Ethiopia



የእስራኤል ወግ አጥባቂዎች ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የሚያስወጣ «የፍልሰት ባለሥልጣን» ለማቋቋም አቅደዋል

የእስራኤል አክራሪ ወግ አጥባቂዎች ከ2.3 ሚሊዮኑ ፍልስጤማውያን ብዙዎቹ ጋዛን ለቀው እንዲወጡ የሚያደርገውን የፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕን እቅድ በደስታ ተ

በቀነኒ አዱኛን አሟሟት ዙሪያ  ፖሊስ ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለምን አስሮ እየመረመረ መኾኑን አስታወቀ

በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ የሚታወቀው አንዷለም ጎሳ ባለቤት፣ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 10 ሰዓት አካባ
የአሜሪካ ድምፅ

በቀነኒ አዱኛን አሟሟት ዙሪያ  ፖሊስ ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለምን አስሮ እየመረመረ መኾኑን አስታወቀ

በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ የሚታወቀው አንዷለም ጎሳ ባለቤት፣ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ ፣ ሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 10 ሰዓት አካባቢ ከቤቷ ማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለሕክምና ርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ሕይወቷ ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዛሬ አስታውቋል፡፡ ክስተቱ በተፈጸመበት ወቅት በቤት ውስጥ ነበረ ያለውን ባለቤቷን፣ ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን በቁጥጥር ስር አውሎ እየመረመረ መሆኑንም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል። ለቤተሰቡ ቅርበት ያላቸውን ምንጮች፣ ጥንዶቹ በሕግ ትዳር አለመመስረታቸውን ጠቅሰው የፍቅር አጋር መኾናቸውን ትላንት ለአሜሪካ ድምጽ የገለጹ ሲኾን፣ በአንድ ቤት ውስጥ ሦስት ዓመት አብረው እንደኖሩንም ነግረውናል። ነገር ግን ፖሊስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አርቲስ አንዷለም ጎሳ የቀነኒ አዱኛ ባለቤት መኾኑን ጠቅሷል። ፖሊስ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ባወጣው በዚኽ መግለጫ፣ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ለምርመራ ሥራ የሚጠቅሙት ተገቢ መረጃዎች ማሰባሰቡን ገልጿል። የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ምርመራ መላኩን እማ የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም በቀጣይ ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ምዕራብ ሐረርጌ ውስጥ የተወለደችው ቀነኒ፣ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ነበረች። የባህላዊ አልባሳትን በመልበስ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በይበልጥ ትታወቅ ነበር።

የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት በኦዴሣ አራት ሰዎች መግደሉን የዩክሬን ባለሥልጣናት አስታወቁ

የዩክሬን ባለሥልጣናት በደቡባዊ ዩክሬን የወደብ ከተማ ኦዴሣ፣ ሌሊቱን በደረሰ የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት፣ አራት ሶሪያውያን ሲገደሉ፣ በርካቶች ቆስለዋል ሲሉ፣ ዛ
የአሜሪካ ድምፅ

የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት በኦዴሣ አራት ሰዎች መግደሉን የዩክሬን ባለሥልጣናት አስታወቁ

የዩክሬን ባለሥልጣናት በደቡባዊ ዩክሬን የወደብ ከተማ ኦዴሣ፣ ሌሊቱን በደረሰ የሩሲያ ሚሳይል ጥቃት፣ አራት ሶሪያውያን ሲገደሉ፣ በርካቶች ቆስለዋል ሲሉ፣ ዛሬ ረቡዕ አስታወቁ፡፡ የመልሶ ግንባታ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሌክሲ ኩሌባ በቴሌግራም ማኅበራዊ መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ ሚሳይሉ ወደ አልጄሪያ የሚላክ ስንዴ በመጫን ላይ በነበረች የጭነት መርከብ ላይ ጉዳት አድርሷል። ሩሲያ የዓለምን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ የተሰማሩ ወደቦችን ጨምሮ የዩክሬን መሠረተ ልማቶችን እያጠቃች መኾኑ ተመልክቷል። ሌላ የሚሳይል ጥቃት በዲኒፕሮፔትሮቭስክ ክልል ውስጥ በምትገኘው የፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ የትውልድ ከተማ ክሪቪ ሪህ ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡ በዚህ ጥቃት ቢያንስ አንድ ሰው ሲሞት ዘጠኝ ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የክልሉ ገዥ ተናግረዋል። አገረ ገዥው ሰርሂ ሊሳክ ክልሉ ከሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት እንደደረሰበት እና በጥቃቱም ከፍተኛ ፎቆች፣ አስተዳደራዊ ሕንፃዎች እና ትምህርት ቤት ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። የዛፖሪዥያ ክልል ባለሥልጣናት የሩስያ ሰው አልባ አውሮፕላን ሕክምና ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ማድረሱንም ገልጸዋል፡፡ የዩክሬን ጦር ዛሬ ረቡዕ እንዳስታወቀው የሩሲያ ጦር በአንድ ሌሊት ካስወነጨፋቸው 133 ሰው አልባ አውሮፕላኖች ውስጥ 98ቱን መትቶ ማውረዱን አስታውቋል። ድሮኖቹ የተመቱት “በቼርካሲ፣ ቼርኒሂቭ፣ ዲኒፕሮፔትሮቭስክ፣ ካርኪቭ፣ ክኸርሰን፣ ክምለኒትስኪ፣ ኪይቭ፣ ኦዴሳ፣ ፖልታቫ፣ ሪቪኔ፣ ሱሚ፣ ቴርኖፒል፣ ቪኒትሲያ፣ ዛፖሪዥያ እና ዚሂቶሚር ክልሎች ላይ ነው” ሲል ጦር ሠራዊቱ ይፋ አድርጓል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ረቡዕ ፣ 21 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) አውድሟል፡፡ የአየር መከላከያው ድሮኖቹ የተመቱት በብሪያንስክ፣ ኩርስክ እና ካልጋ ክልሎች እንዲሁም በጥቁር ባህር እና በሩሲያ በተያዘው ክራይሚያ ውስጥ መኾኑን ገልጿል። የአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት በዩክሬን ጥቃት ስለደረሰው ጉዳት እና ውድመት አልገለጹም። 

የቡና ስርቆት በአሜሪካ

በአሜሪካ የጭነት ተሽከርካሪዎች ኩባንያ መስሎ በመቅረብ በቡና ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ በመጨመር ላይ ነው። አሜሪካ በዓለም ከፍተኛ ቡና አስገቢ ሀገር ስትሆን፣
የአሜሪካ ድምፅ

የቡና ስርቆት በአሜሪካ

በአሜሪካ የጭነት ተሽከርካሪዎች ኩባንያ መስሎ በመቅረብ በቡና ላይ የሚፈጸም ዝርፊያ በመጨመር ላይ ነው። አሜሪካ በዓለም ከፍተኛ ቡና አስገቢ ሀገር ስትሆን፣ ባለፈው አንድ ዓመት ከዚህ በፊት ታይቶ በማያውቅ መጠን ዋጋው አሻቅቧል። ጉዳዩ ሂውስተን ውስጥ በተካሄደው የአሜሪካ ብሔራዊ የቡና ማኅበር ዓመታዊ ኮንፈረንስ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል። ቡና ሞቃታማ የአየር ንብረት ባላቸው ሀገራት የሚመረት በመኾኑ፣ በዓለም ቀዳሚ ቡና ጠጪ የሆነችው አሜሪካ ምርቱን መቶ በመቶ ከውጪ ለማስመጣት ተገዳለች፡፡ ምርቱ በአብዛኛው ከወደብ ወደ ቡና መቁያ ፋብሪካዎች የሚጓጓዘው በጭነት መኪና ነው። የዋጋውን መወደድ ያዩ ዘራፊዎች ታዲያ የጭነት ኩባንያ በመምሰል ቀርበው ቡናውን ጭነው ይሰወራሉ። ባለፈው አንድ ዓመት በደርዘን የሚቆጠሩ የጭነት መኪኖች ቡና ይዘው ተሰውረዋል። ቡና አምራች በሆኑ እንደ ብራዚል እና ቬትናም ባሉ ሀገራት ዝርፊያው የሚፈፀመው ገበሬዎች ምርቱን ሰብስበው ለጊዜው በሚያከማቹበት ሥፍራ ነው። ከአንድ ወር በፊት በብራዚል 230 ሺሕ ዶላር የሚያወጣ 500 ጆንያ ቡና በታጣቂዎች ተዘርፏል። በአሜሪካ ዝርፊያውን የሚፈጽሙት የትራንስፖርት ኩባንያ መስለው የሚቀርቡ ወሮበሎች ናቸው። አንድ የጭነት መኪና 20 ሺሕ ኪሎ ግራም የሚጠጋ ቡና ሲይዝ ይህም 180 ሺሕ ዶላር ይገመታል። ወሮበሎቹ የዘረፉትን፣ ቡና ለሚቆሉ አነስተኛ ኩባንያዎች በውድ ዋጋ ይሸጣሉ። አንዳንድ አስመጪዎች ታዲያ በጆንያው ላይ አቅጣጫ አመልካች መሣሪያ ለመግጠም ተገደዋል።

ዩጋንዳ በደቡብ ሱዳን ልዩ ኃይሏን አሰማራች

በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር እና በተቀዳሚ ምክትላቸው ሪክ ማቻር መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፤ ሀገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ሊመልሳት ይችላ
የአሜሪካ ድምፅ

ዩጋንዳ በደቡብ ሱዳን ልዩ ኃይሏን አሰማራች

በደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር እና በተቀዳሚ ምክትላቸው ሪክ ማቻር መካከል የተፈጠረው አለመግባባት፤ ሀገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት ሊመልሳት ይችላል የሚለው ስጋት እያየለ መሄዱን ተከትሎ፣ ዩጋንዳ ልዩ ኃይሏን በዋና ከተማዋ ጁባ ማሰማራቷን የኡጋንዳ ጦር አዛዥ ትላንት ማክሰኞ አስታወቁ። ነዳጅ አምራች በኾነችው ደቡቡ ሱዳን የኪር መንግሥት ሁለት ሚኒስትሮችን እና በርካታ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣናትን ማሰሩን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል። በጁባ የተካሄደው እስር እና በሰሜናዊው ናሲር ከተማ የተቀሰቀሰው ግጭት፣ በኪር እና በማቻር ታማኝ ኃይሎች መካከል የተካሄደውን እና ወደ 400 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ህልፈት ምክንያት የሆነውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም እ.አ.አ በ2018 የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ እንደሚጥል ተገልጿል። የኡጋንዳ የጦር አዛዥ ሙሆዚ ካይኔሩጋባ በኤክስ የማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት «ልዩ ኃይላችን ከሁለት ቀናት በፊት ፀጥታዋን ለማስጠበቅ ጁባ ገብቷል» ብለዋል። በዚሁ መልዕክታቸው አክለውም «የዩጋንዳ ጦር የሚያውቀው አንድ የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ብቻ ነው ። እሳቸውም ሳልቫ ኪር ናቸው። እሳቸውን በመቃወም የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ በዩጋንዳ ላይ ጦርነት እንደማወጅ ይቆጠራል» ብለዋል። ሮይተርስ በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር የደቡብ ሱዳን ማስታወቂያ ሚኒስትር ቃል አቀባይ እና የጦሩ ቃል አቀባይ የእጅ ስልክ ላይ በመደወል ያደረገ ሙከራ አልተሳካም ። እ.አ.አ በ2013 በደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ዩጋንዳ ከማቻር ጋራ የሚዋጋውን የኪር ኃይል ለማጠናከር ወታደሮቿን በጁባ አሰማርታ የነበር ሲኾን፣ እ.አ.አ በ2015 ለቀው ወጥተዋል። እ.አ.አ በ2016ም በሁለቱ ወገኖች መካከል ጦርነት በመቀስቀሱ የዩጋንዳ ጦር በድጋሚ ለአጭር ጊዜ ተሰማርቶ ነበር። ኡጋንዳ በሰሜን በኩል በምትዋሰናት ጎርቤቷ በድጋሚ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ከፍተኛ የስደተኞች ማዕበል ሊነሳ እና በሀገሯ አለመረጋጋት ሊፈጥር ይችላል ስትል ትሰጋለች። ካይኔሩጋባ፣ ዩጋንዳ ጦሯን በጁባ ያሰፈረችው በኪር መንግሥት ተጠይቆ ይሁን ወይም ወታደሮቹ ለምን ያህል ጊዜ በደቡብ ሱዳን እንደሚቆዩ አልተናገሩም።

ዶናልድ ትረምፕ የክሪፕቶ ግብይት እና ዲጂታል ሀብትን በተመለከተ ከመስኩ መሪዎች ጋራ ምክክር አደረጉ

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በክሪፕቶ ግብይት መሪ የኾኑ ግለሰቦችን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በዋይት ሐውስ ጋብዘው ዲጂታል ሀብት መገንባትን በተመለከተ ምክክር
የአሜሪካ ድምፅ

ዶናልድ ትረምፕ የክሪፕቶ ግብይት እና ዲጂታል ሀብትን በተመለከተ ከመስኩ መሪዎች ጋራ ምክክር አደረጉ

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በክሪፕቶ ግብይት መሪ የኾኑ ግለሰቦችን ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በዋይት ሐውስ ጋብዘው ዲጂታል ሀብት መገንባትን በተመለከተ ምክክር አድርገዋል። ፕሬዝደንቱ የቢትኮይን ሀብት ክምችትን ለመፍጠር ያላቸውን ፍላጎት በተመለከተም ተወያይተዋል። “አንዳንዶቻችሁ ሰዎች ስለ ጉዳዩ ምንም በማያውቁበት ወቅት ለረዥም ጊዜ ስትሠሩ ቆይታችኋል። እናም እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ። ይህ ትልቅ ቀን ነው” ብለዋል ትረምፕ፡፡ ስብሰባው አሜሪካ በክሪፕቶ መገበያያ ላይ ያላትን የፖሊሲ ለውጥ ያመለከተ ነው። የመስኩ መሪዎች በቀድሞው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስተዳደር ወቅት የነበሩ ደንቦችን በተመለከተ ቅሬታ ሲያሰሙ ቆይተዋል። ትረምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅትም ክሪፕቶን እንደሚያሳድጉ ቃል ገብተው ነበር። የመስኩ ባለሀብቶችም ለምርጫ ዘመቻቸውና ለበዓለ ሲመታቸው በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ ለግሰዋል። በአንዳንድ የክሪፕቶ ኩባንያዎች ላይ የነበረው ክስም እንዲሰረዝ ተደርጓል። “በባይደን አስተዳደር ወቅት በክሪፕቶ ላይ የታወጀውን ጦርነት የእኔ አስተዳደር ለማስቆም እየሠራ ነው” ሲሉ ተናግረዋል ትረምፕ፡፡ ትረምፕ በተጨማሪም የቢትኮይን መጠባበቂያ እንዲቋቋም ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዝ ፈርመዋል። የፒው ጥናት ተቋም እንደሚለው አብዛኞቹ አሜሪካውያን የክሪፕቶ መገበያያ አስተማማኝነት ያሳስባቸዋል። የክሪፕቶ መገበያያ ለተጠቃሚውም ኾነ ለፋይናንስ ሥርዓቱ አደጋ እንዳለው ነቃፊዎች ይናገራሉ። ሌሎች ደግሞ የትረምፕ አስተዳደር የክሪፕቶ መጠባበቂያ መመሥረቱ ኢንቨስተሮች በዲጂታል ሀብት ላይ እንዲተማመኑ ያደርጋል ይላሉ። “የክሪፕቶን መገበያያ ሕጋዊ ለማድረግ የተወሰደ ርምጃ ነው። መንግሥት ተቀብሎት የሚቀጥል ከሆነ፣ ግብይቱ ሕጋዊ ነው ማለት ነው” ብለዋል ፖል ኩፔክ ከአሜሪካ ኢንተርፕራይዝ ኢንስቲቱት፡፡ አንዳንድ ታዛቢዎች ደግሞ አሜሪካ በክሪፕቶ መገበያያ መሪ መሆን አለባት ባይ ናቸው። “ትይዩ የሆነ ሁለተኛ የመገበያያ የፋይናንስ ሥርዐት እየፈጠርን ነው። አሜሪካ የፋናንስ ኅይል እንዲኖራት በመስኩ መሳተፏ የአሜሪካ ዜጎችን ጥቅም የሚያስጠብቅ ነው” የሚሉት የኦላፍ ግሮት ከሃስ የንግድ ኮሌጅ ባልደረባ ናቸው። የቢትኮይን መጠባበቂያ የመጀመሪያ ሥራ የሚሆነው፣ መንግሥት ምን ያህል ቢትኮይን እንዳለው ማወቅ ነው። የዋይት ሃውስ ባለሥልጣናት እንደሚገምቱት መንግሥት 200ሺሕ ቢትኮይን እንዳለው ይገምታሉ። ይህም ወደ 17 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መሆኑ ነው። ዘገባው ሚሼል ኩዊን ነው።

አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን የስለላ መረጃ እና የፀጥታ እርዳታ እንደገና ጀመረች

የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለስልጣናት ማክሰኞ በሳዑዲ አረብያ፣ ጅዳ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ፣ የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በዩክሬን
የአሜሪካ ድምፅ

አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን የስለላ መረጃ እና የፀጥታ እርዳታ እንደገና ጀመረች

የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ባለስልጣናት ማክሰኞ በሳዑዲ አረብያ፣ ጅዳ ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ፣ የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በዩክሬን የስለላ መረጃ ማጋራት ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ እንደሚያነሳ እና ለዩክሬን የፀጥታ ድጋፍ መስጠት እንደሚቀጥል አስታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካ ባለስልጣናት በሚቀጥሉት ቀናት ከሩሲያ ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል። የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮቭ በዚህ ሳምንት ከሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሞስኮ ይገናኛሉ ተብሏል። ስምንት ሰዓት ከፈጀ ንግግር በኃላ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በምታካሂደው ጦርነት «አስቸኳይ የ30-ቀናት ተኩስ አቁም» ለማድረግ ዩናይትድ ስቴትስ ያቀረበችውን ሃሳብ ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ያስታወቀች ሲሆን፣ ክሬምሊንም ሀሳቡን መቀበል ይኖርበታል። የካቲት 26፣ 2017 ዓ.ም ትራምፕ ከዩክሬን ጋር ይደረግ የነበረውን የስለላ መረጃ ልውውጥ እንዲቋረጥ ያዘዙት፣ የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ጦርነቱን ለማቆም ከሩሲያ ጋር እንዲነጋገሩ ግፊት ለማድረግ መሆኑ ተመልክቷል። ክሬምሊን ዩናይትድ ስቴትስ እና ዩክሬን ባቀረቡት የተኩስ አቁም ሀሳብ ዙሪያ እስካሁን ምንም አስተያየት አልሰጠም። ሆኖም የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ በዚህ ሳምንት ከዩናይትድ ስቴትስ ባለስልጣናት ጋር ድርድር ሊደረግ እንደሚችል አመልክቷል። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልትዝ በጅዳ በተካሄደው ውይይት ላይ የተሳተፈውን የአሜሪካ ልዑካን ቡድን የመሩ ሲሆን ዘለንስኪ በስብሰባው ላይ አልተገኙም። በምትካቸው የዘለንስኪ ዋና አማካሪ አንድሪይ የርማክ፣ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪ ሺቢሃ፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሩስቴም ኡሜሮቭ እና የጦር አዛዥ ኮማንደር ፓቭሎ ፓሊሳ ተገኝተዋል። ከውይይቱ በኃላ ሩቢያ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል ዩክሬን ጦርነቱን ለማስቆም የሚያስችል አንድ እርምጃ ወደፊት ተራምዳለች ብለዋል። «አሁን ይህንን ሀሳብ ወደ ሩሲያኖች እንወስዳለን። እናም እንደሚስማሙ ተስፋ እናደርጋለን። ለሰላም ሲሉ ይስማማሉ። አሁን ኳሱ በእነሱ ደጅ ነው ያለው» ብለዋል።

የወጣቷ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ አሟሟት በመጣራት ላይ መኾኑን ፖሊስ አስታወቀ

ትላንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በድንገት ሕይወቷ ያለፈው ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ አሟሟት እየተጣራ መኾኑን ፖሊስ ጠቆመ በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ
የአሜሪካ ድምፅ

የወጣቷ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ አሟሟት በመጣራት ላይ መኾኑን ፖሊስ አስታወቀ

ትላንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. በድንገት ሕይወቷ ያለፈው ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ አሟሟት እየተጣራ መኾኑን ፖሊስ ጠቆመ በኦሮምኛ ቋንቋ ዘፈኑ የሚታወቀው አንዷለም ጎሳ የፍቅር አጋር እና ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሞያ ቀነኒ አዱኛ፣ ትላንት ሌሊት በአዲስ አበባ ከተማ ፣ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በድንገት ሕይወቷ ማለፉን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉና ለቤተሰብ ቅርብ የኾኑ ምንጮች ተናገሩ። ምስራቅ ሐረርጌ ውስጥ የተወለደችው ቀነኒ እና ድምፃዊ አንዷለም መኖሪያ ቤታቸው ህንጻ ላይ እንደሚገኝና፣ «ከአምስተኛ ፎቅ ራሷን ወርውራ» ሕይወቷ ማለፉን እኚኽ ለቤተሰቡ ቅርብ የኾኑ ምንጭ ገልጸዋል። ነገር ግን አሟሟቷን በተመለከተ ቪኦኤ ከፖሊስም ኾነ ለሌላ ገለልተኛ ምንጭ አላረጋገጠም። የባህላዊ አልባሳትን በመልበስ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በይበልጥ የምትታወቀው ቀነኒ፣ ከታዋቂው አንዷለም ጎሳ ጋራ ለሦስት ዓመታት በአንድ ቤት ይኖሩ የነበሩ የፍቅር አጋር መኾናቸውን እኚኹ ግለሰብ ነግረውናል። አርቲስት አንዷለምን ፖሊስ ለጥያቄ ፈልጎ እንደወሰደውና ይኽ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ፣ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እንደሚገኝ ምንጫችን ነግረውናል። በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን፣ የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ፣ በጉዳዩ ላይ መረጃ ለመስጠት ጊዜው ገና መኾኑን ተናግረዋል። ማምሻውን ያገኘናቸው አንድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ባልደረባ፣ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረገ መኾኑን ከመግለጽ ውጭ ምንም መረጃ እንደማይሰጡን ነግረውናል። የወጣት ቀነኒ አዱኛ አስከሬን ዛሬ ጠዋት ዳግማዊ በሚኒልክ ሆስፒታል የአስከሬን ምርመራ ከተደረገለት በኋላ ዛሬ ከሰዓት፣ 9 ሰዓት አካባቢ ሱሉልታ ወደሚገኘው እህቷ ቤት እንደተወሰደ ምንጩ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

የአውሮፓ ኅብረት በትግራይ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለፀ

በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት በንግግር እንዲፈታ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ጠይቀዋል። አምባሳደሯ ሶፊ ፍሮም፣ በኅብረቱ እና በኢትዮጵያ የሁለ
የአሜሪካ ድምፅ

የአውሮፓ ኅብረት በትግራይ ያለው ውጥረት እንደሚያሳስበው ገለፀ

በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት በንግግር እንዲፈታ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ጠይቀዋል። አምባሳደሯ ሶፊ ፍሮም፣ በኅብረቱ እና በኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ በሰጡበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ ለሰብአዊ መብቶች መሻሻልም መሥራት እንዳለባት ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኤመንስበርገር ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 2 በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ አምባሳደሯ፣ ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኅብረት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 50ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሰጡት መግለጫ ላይ፣ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችን እና ውጥረቶችን በተመለከተ ተጠይቀው መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዋናነት፣ በፕሪቶሪያው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ግምገማ እና ከህወሓት ሕጋዊ ቁመና ጋራ በተገናኘ ያለውን አለመግባባት ተከትሎ በትግራይ ክልል ያለው ውጥረት የአውሮፓ ኅብረትን እንደሚያሳስብ አምባሳደሯ ገልፀዋል፡፡ በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲሁም በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ እንዲያገኝም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የአሜሪካ አክሲዮን ገበያዎች አሽቆልቁለው አደሩ

በአሜሪካ የሚገኙ ሦስቱም ዋና የአክሲዮን ገበያዎች ትላንት ሰኞ በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁለው አድረዋል። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በአሜሪካ የንግድ ሸሪኮች
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ አክሲዮን ገበያዎች አሽቆልቁለው አደሩ

በአሜሪካ የሚገኙ ሦስቱም ዋና የአክሲዮን ገበያዎች ትላንት ሰኞ በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁለው አድረዋል። ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ በአሜሪካ የንግድ ሸሪኮች ላይ በጣሉት ታሪፍ እንዲሁም በሚቀጥሉት ወራት ኢኮኖሚው እንደማይዳከም ማስተማመኛ አለመስጥታቸው ኢንቨስተሮችን ያሳሰበ ጉዳይ ሆኗል። በዳው ጆንስ የአክሲዮን ገበያ የነበሩ 30 ብሉ ቺፕስ አክሲዮኖች በ2.1 በመቶ ሲያሽቆለቁሉ፣ የስታንዳርድ ኤንድ ፑር 500 (ኤስ ኤንድ ፒ 500) ደግሞ በ2.7 በመቶ ወርዷል። በአብዛኛው ቴክኖሎጂ ነክ አክሲዮኖችን የያዘው ናስዳክ ደግሞ በ4 በመቶ ዝቅ ብሏል። ኤስ ኤንድ ፒ 500 ከአንድ ወር በፊት ከነበረበት ከፍተኛ ሽያጭ በ8.6 በመቶ ወርዷል። ናስዳክ ደግሞ ከመስከረም 2014 ዓ/ም ወዲህ በአንድ ቀን ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሲያሽቆለቁል ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። የትረምፕ ታሪፍ መጫን ኢንቨስተሮችን ስጋት ውስት ጥሏል። የንግድ ምኒስትሩ በአሜሪካ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል እንደማይኖር ቢናገሩም፣ ትረምፕ ግን “መተንበይ አልወድም፣ ነገር ግን የሽግግር ወቅት ይኖራል።“ ብለዋል

ውጥረቱ እያየለ በመጣባት ሰርቢያ ተቃዋሚዎች ወደ ዋናው የሰርቢያ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሚወስደውን መንገድ ዘግተው ዋሉ

በመቶዎች የተቆጠሩ ተማሪዎች ውጥረቱ እያየለ በመጣባት የባልካን ሀገር፣ ለፊታችን ቅዳሜና እሑድ ከታቀደው ግዙፍ ሰልፍ ቀናት አስቀድመው ቤልግሬድ የመንግሥቱ
የአሜሪካ ድምፅ

ውጥረቱ እያየለ በመጣባት ሰርቢያ ተቃዋሚዎች ወደ ዋናው የሰርቢያ ቴሌቭዥን ጣቢያ የሚወስደውን መንገድ ዘግተው ዋሉ

በመቶዎች የተቆጠሩ ተማሪዎች ውጥረቱ እያየለ በመጣባት የባልካን ሀገር፣ ለፊታችን ቅዳሜና እሑድ ከታቀደው ግዙፍ ሰልፍ ቀናት አስቀድመው ቤልግሬድ የመንግሥቱን የሰርቢያ ቴሌቪዥን ጣቢያ ህንጻ ዘግተው ውለዋል። ለሳምንቱ መጨረሻ የተጠራው ግዙፍ ሰልፍ ለወራት የቀጠለው የጸረ መንግሥት ተቃውሞ መዳረሻ ተደርጎ ታይቷል። ማዕከላዊ ቤልግሬድ የሚገኘውን የቴሌቭዥን ሕንጻ ትላንት ማምሻው ላይ የዘጉት ተማሪዎች፣ ዛሬ ማክሰኞም ብዙ መቶዎች ኾነው ተሰባስበው የመንገድ መዝጋቱ ጥረት ለተጨማሪ 22 ሰዓታት እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። በሁለተኛዋ የሃገሪቱ ትልቅ ከተማ ኖቪ ሳድ’ም ተመሳሳይ ተቃውሞ ተደራጅቷል። በኖቪ ሳድ የባቡር ጣቢያ የኮንክሪት ጣሪያ ተደርምሶ የ15 ሰዎች ህይወት ካጠፋ በኋላ፣ በየዕለቱ የሚካሄዱትን ሰልፎች የሚያደራጁት በተለያዩ የሰርቢያ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች ናቸው። የተቃውሞ ሰልፎቹ የሕዝበኝነት አቀንቃኙን የፕሬዝዳንት አሌክሳንዳር ቩቲች አገዛዝ እና ሥልጣን የሙጥኝ ብለው በመቀጠል የያዙትን አቋም አናውጠዋል። ትላንት ሰኞ አመሻሹ ላይ በቴሌቪዥን ጣቢያው ዋና የዜና እወጃ ወቅት እንግዳ የነበሩት የሰርቢያው ፕሬዝደንት በቃለ መጠይቁ ወቅት በተማሪዎች የሚመራውን የተቃውሞ ሰልፍ ሲዘልፉ ታይተዋል። «የጸጥታ ኃይሎች በቅዳሜው ታላቅ ሰልፍ ላይ የኃይል ርምጃ ይወስዳሉ» ሲልም አስጠንቅቀዋል። በመላ አገሪቱ የተካሄደውን መጠነ ሰፊ ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ ከሥልጣን አልወርድም ሲሉ የዛቱት ቩቲች «ሃሳባችሁ እኔን መተካት ከሆነ የምትተኩኝ ገድላችሁኝ ነው» ሲሉ ተደምጠዋል። ተማሪዎቹ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ከቩቲች እና ከአስተዳደራቸው ጎን የቆመውን የመንግሥቱን ቴሌቭዥን ጣቢያ ፈጸመ ላሉት ድርጊት ተጠያቂ አድርገዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ቩቲች በዛሬው ዕለት ቤልግሬድ ከገቡት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ የበኩር ልጅ ዶናልድ ትረምፕ ጁኒየር ጋር ተገናኝተው ተነጋግረዋል። የጉብኝቱ ዓላማ ግን ለጊዜው አልታወቀም።ሩሲያው ቩቲች የፕሬዝደንት ትረምፕ ዋና ደጋፊ መሆናቸው ይታወቃል።

የህወሓት የዓዲግራት ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ውዝግብና የጄነራሎች እግድ

የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተካሮ፣ ዛሬ በዓዲግራት ከተማ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ይገባኛል ጥያቄ ውዝግ
የአሜሪካ ድምፅ

የህወሓት የዓዲግራት ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ውዝግብና የጄነራሎች እግድ

የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተካሮ፣ ዛሬ በዓዲግራት ከተማ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ይገባኛል ጥያቄ ውዝግብ መፍጠሩ ተገለጸ። በዶ.ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን፣ ለዓዲግራት ከተማ የሾማቸውን ከንቲባ፣ ጽሕፈት ቤቱን በኃይል በመስበር አስገብቷል ሲል ፣ የትግራይ ምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ሓላፊ አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ ለአሜሪካ ድምፅ ገለፁ። በዛሬው ዕለት ከንቲባው ጽሕፈት ቤት ገቡ የተባሉት፣ አቶ ረዳኢ ገብረ እግዚአብሔር፣ “ወደ ጽሕፈት ቤቱ በር ሰብረን አልገባንም፣ ህዝብ በምክርቤት የተመረጠ ከንቲባ ይግባ ብሎ በሰልፍ ስለመጣ ነው ወደ ፅሕፈት ቤት የገባነው ብለዋል። በሌላ ዜና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት፣አቶ ጌታቸው ረዳ ሦስት የትግራይ ሠራዊት ከፍተኛ አዛዦችን አገዱ። በትላንትናው ዕለት በአቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ የተጻፈ ደብዳቤ፣ ሜጀር ጄነራል ዮሐንስ ወ/ጊዮርጊሰ፣ ሜጀር ጄነራል ማሾ በየነ እና ብርጋዴር ጄነራል ምግበይ ኅይለ በጊዜያዊነት ታግደዋል በማለት ያስረዳል። ውሳኔው በደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን እና የክልሉ የፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ተቃውመውታል።

የአላባማዋ ሰልማ ከተማ 60ኛውን 'የሰንበት ሰቆቃ' መታሰቢያ አከበረች

እ.አ.አ በመጋቢት 7፣ 1965፣ በዩናይትድ ስቴትስ አላባማ ግዛት፣ ሰልማ ከተማ ውስጥ የመምረጥ መብት እንዲሰጣቸው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በኤድመንድ ፔተስ ድልድይ ላይ
የአሜሪካ ድምፅ

የአላባማዋ ሰልማ ከተማ 60ኛውን 'የሰንበት ሰቆቃ' መታሰቢያ አከበረች

እ.አ.አ በመጋቢት 7፣ 1965፣ በዩናይትድ ስቴትስ አላባማ ግዛት፣ ሰልማ ከተማ ውስጥ የመምረጥ መብት እንዲሰጣቸው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በኤድመንድ ፔተስ ድልድይ ላይ የተጓዙ ሰልፈኞችን ከፊት ከሚመሩት መካከል አንዱ ቻርለን ሞልዲን ነበሩ። ሰልፈኞቹ ነጭ ባለሥልጣናት፣ ጥቁር አላባማውያን ድምፅ ለመስጠት እንዳይመዘገቡ መከልከላቸውን እና ከቀናት በፊት ጂሚ ሊ ጃክሰን የተሰኘው ሚኒስትር እና የመምረጥ መብት አደራጅ፣ በመንግሥት ወታደሮች ተተኩሶበት መገደሉን ተቃውመው ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ነበሩ። ድንገት ግን ከአላባማ ወንዝ ጫፍ ላይ ምን እንደሚጠብቃቸው ተመለከቱ፤ በፈረስ ላይ የተቀመጡ ሰዎች፣ የመንግስት ተወካዮች እና ወታደሮች። እየቀረቡ ሲመጡ የሕግ አስከባሪ አካላት እንዲበታተኑ ማስጠንቀቂያ ሰጧቸው፣ ብጥብጥም ተፈጠረ። በወቅቱ የ17 ዓመት ወጣት የነበሩት ሞልዲን ሁኔታውን ሲያስታውሱ «ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፖሊሶቹ ጋሻቸውን አውጥተው ይገፉን ጀመር። ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ወንዶችን፣ ሴቶችን፣ ሕፃናትን መምታት፣ አስለቃሽ ጋዝ መጠቀም እና በኤሌክትሪክ ማንዘር ጀመሩ» ይላሉ። ሰልማ ከተማ ትላንት እሑድ «በደም የታጠበው እሑድ» በመባል የሚጠራውን ጥቃት 60ኛ ዓመት አክብራ ውላለች። በሰልፈኞቹ ላይ የተፈጸመው ጥቃት መላ ሀገሪቱን ያስደነገጠ ሲሆን እ.አ.አ በ1965 ድምፅ የመስጠት መብት እንዲፀድቅ ድጋፍ አስገኝቷል። በዚህ ዓመታዊ መታሰቢያ የጥቁሮች የመምረጥ መብት እንዲከበር ለታገሉ ክብር የተሰጠ ሲሆን፣ እኩልነት ለማምጣት ለሚደረገው ትግልም በድጋሚ ጥሪ ቀርቧል። የዘንድሮ በዓል የተከበረው በመምረጥ መብት ዙሪያ አዳዲስ ክልከላዎች እየመጡ ነው የሚል ስጋት ባየለበት እና የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ ለሁሉም ዜጎች ዲሞክራሲያዊ እንድትሆን የረዱ የፌደራል ተቋማት እንደአዲስ እንዲቋቋሙ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ዓመታዊው ክብረ በዓል የሚጠናቀቀው 'በደም የታጠበው እሁድ' በተፈፀመበት የኤድመንድ ፔተስ ድልድይ ላይ የእግር ጉዞ በማድረግ ነው።

በራያ አላማጣ ጥሙጋ ቀበሌ አንድ የቤተክርስቲያን መምሕርና አራት ተማሪዎች ተገደሉ

በራያ ኣላማጣ ጥሙጋ በተባለ ቀበሌ ውስጥ ባለፈው አርብ፣ በአንድ ቤተ ክርስትያን መምህር እና ተማሪዎች በተፈፀመ ጥቃት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው አ
የአሜሪካ ድምፅ

በራያ አላማጣ ጥሙጋ ቀበሌ አንድ የቤተክርስቲያን መምሕርና አራት ተማሪዎች ተገደሉ

በራያ ኣላማጣ ጥሙጋ በተባለ ቀበሌ ውስጥ ባለፈው አርብ፣ በአንድ ቤተ ክርስትያን መምህር እና ተማሪዎች በተፈፀመ ጥቃት አምስት ሰዎች መገደላቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ገለጹ። የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ሕሉፍ፣ በሌሎች አራት ሰዎች ላይም በጥቃቱ ጉዳት መስረሱን ተናግረዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።  

የአሜሪካ ታጋቾች ተደራዳሪ ከሐማስ ጋራ የነበራቸውን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል

የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ተደራዳሪ በቅርቡ በአሜሪካ ከተሰየመው የሽብር ቡድን ሐማስ ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል። ንግግሩ በ
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ ታጋቾች ተደራዳሪ ከሐማስ ጋራ የነበራቸውን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል

የትረምፕ አስተዳደር የታጋቾች ተደራዳሪ በቅርቡ በአሜሪካ ከተሰየመው የሽብር ቡድን ሐማስ ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ንግግር “ጠቃሚ” ብለውታል። ንግግሩ በሐማስ ተይዞ የነበረውን አሜሪካዊ-እስራኤላዊን በመልቀቅ ላይ ያተኮረ ነበር። ንግግሩ የተካሄደው እስራኤል በዚህ ሳምንት የተኩስ አቁም ድርድር ላይ ለመወያየት የልዑካን ቡድን ልታሰማራ እንደሆነ በገለጸችበት ወቅት ነው፡፡ የቪኦኤ አራሽ አራብሳዲ የላከቸውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።  

ሩሲያ ዩክሬን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 11 ሰዎች መገደላቸውን ኪቭ አስታወቀች

ኪቭ፣ ዩክሬን — ሩሲያ ትላንት ቅዳሜ የካቲት  29 ቀን 2017 ዓ.ም፣ በዩክሬን ምሥራቃዊ ከተማ ዶቭሮፒሊያ ላይ በአንድ ምሽት ባደረሰችው፣ የሚሳዬልና ሰው አልባ አው
የአሜሪካ ድምፅ

ሩሲያ ዩክሬን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 11 ሰዎች መገደላቸውን ኪቭ አስታወቀች

ኪቭ፣ ዩክሬን — ሩሲያ ትላንት ቅዳሜ የካቲት  29 ቀን 2017 ዓ.ም፣ በዩክሬን ምሥራቃዊ ከተማ ዶቭሮፒሊያ ላይ በአንድ ምሽት ባደረሰችው፣ የሚሳዬልና ሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ቢያንስ 11 ሰዎች ሲገደሉ፣ አምስት ሕፃናትን ጨምሮ 30 ሰዎች መቁሰላቸውን የዩክሬን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሰሜን ምስራቅ ካርኪቭ ግዛት ላይ በደረሰው ጥቃት ፣ ሌሎች ሦስት ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸውን ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል። የሩሲያ ጦር ኃይል ወደ ይክሬኗ ከተማ፣ ባስወነጨፋቸው ባላስቲክ ሚሳዬሎች፣ በተኮሰቸው በበርካታ ሮኬቶች እና በላከቸው ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት፣ ዶቭሮፒሊያ ውስጥ የሚገኙ ስምንት የተለያዩ ሕንፃዎችና 30 መኪኖች መውደማቸውን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ ገልጿል። ሚኒስቴሩ፣ በቴሌግራም መልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያ ላይ እንዳሰፈሩት፣ «በጥቃቱ ምክኒያት የተቀጣጠለውን እሳት ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ በነበረበት ወቅት፣ ሌላ ተጨማሪ ጥቃት ደርሶ የእሳት አደጋ መከላከያ እና ማጥፊያ መኪናውን ላይ ጉዳት አድርሷል» ብለዋል። ሚኒስቴሩ በቴሌግራም መልዕክታቸው፣ በከፊል የወደሙ ፍርስራሾችን፣ በእሳት ውስጥ የተዋጡ ሕንፃዎችን እና የነፍስ አድን ሠራተኞች ከሕንፃዎቹ ላይ ፍርስራሾችን ሲያነሱ የሚያሳዩ ምስሎችን አጋርተዋል። ከዩክሬን የዶኔትስክ ግዛት የፖክሮቭስክ ቁልፍ ማዕከል 22 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ዶቭሮፒሊያ፣ ከጦሩነቱ በፊት ወደ 28 ሺሕ የሚጠጉ ነዋሪዎች ያሉባት ከተማ ስትኾን ፣ የሩስያ ወታደሮች ለሳምንታት ጥቃት ሲሰነዝሩበት መቆየታቸውን የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል። ሚኒስቴሩ አያይዘው፣ ካርኪቭ ላይ በተፈጸመ ሌላ የድሮን ጥቃት፣ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን እና ሌሎች ሰባት ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል። የዩክሬ ጦር በበኩሉ፣ ሩሲያ 145 ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሦስት የተለያዩ ሚሳዬሎችን ልካ ጥቃቱን እንደፈጸመች አስታውቋል። የጦር ኃይሉ አክሎም፣ አንድ የክሩዝ ሚሳዬል እና 79 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መቶ መጣሉን ገልጿል። ሌሎች 54 ሰው አልባ አውሮፕላኖች ደግሞ በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ በተወሰዱ የመከላከያ ርምጃዎች ምክንያት ዒላማቸው ላይ ሳይደርሱ እንዲከሽፉ መደረጋቸውን የዩክሬን ወታደራዊ ክንፍ አስታውቋል።

በዋይት ሐውስ አቅራቢያ የታጠቀ ግለሰብ በፕሬዝደንታዊ የደኅንነት ጥበቃ ሠራተኞች ተመታ

አንድ ከኢንዲያና ግዛት አካባቢ እንደመጣ የተገመተ እና በዋይት ሐውስ አካባቢ መሳሪያ ታጥቆ፣ ከፖሊስ ጋራ እሰጥ አገባ ውስጥ ገብቷል የተባለ ግለሰብ ፣ “ሴክሬ
የአሜሪካ ድምፅ

በዋይት ሐውስ አቅራቢያ የታጠቀ ግለሰብ በፕሬዝደንታዊ የደኅንነት ጥበቃ ሠራተኞች ተመታ

አንድ ከኢንዲያና ግዛት አካባቢ እንደመጣ የተገመተ እና በዋይት ሐውስ አካባቢ መሳሪያ ታጥቆ፣ ከፖሊስ ጋራ እሰጥ አገባ ውስጥ ገብቷል የተባለ ግለሰብ ፣ “ሴክሬት ሰርቪስ” በመባል በሚታወቀው፣ ዩናይትድ ስቴትስ የፕሬዝደንታዊ የደኅንነት ጥበቃ አባላት መመታቱን ባለሥልጣናት አስታወቁ። ከዋይት ሐውስ በአንድ አካፋይ መንገድ ብቻ በሚርቅ ቦታ ላይ፣ እኩለ ሌሊት አካባቢ በተፈጠረው በዚኽ ክስተት ከታጠቀው ገለሰብ በስተቀር የተጎዳ ሌላ ሰው አለመኖሩን የ«ሴክሬት ሰርቪሱ» መግለጫ አመልክቷል። በሰዓቱም ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ፍሎሪዳ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ነበሩ ተብሏል። የጥበቃ አገልግሎቱ፣ «አንድ ራሱን ሊያጠፋ ነው» በሚል የሚጠረጠር ግለሰብ ከኢንዲያና ተጉዞ መምጣቱን ከአካባቢ ፖሊስ መረጃ እንደደረሰው ገልጾ፣ ከተሰጠው ዝርዝር መግለጫ ጋራ የሚመሳሰለውን መኪና እና ግለሰቡን በዋይት ሐውስ አቅራቢያ ማግኘቱን አስታውቋል። «ፖሊስ ወደ መኪናው እየቀረበ ሲኼድ ግለሰቡ መሳሪያ በማውጣት እሰጥ አገባ ገጠመ፣ በዚኽ ወቅትም ከኛ በኩል ርምጃ ተወስዷል» ሲል ፕሬዝደንታዊ ደኅንነት ጥበቃ አገልግሎቱ በመግለጫው ላይ አስፍሯል። ግለሰቡ ሆስፒታል እንደሚገኝ የጠቆመው መግልጫው ፣ አኹን ያለበት ኹኔታ ግን «አይታወቅም» ብሏል።

«ከከተሞች ውጭ ያሉ አካል ጉዳተኞችም ትኩረትን ይሻሉ» - ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ

የአብስትራክት ዘይቤ ሠዓሊው ብሩክ የሺጥላ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ስመ ጥር ከኾኑ አካል ጉዳተኛ ሠዓሊዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ብሩክ፥ ወጣት አካል ጉዳተኞችን በማ
የአሜሪካ ድምፅ

«ከከተሞች ውጭ ያሉ አካል ጉዳተኞችም ትኩረትን ይሻሉ» - ሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ

የአብስትራክት ዘይቤ ሠዓሊው ብሩክ የሺጥላ፥ ኢትዮጵያ ውስጥ ስመ ጥር ከኾኑ አካል ጉዳተኛ ሠዓሊዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ብሩክ፥ ወጣት አካል ጉዳተኞችን በማነቃቃት፣ በማስተማር እና በማበረታታት ለማብቃት፣ ብዙኀን መገናኛዎች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ይናገራል፡፡  በተለይም፣ ከከተሞች ውጭ የሚገኙ ወጣት አካል ጉዳተኞች በሚሰባሰቡባቸው ስፍራዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብሮች ማካሔድ እንደሚገባ ሠዓሊ ብሩክ አመልክቷል፡፡  ኤደን ገረመው፥ ከሠዓሊ ብሩክ የሺጥላ ጋራ ያደረገችውን ቆይታ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ። 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማርች 8ትን በሴቶች ብቻ በሚደረጉ በረራዎች እያከበረ ነው

ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በተለያዩ ሥነ ሥርዐቶች ያከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከትናንት የካቲት 28 ቀን 2017 አንስቶ በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስድስት በረራዎ
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማርች 8ትን በሴቶች ብቻ በሚደረጉ በረራዎች እያከበረ ነው

ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በተለያዩ ሥነ ሥርዐቶች ያከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከትናንት የካቲት 28 ቀን 2017 አንስቶ በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስድስት በረራዎችን ወደተለያዩ መዳረሻዎች ማድረግ ጀምሯል። የበረራ ፕሮግራሙ ሴት ሞያተኞችን በዓለምአቀፍ አቪየሺን ኢንዱስትሪ ላይ እያሳረፉ ያለው ደማቅ አሻራ ጎልቶ እንዳታይ የሚያደርግ ነው ሲሉ የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ ተናግረዋል ። አየር መንገዱ፣ በሴቶች ብቻ የሚመሩ በረራዎቹን የሚያደርገው ወደ አቴንስ ፣ሳኦ ፖሎ፣ኒው ደልሂ፣ዊንድሆክ፣ዱባይና ባሕርዳር መኾኑን አስታውቋል ። በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተናገሩት የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ኃላፊ ለማ ያዴቻ፣ ሰድስቱ በረራዎች ከአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሴቶች የሚመሩ መኾናቸውን አስታውቀዋል። በረራዎቹ የአየር መንገዱን ሴት ሠራተኞች አስተዋጽኦ እንደሚያስተዋውቁም ጠቅሰዋል ። በኹሉሞ ዘርፎች እየታያ ነው ያሉትን የሴት ሞያተኞች ተሳትፎ ያብራሩት አቶ ለማ፣ ይሄም የተቋቋሙ ጥንካሬ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በተለምዶ የወንዶች ተሳትፎ ልቆ በሚታይበት የአቪየሺን ዘርፍ ውስጥ የሴቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መኾኑን የገለፁት ኃላፊው አየር መንገዱ ሚናቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እየሠራ መኾኑንም ጠቅሰዋል። በረራዎቹ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን አጉልቶ ለማሳየትና አጋርነትን ለመግለጽ ጭምር የተካሄዱ መኾናቸውንም ተናግረዋል። ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን (ማርች 8) ዘንድሮ እየተከበረ ያለው «መብት እኩልነትና አቅም መጎልበት ለሴቶች በሙሉ» በሚል መሪ ቃል ነው።

በመንና ጅቡቲ ጀልባዎች ሰጥመው ፍልሰተኞች መሞታቸውንና በርካቶች የደረሱበት አለመታወቁን ተመድ አስታወቀ 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልሰተኞች ኤጀንሲ እንደገለፀው በየመንና ጅቡቲ የባህር ዳርቻ አራት የፍልሰተኞች ጀልባዎች ሰጥመው ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚ
የአሜሪካ ድምፅ

በመንና ጅቡቲ ጀልባዎች ሰጥመው ፍልሰተኞች መሞታቸውንና በርካቶች የደረሱበት አለመታወቁን ተመድ አስታወቀ 

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፍልሰተኞች ኤጀንሲ እንደገለፀው በየመንና ጅቡቲ የባህር ዳርቻ አራት የፍልሰተኞች ጀልባዎች ሰጥመው ሁለት ሰዎች ሲሞቱ 186 የሚሆኑት ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም። የዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ቃል አቀባይ ታሚም ኤሊየን እንዳሉት ሁለት ጀልባዎች በየመን ባህር ላይ የሰጠሙት ሀሙስ ምሽት ሲሆን የጠፉት 181 ፍልሰተኞችና አምስት የየመን የጀልባው ሰራተኞች መሆናቸውን ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል። ሁለት የጀልባው ሰራተኞችን ማትረፍ ተችሏል ብለዋል፡፡ ሌሎች ሁለት ጀልባዎች ደግሞ በትንሿ አፍሪካዊቷ ሀገር ጅቡቲ በተመሳሳይ ሰዓት ላይ ሰጥመዋል ሲሉ ተናግረዋል። የሁለት ፍልሰተኞች አስከሬን የተገኘ ሲሆን በጀልባው ውስጥ የነበሩ ሌሎች ሰዎችንም ማትረፍ መቻሉን ገልጸዋል፡፡ በደቡብ ምእራብ የመን ታይዝ ግዛት በዱባብ ወረዳ የተገለበጠችው ሶስተኛዋ ጀልባ 31 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችና ሶስት የመናውያን ሰራተኞችን አሳፍራ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ አራተኛዋ ጀልባ የሰጠመችው ደግሞ በዚሁ አካባቢ አቅራቢያ ወደሚገኘው የአቢያን ግዛት አህዋር ወረዳ ሲሆን 150 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችንና አራት ሰራተኞችን አሳፋራ የነበረች ናት፡፡ ባለፉት አስርት አመታት ከአፍሪካ ቀንድ ወደ የመን በሚወስደው በዚህ የፍልሰተኞች የባህር ጉዞ ሰጥመው መሞታቸው የተረጋገጡ 693 ሰዎችን ጨምሮ ቢያንስ 2ሽህ 82 ፍልሰተኞች ደብዛቸው ጠፍቷል፡፡

ፕሬዘዳንት ትራምፕ የቴሌቭዥን አቅራቢ የሆኑትን ላውራ ኢንግራሃምንና ማሪያ ባርቲሮሞን ለኬኔዲ ማዕከል ቦርድ አድርገው ሾሙ 

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እንዳስታወቁት የፎክስ ኒውስ ፕሮግራም መሪ ላውራ ኢንግራሃምንና የጣቢያው ቢዝነስ ዘገባ አቅራቢ ማሪያ
የአሜሪካ ድምፅ

ፕሬዘዳንት ትራምፕ የቴሌቭዥን አቅራቢ የሆኑትን ላውራ ኢንግራሃምንና ማሪያ ባርቲሮሞን ለኬኔዲ ማዕከል ቦርድ አድርገው ሾሙ 

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት እንዳስታወቁት የፎክስ ኒውስ ፕሮግራም መሪ ላውራ ኢንግራሃምንና የጣቢያው ቢዝነስ ዘገባ አቅራቢ ማሪያ ባቲሮሞንን ለጆን ኤፍ ኬኔዲ የስነ ጥበባት ማዕከል ቦርድ ሹመዋል፡፡  ትራምፕ ስልጣን ከያዙ ከሳምንታት በኋላ የካቲት ወር ላይ የማዕከሉን ፕሬዝዳንት በማባረር የባለአደራ ቦርድ የተከኩ ሲሆን የድርጅቱን ሊቀመንበርም ሰይመዋል።  ርምጃዎቹ የክብር ትርኢት የሚቀርቡበትና የብሄራዊ ሲምፎኒ ኦርኬስትራ እንዲሁም የዋሽንግተን ብሄራዊ ኦፔራ የሚቀርብበት የባህል ተቋም የሆነውን የኬኔዲ ማዕከል ትራምፕን መቆጣጠራቸውን ያሳያል ተብሏል፡፡  ትራምፕ የኢንግራሃም እና የባርቲሮሞ ሹመት ካስታወቁ በኋላ «ይህ ምርጫችንን ያጠናቅቃል» ሲሉ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡  ትራምፕ ባለፈው ወር የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ልዑክ የሆኑት ሪቻርድ ግሬኔል የማዕከሉ ጊዜያዊ ስራ አስፈፃሚ ሆነው እንዲያገለግሉ ሹመዋል፡፡

የየመን ሁቲዎች ለእስራኤል የጋዛን የእርዳታ እገዳ እንድታነሳ የአራት ቀናት ቀነ ገደብ ሰጡ 

የየመን ሁቲ አማጽያን መሪ እስራኤል በአራት ቀናት ውስጥ በጋዛ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እገዳ ካላነሳች ቡድኑ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን የባህር ሃይል ጥ
የአሜሪካ ድምፅ

የየመን ሁቲዎች ለእስራኤል የጋዛን የእርዳታ እገዳ እንድታነሳ የአራት ቀናት ቀነ ገደብ ሰጡ 

የየመን ሁቲ አማጽያን መሪ እስራኤል በአራት ቀናት ውስጥ በጋዛ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እገዳ ካላነሳች ቡድኑ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን የባህር ሃይል ጥቃት እንደሚቀጥል ትላንት አስታውቋል፡፡  ይህም  እ.ኤ.አ. በጥር ወር የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ እየቀነሰ የመጣው የሁቲዎች ጥቃት ሊባባስ እንደሚችል የሚጠቁም ነው ተብሏል፡፡  ኢራን አጋር የሆኑት የሁቲ አማጽያን እስራኤል በጋዛ በዩናይትድ ስቴትስ በሽብር የተፈረጀው ሃማስ ቡድን ላይ በከፈተችው ጦርነት ምክንያት ለፍልስጤማውያን አጋርነት ለማሳየት በሚል ከእአአ ህዳር 2023 ጀምሮ በመርከብ ላይ ያነጣጠሩ ከ100 በላይ ጥቃቶችን ፈጽሟል፡፡  መሪው አል-ሁቲ በኩል «ለአራት ቀናት ቀነ ገደብ እንሰጣለን፡ ይህም የጊዜ ገደብም ለጋዛ የተኩስ አቁም አሸማጋዮች ለጥረታቸው ሲባል ነው» ብሏል፡፡  እ.ኤ.አ መጋቢት 2 ጀምሮ እስራኤል የእርዳታ መኪኖችን ወደ ጋዛ እንዳይገቡ አግዳለች፡፡ ሃማስ እርዳታዎችን በመስረቅ  ለፍልስጤማውያን እንዳይደርስ አድርጓል ስትልም ትከሳለች፡፡    

የደቡብ ኮሪያ  ፕሬዝዳንት ዩን ከእስር ተለቀቁ 

የደቡብ ኮሪያ ፍርድቤት በክስ ላይ የነበሩት ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል የእስር ማዘዣ እንዲሰረዝ መወሰኑን ተከትሎ አቃቢ ህግ በውሳኔው ላይ ይግባኝ ላለመጠየቅ በ
የአሜሪካ ድምፅ

የደቡብ ኮሪያ  ፕሬዝዳንት ዩን ከእስር ተለቀቁ 

የደቡብ ኮሪያ ፍርድቤት በክስ ላይ የነበሩት ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮል የእስር ማዘዣ እንዲሰረዝ መወሰኑን ተከትሎ አቃቢ ህግ በውሳኔው ላይ ይግባኝ ላለመጠየቅ በመወሰኑ ዛሬ በሴኡል ከሚገኘው እስርቤት ተለቀዋል፡፡  ዮን በእአአ ታህሳስ 3 ቀን ባሳለፉትና ለአጭር ጊዜ በቆየው የማርሻል ህግ ምክንያት ከስራቸው እንደታገዱ የሚቆዩ ሲሆን በአመፅ የቀረበባቸው ክስም እንዳለ ይቆያል ተብሏል፡፡  የወንጀል ጉዳዩ በስልጣን ላይ በሚኖራቸው ቆይታ ዙርያ ክሚታየው የፍርድ ሂደት የተለየ ሲሆን በህገ-መንግሥታዊው ፍርድ ቤት ወደ ሥራ ይመለሱ ወይም ከሥልጣናቸው ይነሱ በሚለው ጉዳይ ላይ በሚቀጥሉት ቀናት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል።   

አሜሪካ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪ አደረገች

ዋሽንግተን — የአሜሪካ መንግሥት፣ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በመቀጠል ላይ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥሪውን በድጋሚ አሰምቷል። የኤም 23 አማፂያን በርካታ ቦ
የአሜሪካ ድምፅ

አሜሪካ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ተኩስ አቁም እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪ አደረገች

ዋሽንግተን — የአሜሪካ መንግሥት፣ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ በመቀጠል ላይ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥሪውን በድጋሚ አሰምቷል። የኤም 23 አማፂያን በርካታ ቦታዎችን በመቆጣጠር ላይ ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካንን መንግሥት ጥሪ በድጋሚ ያሰሙት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ፣ የውጪ ጉዳይ ምኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ከዚህ በፊት በጉዳዩ ላይ ያሳዩትን አቋም በድጋሚ አንጸባርቀዋል። ሩቢዮ ከሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ እና ከኮንጎው ፕሬዝደንት ፊሊክስ ቸሰደኪ ጋራ መነጋገራቸውን ያወሱት ቃል አቀባዩ፣ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆምና ለተከሰተው የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጠያቂነት እንዲኖር ማስገንዘባቸውን ተናግረዋል። ለኮንጎ ሕዝብ እና ለኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሉአላዊነት ያላቸውን ድጋፍ የውጪ ጉዳይ ምኒስትሩ ማስታወቃቸውንም ቃል አቀባዩ አመልክተዋል። አሜሪካ በአንጎላው ፕሬዝደንት ሉዋንዳ ላይ ባለፈው ዓመት የተጀመረውንና የተኩስ ማቆም ስምምምነት እንዲፈረም ያስቻለውን ሂደት እንደምትደግፍም ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል። አሜሪካ በዲፕሎማሲ በኩል ግኑኙነቷን እንደምትቀጥልም ተናግረዋል። የአፍሪካ ኅብረት፣ የተመድ የጸጥታው ም/ቤት እንዲሁም አሜሪካ በኮንጎ የሚታየውን ሁከት አውግዘዋል። ተመድና አሜሪካ፣ ሩዋንዳ የኤም 23 አማፂያንን እንደምትደግፍና ሠራዊቷንም በምስራቅ ኮንጎ ማሰማራቷን ሲገልጹ፣ ሩዋንዳ ታስተባብላለች፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ላይ አሜሪካ ለ90 ቀናት የውጪ ርዳታ ማቋረጧ በሰብአዊ፣ ደኅንነትና ጤና መስኮች ሊደርስ የሚችለው ጉዳት እንደሚያሳስባቸው የአህጉሪቱ መሪዎች አሜሪካ አስታውቀዋል። የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ በበኩላቸው፣ የማቋረጡ ውሳኔ መንግሥት ለውጪ ርዳታዎች የሚውለውን ገንዘብ እንደገና ለመመልከት እና የሚሠራና የማይሠራውን ለመለየት ጊዜና ዕድል እንዲሰጠው ይረዳል ሲሉ ተከላክለዋል። ውሳኔው አሜሪካ ከዚህ በኋላ ርዳታ እንደማትሰጥ የሚያለክት ሳይኾን፣ ውጤታማ የሆነውን የርዳታ ዐይነት ለመለየት የሚጠቅም ነውም ብለዋል። ሰዎች ርዳታ እንዳይቋረጥባቸው ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚያመለክቱበት ሂደትም እንዳለ ጠቁመዋል።

የትረምፕ አስተዳደር ለኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ ሊሰጥ የነበረውን የ400 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ሰረዘ  

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር እንዳስታወቀው በኒዮርክ በሚገኘው የኮሎምብያ ዩንቨርስቲ ካምፓስና አካባቢው ባለው ፀረ ሴማዊ ትንኮ
የአሜሪካ ድምፅ

የትረምፕ አስተዳደር ለኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ ሊሰጥ የነበረውን የ400 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ሰረዘ  

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትረምፕ አስተዳደር እንዳስታወቀው በኒዮርክ በሚገኘው የኮሎምብያ ዩንቨርስቲ ካምፓስና አካባቢው ባለው ፀረ ሴማዊ ትንኮሳ ምክንያት ለዩንቨርስቲው ሊሰጡ የነበሩ ወደ 400 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱ ዕርዳታዎችን እና ውሎችን መሰረዙን አስታውቋል፡፡ ውሳኔው ትላንት ይፋ የተደረገው የፍትህ፣ የትምህርት ፣ የጤና እና የሰብአዊ አገልግሎት እንዲሁም የአጠቃላይ አገልግሎት አስተዳደር መምሪያዎች በጋራ ባወጡት መግለጫ ነው።  የትራምፕ አስተዳደር የገንዘብ ድጎማዎች እና ውሎች በመቋረጡ ሊጎዱ የሚችሉትን ዘርፎች አልያም የፀረ ሴማዊ ትንኮሳ ማስረጃውን ለመግለጽ ፈቃደኛ አይደለም፡፡ ይሁንና ይህ ድጋፍ ለዩንቨርስቲው ቃል ከተገባለት ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ  እርዳታ መካከል ተቀናሽ የሚሆን ነው ተብሏል፡፡  አብዛኛው የገንዘብ ድጋፍ ለጤና አጠባበቅና ሳይንሳዊ ምርምር የሚውል እንደሆነ ያስታወቀው የሮይተርስ ዘገባ አሃዞቹን ግን ማረጋገጥ አለመቻሉንም ገልጿል፡፡  ይፋ የተደረገው “የወዲያውኑ” ቅነሳዎች ህጋዊ ተግዳሮቶች ሊገጥሙት እንደሚችሉም ተገልጿል፡፡ የሲቪል መብት ተሟጋች ቡድኖች የኮንትራቱ መሰረዝ ተገቢውን ሂደት ያልተከተለና ጥበቃ ባላቸው መብቶች ላይ የተወሰደ ኢ-ህገመንግስታዊ ቅጣት ነው ሲሉ ተናግረዋል።  ባለፈው አመት የእስራኤልና የጋዛ ጦርነት በተቀጣጠለበት ወቅት የኮሎምቢያ ዩንቨርስቲ  የፍልስጤም ደጋፊዎችና ጸረ እስራኤል የተማሪዎች ተቃውሞ በግንባር ቀደምትነት ሲካሄድበት የነበረ ነው፡፡ 

በብዙ አገሮች የሽብር ጥቃቶች እየበረከቱ በመጡበት አፍሪካ አስከፊ ጥቃቶችን ማስተናገዷ ተዘገበ

ባለፈው ዓመት በዓለም እጅግ አውዳሚ መሆኑ የተነገረለት የአሸባሪዎች ጥቃት በአፍሪካ ሲፈፀም፤ የዓለም የምጣኔ ሃብት እና የሰላም ተቋም ይፋ ያደረገው የ2025 የዓ
የአሜሪካ ድምፅ

በብዙ አገሮች የሽብር ጥቃቶች እየበረከቱ በመጡበት አፍሪካ አስከፊ ጥቃቶችን ማስተናገዷ ተዘገበ

ባለፈው ዓመት በዓለም እጅግ አውዳሚ መሆኑ የተነገረለት የአሸባሪዎች ጥቃት በአፍሪካ ሲፈፀም፤ የዓለም የምጣኔ ሃብት እና የሰላም ተቋም ይፋ ያደረገው የ2025 የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች ጠቋሚ ሪፖርት እንዳመለከተው፤ በአጠቃላይ ከሽብር ጋር ከተዛመዱ ግድያዎች ከገሚስ በላይ የሚሆኑት የተፈጸሙት የዓለም አቀፍ የሽብር ጥቃቶች መናሃሪያ ሆኖ በቆየው የሳሕል ክልል ነው። በሁለት ሀገራት የደረሱትን 3 አደገኛ የሽብር ጥቃቶች ጨምሮ በዓለም ዙሪያ ከተዘገቡት 20 ያህል እጅግ የከፉ ጥቃቶች ውስጥም 17ቱ የተፈጸሙት በአፍሪካ ነው። ባለፈው ዓመት በሰኔ፣ በሀምሌ እና በነሀሴ ወር በኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የተፈጸሙት ጥቃቶች ለ607 ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክኒያት መሆናቸውን አክሎ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአውስትራሊያ ያደረገው ይሄው የጥናት ቡድን አረጋግጧል። በዚሁ ዓመት በሳህል ክልል ከግጭቶች ጋር ተያይዘው የደረሱ ሞቶች ቁጥር ከ25,000 በላይ ሰዎች የጠፋባቸው ድንገቶች ዓመታዊው ጥናታዊ ሪፖርት ይፋ መደረግ ከጀመረ ወዲህ ከተዘገቡት ሁሉ እጅግ ግዙፍ መሆኑ እና ከእነዚህም ውስጥ 3,885 ያህሉ በአሸባሪዎች የተፈጸሙ መሆናቸው ተመልክቷል። በመሰል የአሸባሪዎች ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ሃገራት ቀዳሚዋ ቡርኪና ፋሶ ስትሆን፤ ብርቱ ጉዳት ከደረሰባቸው ጥቂት የአፍሪካ ሀገሮች ማሊ፣ ኒጀር፣ ናይጄሪያ፣ ሶማሊያ እና ካሜሩን እንደሚገኙባቸው ታውቋል። ቡርኪና ፋሶ በዘገባዎች እንደተገለጸው ክፉኛ የተጎዳች ሀገር ብትሆንም፤ አጠቃላይ የጥቃት እና የሟቾች መጠን የሚያመለክቱ አሃዞች በጠቅላላው በ21 በመቶ እና በ57 ቀንሰዋል። ያም ሆኖ ቡርኪና አሁንም በአለም አቀፍ ደረጃ በአሸባሪዎች በሚደርሱ ጥቃቶች የከፋ አደጋ ከሚደርስባቸው አምስተኛዋ አገር ነች። በዓመቱ ውስጥ ቢያንስ አንድ የሽብር ጥቃት የደረሰባቸው ሀገራት ቁጥር ከ58 ወደ 66 ከፍ ማለቱንም ሪፖርት አክሎ አስፍሯል። ከዚህም ውስጥ ከእስላማዊው ጽንፈኛ ቡድን አይሲስ ጋር ቁርኝት ያላቸው ቡድኖች በዓለም ዙሪያ በ22 የተለያዩ አገሮች ውስጥ ባደረሷቸው የሽብር ጥቃቶች 1, 805 ሰዎች ተገድለዋል። በሌላ በኩል እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ2024 በሽብርተኞች የተፈጸሙ ጥቃቶች ቁጥር ወደ 7,555 ዝቅ ማለቱ ሲዘገብ፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ13 በመቶ ያነሰ መሆኑ ታውቋል።  

በ62 ግብር ከፋዮች ላይ የጉዞ እግድ ተላለፈ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ፣ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የታክስ ዕዳ አለባቸው ባላቸው 62 ግብር ከፋዮች ላይ ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን አስታወቀ
የአሜሪካ ድምፅ

በ62 ግብር ከፋዮች ላይ የጉዞ እግድ ተላለፈ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ፣ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር የታክስ ዕዳ አለባቸው ባላቸው 62 ግብር ከፋዮች ላይ ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን አስታወቀ፡፡ ስለጉዳዩ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ የሰጡት፣ የተቋሙ የኮምዩኒኬሽንስ ዲሬክተር አቶ ሰውነት አየለ፣ ከጉዞ እግዱ በተጨማሪ ቢሮው ሌሎች አስተዳደራዊ ርምጃዎችንም እየወሰደ መኾኑን ተናግረዋል፡፡ በእግዱ ዙርያ አስተያየት የሰጡን አንድ የሕግ ባለሞያ ደግሞ፣ ቢሮው ይህን የማድረግ ሥልጣን በዐዋጅ እንደተሰጠው ገልጸው፣ ነገር ግን የዚህ ዐይነት ውሳኔ የሚተላለፈው፣ ታክስ ከፋዩ ግለሰብ ከሀገር ሊወጣ ይችላል የሚል በቂ ምክንያት ሲኖር ብቻ ነው ብለዋል፡፡ ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ትራምፕ የያደረጉትን የቀረጥ ጭማሪ ተከትሎ ቻይና ‘የአፀፋ ርምጃ እወስዳለሁ’ ስትል አስጠነቀቀች

ቤጂንግ «በዘፈቀደ የተፈጸመ» ላለችው የትራምፕ አስተዳደር ለደነገገው ተጨማሪ የቀረጥ የአጸፋ መልስ እሰጣለሁ ስትል አስጠንቅቃለች። የቻይናው የውጭ
የአሜሪካ ድምፅ

ትራምፕ የያደረጉትን የቀረጥ ጭማሪ ተከትሎ ቻይና ‘የአፀፋ ርምጃ እወስዳለሁ’ ስትል አስጠነቀቀች

ቤጂንግ «በዘፈቀደ የተፈጸመ» ላለችው የትራምፕ አስተዳደር ለደነገገው ተጨማሪ የቀረጥ የአጸፋ መልስ እሰጣለሁ ስትል አስጠንቅቃለች። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ “መልካምን በክፉ ትመልሳለች” ሲሉም ዩናይትድ ስቴትስን ወንጅለዋል። የአሜሪካ ድምጹ ቢል ጋሎ እንደዘገበው፣ ይህ ቤጂንግ ራሷን ለዓለም መረጋጋት የቆመ ኃይል አድርጋ ለማሳየት የምታደርገው ጥረት አካል መሆኑን ጠቁሟል። ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

ጥንቃቄ የሚሻው የወጣቶች የማኅበራዊ ሚድያ አጠቃቀም

በኢትዮጵያ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት የሚሰራጩ ሐሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጩ እና በሀገር ውስጥ ለሚካሄዱ የተለያዩ
የአሜሪካ ድምፅ

ጥንቃቄ የሚሻው የወጣቶች የማኅበራዊ ሚድያ አጠቃቀም

በኢትዮጵያ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት የሚሰራጩ ሐሰተኛ መረጃዎች እና የጥላቻ ንግግሮች በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጩ እና በሀገር ውስጥ ለሚካሄዱ የተለያዩ ግጭቶች መባባስ ምክንያት እየሆኑ መሄዳቸውን ተከትሎ፣ ስለሀሰተኛ መረጃ ምንነት እና መረጃን ከተለያዩ ምንጮች የማጣራት ክህሎት የሚያስጨብጥ የሚዲያ አጠቃቀም ትምህርት ወሳኝ መሆኑን በርካታ ጥናቶች ያመለከታሉ። ተማሪዎች እና ወጣቶች በማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ ያላቸው እውቀት ምን እንደሚመስል ጠይቀናቸዋል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።  

ዶናልድ ትረምፕ የኑክሌር ድርድር እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለኢራን ላኩ

የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከኢራን ጋራ የኑክሌር ድርድር ማድረግ እንደሚሹ ለሀገሪቱ መሪዎች ትላንት ሐሙስ ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል። የኢራ
የአሜሪካ ድምፅ

ዶናልድ ትረምፕ የኑክሌር ድርድር እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለኢራን ላኩ

የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ከኢራን ጋራ የኑክሌር ድርድር ማድረግ እንደሚሹ ለሀገሪቱ መሪዎች ትላንት ሐሙስ ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል። የኢራን መሪዎች ለመነጋገር ይስማማሉ ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ትረምፕ አስታውቀዋል። ትረምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋራ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፣ ኢራን ለድርድር ትቀርባለች ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉና፣ ይህም ለኢራን መልካም ሁኔታዎችን ሊፈጥር እንደሚችል ጠቁመዋል። “ደብዳቤውን ለማግኘት የፈለጉ ይመስለኛል፣ ሌላው አማራጭ ግን አንድ ነገር ማድረግ ይኖርብናል፣ ምክኒያቱም የኑክሌር መሣሪያ እንዲኖራቸው መፍቀድ  አይቻልም “ ብለዋል ትረምፕ፡፡ ደብዳቤው የተላከው ለኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ ኻሚኒ እንደሆነ  የተገመተ ሲሆን፣ ይህንኑ ከኋይት ሃውስ ለማጣራት የተደረገው ሙከራ መልስ ባለመገኘቱ እንዳልተሳካ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል። የሩሲያው ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ርያብኮቭ የኢራንን የኑክሌር ፕሮግራም አስመልክቶ የተፈጠረውን ውዝግብ ለመፍታት የሚደረገውን ዓለም አቀፍ ጥረት በተመለከተ ከኢራኑ አምባሳደር ካዜም ጃላሊ ጋራ እንደተወያዩ የሩሲያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ዓርብ አስታውቋል።

ሩቶና ኦዲንጋ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ከቀድሞው ዋና ተፎካካሪያቸው ከራይላ ኦዲንጋ ጋራ በፖለቲካ ጉዳዮች ትብብር ለማድረግ ስምምነት ተፈራርመዋል። ሁለቱ ወገኖ
የአሜሪካ ድምፅ

ሩቶና ኦዲንጋ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

የኬንያው ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ከቀድሞው ዋና ተፎካካሪያቸው ከራይላ ኦዲንጋ ጋራ በፖለቲካ ጉዳዮች ትብብር ለማድረግ ስምምነት ተፈራርመዋል። ሁለቱ ወገኖች እየጨመረ ያለውን የሃገሪቱን ዕዳ እና ሙስናን ጨምሮ ሌሎቹንም ሃገሪቱን የገጠሟትን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ አብረው ለመሥራት ተስማምተዋል። ሩቶ የግብር ጭማሪ እንደሚያደርጉ ማስታወቃቸውን ተከትሎ በሃገሪቱ በተነሳው ተቃውሞ ቢያንስ 60 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። የነበራቸው የሕዝብ ድጋፍም እያሽቆለቆለ መጥቷል። ተቃውሞው በመበርታቱም ሩቶ ከተቃዋሚያቸው ከኦዲንጋና ከበርካታ የፓርቲ አባሎቻቸው ጋራ”ሰፊ መሠረት ያለው” መንግሥት ለመመስረት እንዲሠሩ አስገድዷቸዋል። ይህንን ስምምነትም ዛሬ በይፋ በመፈረም ሃገሪቱ የገጠማትን ችግሮች ለመቅረፍ በጋራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል። ጉምቱ የተቃዋሚ ፖለቲከኛው ራይላ ኦዲንጋ በኬንያ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ አምስት ጊዜ ተሳትፈው ሳይቀናቸው ቀርቷል። ስምምነቱ በሃገር ውስጥ ያለውን ውጥረት ለማርገብ ያለመ እንደሆነ የ80 ዓመቱ ኦዲንጋ አስታውቀዋል። ሩቶ በበኩላቸው ስምምነቱ “ነፃነትና መልካም አጋጣሚዎች ለሁሉም መድረሳቸውን ማረጋገጫና ወደ ተስፋይቱ ምድር የሚወስድ መንገድም ነው” ብለዋል። የፖለቲካ ተንታኞች ስምምነቱን «እየተንኮታኮተ ያለው አገዛዝ እንዲያንሰራራ የተደረገ ሙከራ» ሲሉ ገልጸውታል።

በርእደ መሬት ጉዳት ሥራ ያቆመው የከሰም ስኳር ፋብሪካ በርካታ ሠራተኞቹን ሊያሰናብት ነው

በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በተደጋጋሚ ባጋጠመው ርእደ መሬት የመፍረስ ጉዳት የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፣ በሺሕ ለሚቆጠሩ ሠራተኞቹ የመጨረሻ የስ
የአሜሪካ ድምፅ

በርእደ መሬት ጉዳት ሥራ ያቆመው የከሰም ስኳር ፋብሪካ በርካታ ሠራተኞቹን ሊያሰናብት ነው

በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በተደጋጋሚ ባጋጠመው ርእደ መሬት የመፍረስ ጉዳት የደረሰበት የከሰም ስኳር ፋብሪካ፣ በሺሕ ለሚቆጠሩ ሠራተኞቹ የመጨረሻ የስንብት ማስታወቂያ አወጣ፡፡ የፋብሪካው ሠራተኞች ማኅበር ውሳኔውን «አግባብነት የሌለው» ሲል ተችቷል፡፡ «ፋብሪካው ለሠራተኞቹ የስንብት ማስታወቂያ ከማውጣቱ በፊት ሌሎች አማራጮችን መመልከት ነበረበት፤» ብሏል ማኅበሩ፡፡ የፋብሪካው ሠራተኞች በበኩላቸው፣ «በስንብት ማስታወቂያው ተደናግጠናል፡፡ ውሳኔው አኹን ያለውን የኑሮ ውድነት እና የጸጥታ ስጋት ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው፤» ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ የፋብሪካው አመራሮች፣ ውሳኔያቸውን አስመልክቶ እስከ አኹን ለብዙኃን መገናኛ የሰጡት መግለጫ የለም፡፡ የአሜሪካ ድምፅም ተደጋጋሚ ሙከራ አድርጎ አልተሳካለትም፡፡ የአገሪቱን የስኳር ፋብሪካዎች በበላይነት የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፣ ፋብሪካው ሠራተኞቹን ለማስቀጠል በሚያስችል ቁመና ላይ አይደለም፤ ብሏል፡፡ የአገር አቀፍ እርሻ እና አግሮ ኢንዱስትሪ ሠራተኛ ማኅበራት ፌዴሬሽን ደግሞ፣ በሠራተኞቹ ላይ ስለደረሰው ጉዳት እና በመጻኢ ዕድላቸው ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋራ እየተወያየ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል በኮሌራ ወረርሽኝ የሟቾች ቀጥር ከ30 መብለጡ ተገለጸ

በጋምቤላ ክልል በኑዌር ዞን በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ30 በላይ ሰዎች መሞታቸውንና ከአንድ ሺሕ በላይ የሚደርሱ ደግሞ በበሽ
የአሜሪካ ድምፅ

በጋምቤላ ክልል በኮሌራ ወረርሽኝ የሟቾች ቀጥር ከ30 መብለጡ ተገለጸ

በጋምቤላ ክልል በኑዌር ዞን በተከሠተው የኮሌራ ወረርሽኝ፣ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ30 በላይ ሰዎች መሞታቸውንና ከአንድ ሺሕ በላይ የሚደርሱ ደግሞ በበሽታው መታመማቸውን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ። የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ሓላፊ አቶ ጋትቤል ግርማ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ ወረርሽኙ ቀድሞ የተከሠተባቸው ዋንታዎ እና አኮቦ ወረዳዎች፣ አኹንም ስርጭቱ ከፍተኛ እንደኾነ ጠቅሰው፣ መድኃኒትም በበቂ ኹኔታ አልቀረበም፤ ብለዋል። ከጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት፣ ወደ ከፍተኛ አመራሮች ስልክ ብንደውልም ጥሪው ባለመነሣቱ ምክንያት ምላሻቸውን ማካተት አልቻልንም።  

የአሜሪካ እና የካናዳ መሪዎች ስለዘገዩት ቀረጦች እና ስለ ንግድ ነክ ጉዳዮች ተወያዩ

የዩናይትድ ስቴትስ እና የካናዳ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ትላንት ረቡዕ በንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች ውይይት አካሂደዋል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ት
የአሜሪካ ድምፅ

የአሜሪካ እና የካናዳ መሪዎች ስለዘገዩት ቀረጦች እና ስለ ንግድ ነክ ጉዳዮች ተወያዩ

የዩናይትድ ስቴትስ እና የካናዳ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ትላንት ረቡዕ በንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች ውይይት አካሂደዋል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕም፣ ከካናዳ እና ከሜክሲኮ በሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ አዲስ የተጣለውን የ25 ከመቶ ቀረጥ ለአንድ ወር አዘግይተዋል ። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የካናዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ «በጋራ ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች፣ በድንበር ደህንነት መጠናከር ፣ በንግድ ልውውጥ እና የኢኮኖሚ ብልጽግና» ሁለቱ ሀገሮች በትብብር መሥራታቸውን ለመቀጠል ስለሚችሉበት መንገድ መወያየታቸውን የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ትረምፕ ቀረጡን ማዘግየታቸውን ከማስታወቃቸው በፊት ከትላልቆቹ የዩናይትድ ስቴትስ መኪና አምራቾች፣ ከፎርድ፣ ጀነራል ሞተርስ እና ስቴላንቲስ የሥራ አስፈፃሚዎች ጋር መነጋገራቸውን የኋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ካሮላይን ሌቪት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡ ትረምፕ መኪና አምራቾቹ፣ የማምረቻ ቦታዎቻቸውን ከሜክሲኮ እና ካናዳ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በማዞር የሚጣልባቸውን ቀረጥ በጠቅላላ ማስወገድ እንዲችሉ ያሳሰቧቸው መሆኑንም ቃል አቀባይዋ አክለዋል፡፡ ትረምፕ በሁለቱ ትላልቆቹ የአሜሪካ የንግድ ሸሪኮች ሌሎች ምርቶች ላይ የጣሏቸው አዲሶቹ ቀረጦች እንዳለ እንደሚቆዩ ሌቪት ገልጸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሌሎችንም ምርቶች ከቀረጥ ነጻ ማድረግ የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ካሉ ለማጤን ዝግጁ መሆናቸውን ቃል አቀባይዋ ተናግረዋል፡፡ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ሀገራቸው ላይ የተጣሉ ሁሉም የአሜሪካ ቀረጦች እስካልተነሱ ድረስ፣ ካናዳ በአጸፋው የጣለቻቸውን ቀረጦች ለማስወገድ ፈቃደኛ አልሆኑም ። የኦንታርዮ ክፍለ ግዛት አገረ ገዥ ደግ ፎርድ “ወደ አሜሪካ በሚላኩ የካናዳ ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው ቀረጥ ባለበት ከቀጠለ በካናዳ የሚገኙ የተሽከርካሪ ማምረቻዎች በ10 ቀናት ውስጥ መዘጋት ይጀምራሉ” ብለዋል፡፡ “ሰዎች ሥራቸውን ያጣሉ” ሲሉም ፎርድ አክለዋል፡ የካናዳ የክልል መሪዎች በዩናይትድ ስቴትስ ገበያ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ከሌሎች አገሮች ጋር የንግድ ልውውጥን ለማስፋት እየሰሩ ነው፡፡ ትረምፕ በቻይና ምርቶች ላይ የጣሉትን ቀረጥ በእጥፍ በማሳደግ 20 ከመቶ በማድረሳቸው የአክሲዮን ገበያው እንዲያሽቆለቁል እና ሸማቾች ላይ ዋጋ የመጨመር ስጋት እንዲፈጠር አድርጓል። ሜክሲኮ፣ ካናዳ እና ቻይና ለትረምፕ እርምጃ በአሜሪካ ምርቶች ላይ የአጸፋ ቀረጥ እንደሚጥሉ አስታውቀዋል። ፕሬዝደንት ትረምፕ በትሩዝ ሶሻል መድረካቸው ላይ ባወጡት ጽሁፍ «ትሩዶ ሀገራቸው ላይ የተጣሉትን አዳዲስ ቀረጦች በሚመለከት ምን ማድረግ እንደሚቻል ትላንት ረቡዕ ስልክ ደውለው ጠይቀውኝ ነበር፡፡ እኔም በካናዳ እና በሚከሲኮ ድንበር በኩል የሚገባው ፈንቲኔል ብዙ ሰው ገድሏል፡፡ ያ መቆሙን የሚያሳምን ነገር አላገኘሁም አልኳቸው፡፡ ከበፊቱ ተሻሽሏል አሉ፡፡ እሱ በቂ እንዳልሆነ ነግሬአቸዋለሁ » ብለዋል፡፡

አሜሪካ የመረጃ ልውውጥ ማቋረጧን ተከትሎ ፈረንሳይ ለዩክሬን የስለላ መረጃ ማጋራት ቀጥላለች

የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስትር ሴባስቲየን ለኮርኑ ሀገራቸው ለዩክሬን የስለላ መረጃ እያጋራች መሆኗን ዛሬ ሐሙስ ተናገሩ፡፡ ርምጃው ዩናይትድ ስቴትስ ከዩክሬ
የአሜሪካ ድምፅ

አሜሪካ የመረጃ ልውውጥ ማቋረጧን ተከትሎ ፈረንሳይ ለዩክሬን የስለላ መረጃ ማጋራት ቀጥላለች

የፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስትር ሴባስቲየን ለኮርኑ ሀገራቸው ለዩክሬን የስለላ መረጃ እያጋራች መሆኗን ዛሬ ሐሙስ ተናገሩ፡፡ ርምጃው ዩናይትድ ስቴትስ ከዩክሬን ጋራ የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ አቋርጫለሁ ማለቷን ተከትሎ የተሰማ ነው። ርምጃው የተወሰደው የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች በብራሰልስ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜለንስኪ በተገኙበት  የመከላከያ ወጪያቸውን በማሳደግ እና ዩክሬን ከሩሲያ ጋራ በምታደርገው ጦርነት ድጋፍ ለመስጠት ቃል ስለ መግባት ውይይት ባደረጉበት በዛሬው ዕለት መሆኑ  ነው፡፡ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከውይይቱ በፊት የአውሮፓ ኅብረት አባላት “ወደፊት ወሳኝ ርምጃዎችን እንደሚወስዱ” ተናግረዋል፡፡ በአዲሱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን ስለምትሰጠው ድጋፍ በወሰደው የአቋም ለውጥ ስጋት ያላቸው መሆኑንም ማክሮን ገልጸዋ፡፡ «የአውሮፓ የወደፊት ዕጣ ፈንታ በዋሽንግተን ወይም በሞስኮ መወሰን የለበትም» ብለዋል ማክሮን፡፡ ትረምፕ ባለፈው ሳምንት ከዘሌንስኪ ጋራ በኋይት ሀውስ ካደረጉት አወዛጋቢ ውይይት በኋላ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለኪቭ ተዋጊዎች የምትሰጠውን ወታደራዊ ርዳታ እንድታቆም በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ አዘዋል። የየዩናይትድ ስቴትስ የማዕከላዊ ስለላ ድርጅት (ሲአይኤ) ዳይሬክተር ጆን ራትክሊፍ ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ለጊዜው የስለላ መረጃ ለኪቭ መረጃ ማጋራቷን ማቆሟን ትላንት ረቡዕ ተናግረዋል:: ሆኖም ዘሌንስኪ በኋይት ሀውስ ከትረምፕ ጋራ የነበራቸውን ልውውጥ “የሚጸጽት” በማለታቸውን እና ሀገራቸው  ከሩሲያ ጋራ ለሚደረገው የሰላም ድርድር ዝግጁ መሆኗን በመናገራቸው  የመረጃ ልውውጡ መቋረጥ ለረጅም ጊዜ ላይቆይ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡

Get more results via ClueGoal