድ ስቴትስ በጉዳዩ ላይ ጸንታ ወደፊት የምትቀጥል ከሆነ ካናዳ ለጠንካራ እና ፈጣን ምላሽ ዝግጁ ናት" በማለት በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃናቸው አማካኝነት አስታውቀዋል። በአንጻሩ ሜክሲኮ በጉዳዩ ላይ ዝምታን የመረጠች ሲሆን፤ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ሚኒስቴር፤ ሜክሲኮ እና ዩናይትድ ስቴትስ “አጋሮች እንጂ ተፎካካሪዎች አይደሉም” በማለት በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃናቸው ላይ አስፍረዋል።

አንድ የሕክምና ማጓጓዣ አውሮፕላን ፊላደልፊያ ውስጥ ተከሰከሰ

አንድ ሕጻንና እናቱን እንዲሁም ሌሎች አራት ተሳፋሪዎችኝ የያዘ የሕክምና አውሮፕላን ፊላደልፊያ ውስጥ መኖሪያ ቤቶች ላይ ተከስክሷል። አውሮፕላኑ ሕክምናው
የአሜሪካ ድምፅ

አንድ የሕክምና ማጓጓዣ አውሮፕላን ፊላደልፊያ ውስጥ ተከሰከሰ

አንድ ሕጻንና እናቱን እንዲሁም ሌሎች አራት ተሳፋሪዎችኝ የያዘ የሕክምና አውሮፕላን ፊላደልፊያ ውስጥ መኖሪያ ቤቶች ላይ ተከስክሷል። አውሮፕላኑ ሕክምናውን ያጠናቀቀ ሕጻንና ሌሎቹን የሕክምና ተጓጓዦች ይዞ ሰሜን ምሥራቅ ፊላደልፊያ ከሚገኝ አየር ማረፊያ በተነሳ በግማሽ ደቂቃ ውስጥ ነበር የተከሰከሰው። አውሮፕላኑ የወደቀው መኖሪያ ቤቶች አካባቢ እንደሆነም ዘገባዎች አመልክተዋል። ተሳፋሪዎቹ በሙሉ ከሜክሲኮ የመጡ እንደሆኑም ታውቋል። አደጋው የደረሰው ዋሽንግተን ዲስ አየር ማረፊያ 60 መንገዶኞችን ይዞ ሊያርፍ የተቃረበ አውሮፕላን ከአንድ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር ጋራ ተጋጭቶ በተከሰከሰና ሁሉም ተሳፋሪዎች ሕይወታቸውን ባጡ በሁለተኛው ቀን ነው።

Get more results via ClueGoal