Select a country

VOA60 America - US envoy in Beirut for talks with Lebanese officials

U.S. envoy Amos Hochstein visited Lebanon on Monday amid Biden administration efforts to halt the fighting between Israel and Hezbollah.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - US envoy in Beirut for talks with Lebanese officials

U.S. envoy Amos Hochstein visited Lebanon on Monday amid Biden administration efforts to halt the fighting between Israel and Hezbollah.

VOA60 World - Gulen, powerful cleric accused by Turkey of orchestrating a Turkish coup, dies

Turkish Muslim preacher Fethullah Gulen, who Ankara says was behind a 2016 failed coup against Turkish leader Tayyip Erdogan, has died at the age of 83 in the United States. The cleric had lived in the United States since 1999, when he came to seek medical tr
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Gulen, powerful cleric accused by Turkey of orchestrating a Turkish coup, dies

Turkish Muslim preacher Fethullah Gulen, who Ankara says was behind a 2016 failed coup against Turkish leader Tayyip Erdogan, has died at the age of 83 in the United States. The cleric had lived in the United States since 1999, when he came to seek medical treatment.

በጀርመን እስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ በማሴር የተጠረጠረ ሊቢያዊ በቁጥጥር ስር ዋለ

በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል ተብሎ የተጠረጠረ እና ከእስላማዊ መንግስት ቡድን ጋር ግንኙነት እንዳለው የተገለጸው ሊቢያዊ
የአሜሪካ ድምፅ

በጀርመን እስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ በማሴር የተጠረጠረ ሊቢያዊ በቁጥጥር ስር ዋለ

በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል ተብሎ የተጠረጠረ እና ከእስላማዊ መንግስት ቡድን ጋር ግንኙነት እንዳለው የተገለጸው ሊቢያዊ ተጠርጣሪ እሁድ ፍርድቤት እንደሚቀርብ የጀርመን አቃብያነ ህጎች አስታወቁ።  ስሙ ኦማር ኤ. እንደሆነ የተገለጸው ተጠርጣሪ፣ ቅዳሜ ምሽት በቁጥጥር ስር የዋለው፣ ከጀርመን ዋና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኘው በርናው ከተማ መኖሪያ ቤቱ ውስጥ መሆኑን የፌደራል አቃቢያነ ህጎች ቢሮ አመልክቷል።  ቢሮው አክሎ፣ ኦማር ኤ. በርሊን በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ላይ «በጦር መሳሪያ የታገዘ ከፍተኛ ጥቃት ለማድረስ አቅዷል» የሚል ክስ እንደተመሰረተበት አመልክቷል። የእስላማዊ መንግስት ርዕዮተ ዓለም ደጋፊ መሆኑን የገለጸው አቃቤ ህግ፣ ለጥቃቱ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅትም «ከእስላማዊ መንግስት አባላት ጋር በማህበራዊ ሚዲያ መልዕክት ተለዋውጧል» ብሏል።  በርሊን የሚገኙት የእስራኤል አምባሳደር ሮን ፕሮሶር በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት «የሙስሊም ፀረ-ሴማዊነት፣ ትርክት ብቻ ሳይሆን በዓለም ዙሪያ የሽብር ድርጊቶችን የሚያበረታታ እና የሚያነሳሳ ነው» ብለዋል። አክለውም የእስራኤል ኤምባሲዎች «በዲፕሎማሲው ጦር ሜዳ ግንባር ተሰላፊ ናቸው» ሲሉም አመልክተዋል።  የጀርመን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ናንችይ ፌዘር በበኩላቸው፣ በጀርመን የሚገኙ አይሁዳውያንን እና የእስራኤል ተቋማትን መጠበቅ «ከምንም በላይ ቅድሚ የምንሰጠው ነው» ያሉ ሲሆን፣  የሕግ አስከባሪ አካላት ማንኛውንም እስላማዊ፣ ፀረ-ሴማዊ እና ፀረ-እስራኤል ጥቃቶችን ለመከላከል ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረጉ መሆናቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

እስራኤል በባህር ኃይል የንግድ ትርዒት እገዳ ምክንያት በማክሮን ላይ ህጋዊ እርምጃ ልትወስድ ነው

በፓሪስ በሚካሄደው ወታደራዊ የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እስ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በባህር ኃይል የንግድ ትርዒት እገዳ ምክንያት በማክሮን ላይ ህጋዊ እርምጃ ልትወስድ ነው

በፓሪስ በሚካሄደው ወታደራዊ የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ተከትሎ፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፣ መስሪያቤታቸው በፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ላይ ክስ እንዲመሰርቱ ማዘዛቸውን እሁድ እለት አስታውቀዋል።  የእስራኤል ተቋማትን የማገድ ውሳኔው፣ እስራኤል በጋዛ እና ሊባኖን እያካሄደችው ባለው ጦርነት ምክንያት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተባባሰ የሄደው የማክሮን መንግስት ቅሬታ አካል ነው። እ.አ.አ ከህዳር 4 -7 በፓሪስ የሚካሄደው የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት አዘጋጅ ኢዩሮናቫል ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ፣ የፈረንሳይ መንግስት፣ የእስራኤል ልዑካን በትርዒቱ ላይ መሳተፍም ሆነ መሳሪያዎቻቸውን ማሳየት እንደማይችሉ ማሳወቁን አመልክቷል። ውሳኔው ሰባት ተቋማት ላይ ተፅእኖ ማሳደሩንም ጠቅሷል።   ውሳኔውን ተከትሎ ካትዝ በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈረው መልዕክት «የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት፣ በመጪው ወር ፓሪስ ላይ በሚካሄደው የባህር ኃይል የንግድ ትርዒት ላይ የእስራኤል ተቋማት ምርቶቻቸውን እንዳያሳዩ በመከልከላቸው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሕጋዊ እና ዲፕሎማሲያዊ እርምጃ እንዲወስድ መመሪያ ሰጥቻለሁ» ብለዋል።  ካትዝ አክለው «ለሁለተኛ ጊዜ በእስራኤል ተቋማት ላይ የተጣለው እቀባም ሆነ ተቀባይነት የሌላቸው ቅድመ ሁኔታዎች ዲሞራሲያዊ ያልሆኑ ከመሆናቸውም በላይ፣ በሁለት ወዳጅ ሀገሮች መካከል ተቀባይነት የሌላቸው ናቸው» ያሉ ሲሆን ፕሬዝዳንት ማክሮን ውሳኔያቸውን ሙሉ ለሙሉ እንዲሰርዙ አሳስበዋል። 

እስራኤል በጋዛ ጥቃት 73 ሰዎችን ስትገድል፣ በቤይሩት ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች

እስራኤል በሊባኖስ ዋና ከተማ የሂዝቦላህ «የትዕዛዝ ማዕከል» ነው ባለችው ዒላማ ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ጦርነቱ እሁድ እለት በሁለት ግንባር የተካሄ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በጋዛ ጥቃት 73 ሰዎችን ስትገድል፣ በቤይሩት ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች

እስራኤል በሊባኖስ ዋና ከተማ የሂዝቦላህ «የትዕዛዝ ማዕከል» ነው ባለችው ዒላማ ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ጦርነቱ እሁድ እለት በሁለት ግንባር የተካሄደ ሲሆን፣ በጋዛ ባካሄደችው የአየር ጥቃትም 73 ሰዎች መገደላቸውን የነፍስ አድን ሰራተኞች አስታውቀዋል።  የሂዝቦላህ ጠንካራ ይዞታ በሆነው ደቡባዊ ቤይሩት ላይ ጥቃቱ የተካሄደው፣ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በኢራን የሚደገፈው ቡድን መኖሪያ ቤታቸውን ዒላማ በማድረግ ሊገድሏቸው እንደሞከረ ገልጸው ከከሰሱ በኃላ ነው።  የእስራኤል ጥቃት ሃረት ሄሪክ ውስጥ በአንድ መስጊድ እና ሆስፒታል አቅራቢያ የሚገኝ የመኖሪያ ህንፃ መምታቱን የሊባኖስ ብሐራዊ የዜና ማሰራጫ አስታውቋል።  የእስራኤል ጦር በበኩሉ በቤይሩት የሚገኘውን «የሂዝቦላህ የስለላ ድርጅት ዋና ማዕከል» እና የምድር ውስጥ ጦር መሳሪያ ማከማቻ መምታቱን እና በሌሎች ጥቃቶች ደግሞ ሦስት የሂዝቦላህ ታጣቂዎች መግደሉን አስታውቋል።  እስራኤል ጥቃቱን ካደረሰች ደቂቃዎች በኃላ፣ ከሊባኖስ አቅጣጫ 70 ሚሳይሎች ወደ እስራኤል መተኮሳቸውን እና ሁሉንም አየር ላይ እንዳሉ ማክሸፋቸውንም ጦሩ ጨምሮ ገልጿል።  በሌላ በኩል እስራኤል በጋዛ ሰሜናዊ ግዛት ቤይት ላሃ በተሰኘ አካባቢ፣ መኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 73 ፍልስጠማውያን መገደላቸውን የጋዛ ሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ አስታውቋል።  

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት አለቃቸውን 'ጨካኝ' ሲሉ ከሰሷቸው

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ እሁድ እለት፣ አለቃቸውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ «ጨካኝ» እና «አረመኔ» ሲሉ በ
የአሜሪካ ድምፅ

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት አለቃቸውን 'ጨካኝ' ሲሉ ከሰሷቸው

ከስልጣናቸው የተባረሩት የኬንያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ እሁድ እለት፣ አለቃቸውን ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ «ጨካኝ» እና «አረመኔ» ሲሉ በመንቀፍ፣ ህይወታቸው አደጋ ላይ ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።  ጋቻጉዋ ሐሙስ እለት በህግ መወሰኛ ምክርቤት ፊት ከተከሰሱባቸው 11 ክሶች አምስቱ ተቀባይነት በማግኘታቸው ከስልጣናቸው የተነሱ ሲሆን፣ በምትካቸው ሌላ የመሾሙን ሂደት ግን የፍርድ ቤት ውሳኔ አግዶታል።  «ፕሬዝዳንት እንዲሆን የረዳሁት፣ ያመንኩት እና እሱን በመደገፌ የተሳደድኩበት ሰው እንዴት በእኔ ላይ ይህን ላክል ጨካኝ ሊሆን እንደቻለ አስደንግጦኛል» ብለዋል ጋቻጉዋ። የ59 ዓመቱ አዛውንት የተመደቡላቸው የፀጥታ አካላት መነሳታቸውን እና ሁሉም ሰራተኞቻቸው አስገዳጅ እረፍት እንዲወጡ መደረጋቸውንም ገልጸው «በእኔ ላይ ወይም በቤተሰቤ ላይ የሆነ ነገር ቢደርስ፣ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ተጠያቂ መሆን አለባቸው» ሲሉ ተናግረዋል።  ጋቻጉዋ ይህንን ንግግር ያደረጉት፣ በደረታቸው ላይ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በዋና ከተማዋ ናይሮቢ ሲታከሙበት ከነበረው ሆስፒታል ከወጡ በኃላ ነው።  «ይህን አይነት መጠን ያለው ጭካኔ አይገባኝም» ያሉት ጋቻጉዋ «አንድ ሰው በህይወቱ እጅግ በጣም መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ባለበት ወቅት እና በህይወት ለመቆየት በሚፍጨረጨርበት ወቅት፣ ሆን ተብሎ እንደዚህ አይነት ጭካኔ ይፈፀምበታል» ብለዋል። 

በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት ተቃጣ

የኢራኑ መሪ ባለፈው ዓመት በጎሮጎርሳዊያኑ ጥቅምት ሰባት ሀማስ የፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ዋናየእቅዱ መስራች የሆኑት የሀማሱ መሪ መገደላቸውን ተከትሎ፤ ሀማስ ከ
የአሜሪካ ድምፅ

በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ላይ ጥቃት ተቃጣ

የኢራኑ መሪ ባለፈው ዓመት በጎሮጎርሳዊያኑ ጥቅምት ሰባት ሀማስ የፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ዋናየእቅዱ መስራች የሆኑት የሀማሱ መሪ መገደላቸውን ተከትሎ፤ ሀማስ ከእስራኤል ጋር የሚያደርገውንትግል እንደሚቀጥል ቃል በገቡበት ወቅት፤ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ መኖሪያ ቤትን ዒላማ ያደረገ የድሮን ጥቃት ምንም ዓይነት ጉዳት ሳያደርስ መክሸፉን የእስራኤል መንግስት ዛሬቅዳሜ ተናግሯል።   በአንጻሩ በጋዛ፣ የሆስፒታል ባለስልጣናት እና የአሶሺየትድ ፕሬስ ዘጋቢ እንደገለፁት  እስራኤል በፈጸመቻቸው የተለያዩ  ጥቃቶች ህጻናትን ጨምሮ በትንሹ 21 ሰዎች ተገድለዋል።   ዛሬ ቅዳሜ ማለዳ ከሊባኖስ አቅጣጫ የመጣውን የሰው አልባ ድሮን ጥቃት የሚያስጠነቅቁ ድምጾች በእስራኤል በከፍተኛ ሁኔታ ሲጮሁ ነበር ያለው የእስራኤል መንግስት ቃል አቀባይ  መግለጫ፤  ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በቂሳሪያ በሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት እሳቸውም ሆኑ ባለቤታቸው እንዳልነበሩ አስታውቆ  በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ብሏል።    በመስከረም ወር የየመን ሁቲ አማፂያን የኔታኒያሁ አይሮፕላን በቴል አቪቭ በሚገኘው ቤን ጉሪዮን አየርማረፊያ ሲያርፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ማስወንጨፋቸው ይታወሳል።   የኔታኒያሁ መኖሪያ ቤትን ዒላማ ካደረገው የድሮን ጥቃት  በተጨማሪ ቅዳሜ ማለዳ ላይ በሰሜንእስራኤል ከሊባኖስ የተነሱ ወደ 55 የሚጠጉ ዒላማዎች ላይ መተኮሱን የእስራኤል ጦር አስታውቋል።የተወሰኑት መክነዋል የተባለ ሲሆን፤ በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ እስካሁን  የተገለጸ ነገር የለም።

የቡድን ሰባት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ ተጀመረ

በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየተባባሰ እና የዩክሬን ጦርነት ሦስተኛ ክረምቱን እየያዘ ባለበት በዚህ የውጥረት ወቅት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መከላከ
የአሜሪካ ድምፅ

የቡድን ሰባት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ ተጀመረ

በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ግጭት እየተባባሰ እና የዩክሬን ጦርነት ሦስተኛ ክረምቱን እየያዘ ባለበት በዚህ የውጥረት ወቅት የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መከላከያ ሚንስትሮች ጉባኤ በጣሊያን ተጀምሯል።   የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ወቅታዊ ፕሬዝዳንትነቱን የያዘችው ጣሊያን የሰሜን አትላንቲክ የቃልኪዳን ጦር ኔቶ መቀመጫ በሆነችው ኔፕልስ ጉባኤውን እያስተናገደች ነው።   ለኔቶ ሀላፊ ማርክ ሩቴ እና ለአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ሃላፊ ለሆኑት ጆሴፍ ቦሬል እንዲሁም ለጉባኤው ታዳሚዎች አቀባበል ያደርጉት የጣሊያኑ የመከላከያ ሚንስትር ጉዓዶ ክሮሴቶ “ዛሬ እዚህ መሰባሰባችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓታችንን ለመገደብ ለሚጥሩ ሁሉ ጠንካራ መልዕክት ያስተላልፋል ብዬ አምናለሁ” በማለት ተናግረዋል።   ጉባኤው በዋናነት የዩክሬን ጦርነት ላይ ትኩረቱን ቢያደርግም በአፍሪካ እና በፓስፊክ እስያ የጸጥታ ጉዳዮችም ላይ የሚወያይ ይሆናል።  

የኬኒያ ፍርድ ቤት የምክትል ፕሬዝዳንት ምርጫውን አገደ

የኬኒያ ህግ አውጭዎች የሀገሪቱን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጓን በከባድ የስነ ምግባርጉድለት እና ፕሬዚዳንቱን በማቃለል ክስ ከስልጣናቸው እንዲነ
የአሜሪካ ድምፅ

የኬኒያ ፍርድ ቤት የምክትል ፕሬዝዳንት ምርጫውን አገደ

የኬኒያ ህግ አውጭዎች የሀገሪቱን የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪጋቲ ጋቻጓን በከባድ የስነ ምግባርጉድለት እና ፕሬዚዳንቱን በማቃለል ክስ ከስልጣናቸው እንዲነሱ በማድረግ፤ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶለተተኪ ምክትል ፕሬዝዳንት እጩ አድርገው ያቀረቧቸውን በማጽደው ድምጽ ከሰጡ ከአንድ ቀንበኋላ የኬንያ ፍርድ ቤት  አዲሱን ምክትል ፕሬዝዳንት አግዷቸዋል።   ሩቶ ምክትል ፕሬዘዳንት ጋቻጉዋ ከስልጣናቸው እንደተነሱ የምክትል ፕሬዝዳንትነቱን ሥልጣንሹመት ለማካሄድ ጊዜ አላጠፉም።   ተተኪ ፕሬዝዳንት ለመምረጥ ተጨማሪ የ ሁለት ሳምንት ጊዜ የነበራቸው ዊሊያም ሩቶ ምርጫለማድረግ ፣ምክትል ፕሬዝዳንት ጋቻጓን እንዲተኩ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኪቱሬ ኪንዲኪንበፍጥነት ለእጩነት ያቀረቡ ሲሆን ከሰዓታት በኋላ የኪንዲኪ ሹመት ያለምንም ድምጸ ተዐቅቦ እና ተቃውሞ በ236 የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት ድምጽ ጸድቋል።   ፍርድ ቤቱ አርብ ዕለት በሰጠው ብይን የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ጋቻጓ በመተካታቸው ዙሪያ  የተወሰደውን እርምጃ በመቃወም ያቀረቡት አቤቱታ “የህዝብ ጥቅም ጥያቄዎችን ዙሪያ ጠቃሚየህግ ጥያቄ አስነስቷል” ብሏል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በሀገራቸው ጸጥታ እያስከበሩ ወደሚገኙ ሀገራቶች ጉብኝት ማድረግ ጀመሩ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዛሬ ቅዳሜ ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል።  የአሁኑ ጉብኝታቸው በሶማሊያ ጸጥታ በሚያስከብሩ አራት ሀገራት ከሚያደርጉት
የአሜሪካ ድምፅ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በሀገራቸው ጸጥታ እያስከበሩ ወደሚገኙ ሀገራቶች ጉብኝት ማድረግ ጀመሩ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዛሬ ቅዳሜ ዩጋንዳ ካምፓላ ገብተዋል።  የአሁኑ ጉብኝታቸው በሶማሊያ ጸጥታ በሚያስከብሩ አራት ሀገራት ከሚያደርጉት የመጀመሪያው ነው።    ፕሬዝዳንቱ በካምፓላ ከዩጋንዳው አቻቸው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር በጋራ ጉዳዮች፣ በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ ሽግግር አትሚስ ዙሪያ እና ቀጠናዊ ሰላምና መረጋጋትን በተመለከተ እንደሚወያዩ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ቤተመንግስት መግለጫ አስታውቋል።    ሀሰን ሼክ መሃሙድ በቀጣይ በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ አባል ሀገራት ወደ ሆኑትን ብሩንዲ፣ ኬኒያ እና ጅቡቲን ይጓዛሉ። የሶማሊያ ፕሬዘዳንት ቃል አቀባይ አብዱልቃድር ዲጌ ለአሜሪካ ድምጽ አፍሪካ ቀንድ ፕሬዘዳንቱ ኢትዮጵያን አይጎበኙም ሲሉ ተናግረዋል።   በሶማሊያ በሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ጸጥታ ለማስከበር የተሰማሩ ቢሆንም ነገርግን በጎርጎርሳዊያኑ 2024 መግቢያ ላይ ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የተፈራረመችው አጨቃጫቂ ውል ሶማሊያን ሉዓላዊነቴን ጥሳለች በሚል አስቆጥቷታል።   የኢትዮጵያ ሰራዊት በፊታችን ታህሳስ ሙሉ ለሙሉ ከሶማሊያ ለቆ የሚወጣ ሲሆን ሁለት የሶማሊያ ባለስልጣናት ምንጮች ግብጽ በሶማሊያ የአፍሪካ ቀንድ ሰላም አስከባሪ ተልዕኮ አባል ለመሆን ጥያቄ ማቅረቧን አረጋግጠዋል።  የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ አብዱልቃድር ዲጌ በሶማሊያ ቀጣዩ የሰላም አስከባሪ ማን እንደሚሆን መታየቱ ገና እንደቀጠለ ነው ብለዋል።

በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

በዲጂታል፣ ወይም በአጠቃላይ በኢንተርኔት አጠቃቀም ላይ ያለው ነፃነት ለተከታታይ 14 ዓመታት ማሽቆልቆሉን ‘ፍሪደም ሃውስ’ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ዓመታዊ ሪ
የአሜሪካ ድምፅ

በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

በዲጂታል፣ ወይም በአጠቃላይ በኢንተርኔት አጠቃቀም ላይ ያለው ነፃነት ለተከታታይ 14 ዓመታት ማሽቆልቆሉን ‘ፍሪደም ሃውስ’ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ አመልክቷል። በጥናቱ ከተካተቱ ሃገራት ውስጥ 41 በሚሆኑት በያዝነው ዓመት ምርጫ የሚካሄድ በመሆኑ ሁኔታውን አሳሳቢ እንደሚያደርገውና፣ ነጻና ክፍት የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት ዲሞክራሲ እውን እንዲሆን ወሳኝ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል። ኢትዮጵያም በጥናቱ ከተካተቱት ሃገራት አንዷ ስትሆን፣ ኢንተርኔት ሆን ተብሎ ከሚቋረጥበት፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ወይም ሌሎች የግንኙነት መንገዶች ከሚታገዱበት፣ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የመረጃ መረብ ላይ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ምክንያት የአካል ጉዳት ከሚደርስባቸውና ከሚገደሉበት ሃገራት ተርታ ተመድባለች፡፡ ሪፖርቱን የተመለከተው ባልደረባችን እንግዱ ወልዴ፣ ከቪኦኤዋ ቬሮኒካ ባልዴርስ ኤግሌሲያስ ዘገባ ጋራ አጣምሮ ተከታዩን አሰናድቷል።

ድንበር አቋርጠው የሚገቡ ሕገ ወጥ ስደተኞች እና የደኅንነት ጉዳይ

ጥቂት ሳምንታት በቀሩት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድንበር አቋርጠው የሚገቡ ሕገ ወጥ ስደተኞች እና የደኅንነት ጉዳይ አብይ ትኩረት ሆኖ ቀጥሏል።
የአሜሪካ ድምፅ

ድንበር አቋርጠው የሚገቡ ሕገ ወጥ ስደተኞች እና የደኅንነት ጉዳይ

ጥቂት ሳምንታት በቀሩት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ድንበር አቋርጠው የሚገቡ ሕገ ወጥ ስደተኞች እና የደኅንነት ጉዳይ አብይ ትኩረት ሆኖ ቀጥሏል። የአሜሪካ ድምጿ የኢሚግሬሽን ጉዳዮች ዘጋቢ አሊን ባሮስ ከአሪዞና የዩናይትድ ስቴትስ የድንበር ጠባቂዎችን እና የፍልሰት ጉዳይ አዋቂዎችን አነጋግራ ያደረሰችንን አሉላ ከበደ እንደሚከተለው ያቀርበዋል።

ጫሞ ሃይቅ ላይ ከሰመጠ ጀልባ ላይ 13 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከኮሬ ዞን 16 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ አርባምንጭ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ ጫሞ ሃይቅ ውስጥ መስመጡን እና 13 ሰዎች እስካኹን የገቡበት አለመታወቁ
የአሜሪካ ድምፅ

ጫሞ ሃይቅ ላይ ከሰመጠ ጀልባ ላይ 13 ሰዎች የገቡበት አልታወቀም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከኮሬ ዞን 16 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ አርባምንጭ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ ጫሞ ሃይቅ ውስጥ መስመጡን እና 13 ሰዎች እስካኹን የገቡበት አለመታወቁን፣ የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ሦስት ሰዎች በህይወት የተገኙ ሲኾን፣ ቀሪዎቹ ደግሞ እየተፈለጉ እንደኾነ የፖሊስ መምሪያው ሕዝብ ግንኙት ድቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ረታ ተክሉ ገልፀዋል። /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

የመንገዶች መዘጋት ለተለያዩ ችግሮች እንዳጋለጣቸው የደራ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

በኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘውን ደራ ወረዳ ከአጎራባች አካባቢዎች የሚያገናኙ መንገዶች ከአንድ ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ በታጠቁ ኃይሎች ተዘግተው መቀጠ
የአሜሪካ ድምፅ

የመንገዶች መዘጋት ለተለያዩ ችግሮች እንዳጋለጣቸው የደራ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

በኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኘውን ደራ ወረዳ ከአጎራባች አካባቢዎች የሚያገናኙ መንገዶች ከአንድ ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ በታጠቁ ኃይሎች ተዘግተው መቀጠላቸውን የገለጹ ነዋሪዎች፣ ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መጋለጣቸውን ገለጹ። በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው ፍቼ ወረዳና በአማራ ክልል በሚገኘው መራቤቴ ወረዳ በኩል ወደ አገሪቱ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚወስዱ መንገዶች፣ “ተጓዦችን ለዝርፊያ፣ለእገታና ለሞት የሚዳርጉ ናቸው” በማለትም ነዋሪዎቹ አማረዋል። ከአንድ ወር በፊት በመራቤቴ ወረዳ በኩል ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩ ስምንት የንግድ መኪና አሽከርካሪዎች በፋኖ ታጣቂዎች ከታገቱና የተጠየቁትን የማስለቀቂያ ቤዛ ከከፈሉ በኋላ መገደላቸውን፣ ኹኔታውን በቅርብ እንደሚያውቁ የተናገሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል። “በመራቤቴ በኩል ለመጓዝ የሚሞክሩ አሽከርካሪዎች ገንዘብ እየከፈሉ እንደሚያልፉ አውቃለሁ” ያሉት የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ከፍያለው አደሬ፣ተገደሉ ስለተባሉት ስምንት አሽከርካሪዎች ግን መረጃው እንደሌላቸው ጠቅሰዋል። ዋና አስተዳዳሪው ዛሬ ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ከአሜሪካ ድምፅ ጋራ ባደረጉት የስልክ ቃለ ምልልስ፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በዞኑ አምሰት ወረዳዎች ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ደግሞ በሦስት ወረዳዎች ውሰጥ እንደሚንቀሳቀሱ ጠቅሰው ለመንገዶቹ መዘጋትና በአካባቢው ላለው የጸጥታ ችግርም ሁለቱን ቡድኖች ተጠያቂ አድርገዋል። የአሜሪካ ድምፅ በስምንት አሽከርካሪዎች ላይ ተፈፀመ የተባለውን እገታና ግድያ እንደዚሁም ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆነውን አካል ማንነት ከገለልተኛ ወገን አላረጋገጠም። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትና የፋኖ ታጣቂ ቡድኖች ከዚህ ቀደም ለተመሳሳይ ውንጀላዎች በሰጧቸው ምላሾች፣ ታጣቂዎቻቸው ሰላማዊ ሰዎችን ዒላማ እንደማያደርጉ በመግለፅ በጽኑ አስተባብለዋል።

በስምንት ወራት ውስጥ ከስልሳ በላይ ሰዎች በኮሌራ መሞታቸውን አማራ ክልል አስታወቀ

ባለፉት ስምት ወራት በአማራ ክልል 66 ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ መሞታቸውን የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ከ4 ሺሕ በላይ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ
የአሜሪካ ድምፅ

በስምንት ወራት ውስጥ ከስልሳ በላይ ሰዎች በኮሌራ መሞታቸውን አማራ ክልል አስታወቀ

ባለፉት ስምት ወራት በአማራ ክልል 66 ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ መሞታቸውን የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ከ4 ሺሕ በላይ ሰዎች ደግሞ በወረርሽኙ መያዛቸውን ገልጿል። በተቋሙ የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አፈፃፀም ባለሞያ ሲስተር ሰፊ ድርብ፤ ካለፈው ዓመት መጋቢት ወር መጨረሻ ጀምሮ እስከ ትላንት ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በ41 ወረዳዎች በተከሰትው የኮሌራ ወረርሽኝ 66 ሰዎች ሲሞቱ ከ4 ሺ በላይ በወረርሽኙ መያዛቸውን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። /ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ያሏትን ግቦች አደጋ ላይ የጣለው የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግንኙነት

ቱርክ ከሶማሊያ ጋር ያላትን ትብብር በማጠናከር ላይ ትገኛለች። በያዝነው ወርም ለኃይል ምንጮች ፍለጋ ያሰማራቻት አሳሽ መርከብ ወደዚያ አቅንታለች። ዶሪያን
የአሜሪካ ድምፅ

ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ያሏትን ግቦች አደጋ ላይ የጣለው የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግንኙነት

ቱርክ ከሶማሊያ ጋር ያላትን ትብብር በማጠናከር ላይ ትገኛለች። በያዝነው ወርም ለኃይል ምንጮች ፍለጋ ያሰማራቻት አሳሽ መርከብ ወደዚያ አቅንታለች። ዶሪያን ጆንስ ከኢስታንቡል ባጠናቀረው ዘገባው እንዳመለከተው በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ውጥረት አንካራ በአፍሪካ ቀንድ ያሏትን ግቦች ለአደጋ እያጋለጠ ነው።

እስራኤል በሊባኖሱ ጥቃት የሂዝቦላህን አዛዥ መግደሏን አስታወቀች

የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ ባካሄደው ጥቃት የሂዝቦላህን የተዋጊ አዛዥ መገደሉን ዛሬ ሐሙስ አስታውቋል። በጥቃቱ የተገደለው የተዋጊ አዛዥ ሁሴን አዋዳ
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በሊባኖሱ ጥቃት የሂዝቦላህን አዛዥ መግደሏን አስታወቀች

የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ ባካሄደው ጥቃት የሂዝቦላህን የተዋጊ አዛዥ መገደሉን ዛሬ ሐሙስ አስታውቋል። በጥቃቱ የተገደለው የተዋጊ አዛዥ ሁሴን አዋዳ እንደሚባል የገለጸው ጦሩ፣ ወደ እስራኤል ለሚተኮሱ ሚሳይሎች ተጠያቂ መሆኑንም ገልጿል። ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል የሂዝቦላህ ታጣቂዎች ለሚገኙባቸው አካባቢዎች ቅርበት አላቸው ባለቻቸው ቦታዎች የሚኖሩ ሰዎች አካባቢያቸው ጥለው እንዲወጡ  አዲስ ትዕዛዝ አስተላልፋለች። እስራኤል እንዲህ ያሉ  ትዕዛዞች የምታስተላልፈው የአየር ጥቃቶችን ከማካሄዷ ቀደም ብላ ነው።   እስራኤል ትዕዛዙን ካስተላለፈችባቸው አካባቢዎች ውስጥ፣ በሊባኖስ ቤካ  ሸለቆ አካባቢ የሚገኙት ሳራይን፣ ታምኒን እና ሳፋሪ የተሰኙ አካባቢዎች ይገኙበታል። እስራኤል ትላንት ረቡዕ  በደቡባዊው ከተማ ናባቲህ ባካሄደችው የአየር ጥቃት ከንቲባውን ጨምሮ 16 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ50 በላይ መቁሰላቸውን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።  

ባይደን ዩክሬንን ቀዳሚ አጀንዳቸው በማድረግ ወደ ጀርመን አቅንተዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ከባድ ዝናባማው አውሎ ነፋስ (ሄሪኬን ሚልተን) አስቀድሞ የታቀደው ጉዟቸውን ለአንድ ሳምንት ከአስተጓጎለው በኋላ ዛሬ
የአሜሪካ ድምፅ

ባይደን ዩክሬንን ቀዳሚ አጀንዳቸው በማድረግ ወደ ጀርመን አቅንተዋል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ከባድ ዝናባማው አውሎ ነፋስ (ሄሪኬን ሚልተን) አስቀድሞ የታቀደው ጉዟቸውን ለአንድ ሳምንት ከአስተጓጎለው በኋላ ዛሬ ሐሙስ ወደ ጀርመን አቅንተዋል። ባይደን እና የጀርመኑ መሪ፣ ሁለቱም በቅርቡ ለዩክሬን ይፋ ያደረጉት አዲስ የደህንነት እርዳታ እና የሚሰጡትን ድጋፍ አስመልክቶ ከፍተኛ ጫና እያጋጠማቸው ነው። ዩክሬን በመሪዎቹ የመነጋገሪያ አጀንዳ በዋናነት ከተቀመጡት መካከል ናት፡፡ ዋይት ሀውስ ፕሬዚደንት ባይደን ሌላ የ425 ሚሊዮን ዶላር ጥቅል የደህንነት ድጋፍ ይፋ ማድረጋቸውን ትላንት ረቡዕ አስታውቋል።

የአዋሽ ፈንታሌው የመሬት መንቀጥቀጥ እና እስከ አዲስ አበባ የሚሰማው ንዝረት ቀጥሏል

ከአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የተነሳ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ቀን ላይ ተሰምቷል:: የመሬት መንቀ
የአሜሪካ ድምፅ

የአዋሽ ፈንታሌው የመሬት መንቀጥቀጥ እና እስከ አዲስ አበባ የሚሰማው ንዝረት ቀጥሏል

ከአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የተነሳ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በአዲስ አበባ ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ትላንት ምሽት እና ዛሬ ቀን ላይ ተሰምቷል:: የመሬት መንቀጥቀጡ መነሻ ከፈንታሌ 10 ኪሎ ሜትር አካባቢ ባለ ርቀት ላይ መሆኑን እና ከከርሰ ምድር አካባቢ የቅልጥ አለት ወደ መሬት እየሰረገ መምጣት ምክንያቱ መሆናቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ ተመራማሪ እና መምህር ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ተናግረዋል፡፡ በተመሳሳይ የዘርፉ ተመራማሪ እና መምህር ዶ/ር መሰለ ኃይሌ፣ አሁን እየተከሰተ ያለው አነስተኛ ሊባል የሚችል የመሬት መንቀጥቀጥ መሆኑን እና ቀስ በቀስ ኃይሉ እየወጣ መሆኑ የተሻለ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ ሁኔታው ለአዲስ አበባ የጎላ ስጋት ይፈጥራል ብለው እንደማይጠብቁ የገለፁት ሁለቱ ምሁራን፣ ሆኖም ቀጣይነቱ እና መጠኑ በግልፅ ሊተነበይ እንደማይችል እና የጥንቃቄ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

“አባላቴ እየታሰሩ፣ እየታገቱ እና እየተንገላቱ ነው”ተቃዋሚው የትግራይ ነጻነት ፓርቲ

አባላቴ በፖለቲካ እምነታቸው የተነሳ እየታሰሩ፣ እየታገቱ እና እየተንገላቱ ናቸው” ሲል ተቃዋሚው የትግራይ ነጻነት ፓርቲ ውድብ ናፅነት ትግራይ ከሰሰ። በተ
የአሜሪካ ድምፅ

“አባላቴ እየታሰሩ፣ እየታገቱ እና እየተንገላቱ ነው”ተቃዋሚው የትግራይ ነጻነት ፓርቲ

አባላቴ በፖለቲካ እምነታቸው የተነሳ እየታሰሩ፣ እየታገቱ እና እየተንገላቱ ናቸው” ሲል ተቃዋሚው የትግራይ ነጻነት ፓርቲ ውድብ ናፅነት ትግራይ ከሰሰ። በተለይ ከአወዛጋቢው የህወሐት ጉባኤ በኋላ፣ በክልሉ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የማዕድን እና የመሬት ዝርፊያ የሚቃወሙ አባላታችን ከፍተኛ ችግር እየደረሰባቸው ነው” ሲሉ የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር ደጀን መዝገበ ተናግረዋል። ዶክተር ደጀን በሰጡት መግለጫ “አንድ የፓርቲያችን ኣባል ተገድሏል፣ ሌሎች 16 አባላት ደግሞ እስራት፣ እገታ፣ ድበደባ እና እንግልት ደርሶባቸዋል” ሲሉ ወንጅለዋል። የክልሉ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የሰላም እና ፀጥታ ፅህፈት ቤት ኅላፊ አቶ ተስፋይ አባዲ በበኩላቸው፣ ክሱን ከሐቅ የራቀ ስም የማጥፋት ተግባር በማለት አጣጥለውታል።

ለቴክኖሎጂ ዕውቀት ልቀት የሚታትረው የትውልደ ኢትዮጵያውያኑ ተቋም

ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቴክኖሎጂው መስክ የተሻሉ የሥራ አማራጮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያግዙ የስልጠና ተቋማት በዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ እየተበራከ
የአሜሪካ ድምፅ

ለቴክኖሎጂ ዕውቀት ልቀት የሚታትረው የትውልደ ኢትዮጵያውያኑ ተቋም

ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቴክኖሎጂው መስክ የተሻሉ የሥራ አማራጮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያግዙ የስልጠና ተቋማት በዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢዋ እየተበራከቱ ይገኛሉ። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆነው አመኒም ሶሉሽንስ ፣ የቀደመ የቴክኖሎጂ መስክ ልምድ ለሌላቸው ሰዎች አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ለቁም ነገር አብቅቷል። ከሰሞኑ ተቋሙ ባሰናዳው መርሐ ግብር ፣ የቀድሞ ሰልጣኞቹን ስኬት ከማክበሩ በተጨማሪ ፣ የአቅም ግንባታ እና የትስስር መርሐ ግብሮችንም አከናውኗል።

VOA60 World - Israel says it killed Hamas leader Yahya Sinwar in Gaza

Israel: Foreign Minister Israel Katz and the Israeli military said Thursday that Hamas leader Yahya Sinwar was among three people killed by Israeli troops in an operation in Gaza. There has been no confirmation from Hamas.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - Israel says it killed Hamas leader Yahya Sinwar in Gaza

Israel: Foreign Minister Israel Katz and the Israeli military said Thursday that Hamas leader Yahya Sinwar was among three people killed by Israeli troops in an operation in Gaza. There has been no confirmation from Hamas.

ከጥቅምቱ የአሜሪካ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የአይምሮ ጭንቀት

የፖለቲካ ዝንባሌ ምንም ይሁን ምን፣ ምርጫ ሲቃረብ፣ የጭንቀት መጠን እንደሚጨምር የአሜሪካ የሥነ-ልቦና ባለሞያዎች ማህበር ያመለክታል። የማያቋርጥ የዜና ስር
የአሜሪካ ድምፅ

ከጥቅምቱ የአሜሪካ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የአይምሮ ጭንቀት

የፖለቲካ ዝንባሌ ምንም ይሁን ምን፣ ምርጫ ሲቃረብ፣ የጭንቀት መጠን እንደሚጨምር የአሜሪካ የሥነ-ልቦና ባለሞያዎች ማህበር ያመለክታል። የማያቋርጥ የዜና ስርጭት፣ አስጨናቂ ክርክሮች እና ለሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ የሚኖር ስጋት፣ ሁሉም በአይምሮ ጤና ላይ ጫና ያሳድራሉ። አንዳንድ የሥነ ልቦና ባለሞያዎች ታዲያ ችግሩን 'ከምርጫ ጋር የተያያዘ የጭንቀት ህመም' ሲሉ ይጠሩታል።  (ዝርዝሩን ከተያያዘው የቪዲዮ ፋይል ያገኙታል)

የአማራ ክልል ግጭት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ማስከተሉ ተገለፀ

ከአንድ ዓመት በላይ የቀጠለው የአማራ ክልል ግጭት ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት ማስከተሉን ጥናት ማመልከቱን የክልሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም አስታውቋል። ፎ
የአሜሪካ ድምፅ

የአማራ ክልል ግጭት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ማስከተሉ ተገለፀ

ከአንድ ዓመት በላይ የቀጠለው የአማራ ክልል ግጭት ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት ማስከተሉን ጥናት ማመልከቱን የክልሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም አስታውቋል። ፎረሙ ይሄንን ያስታወቀው፣«የሰብዓዊ ምላሽ ስልት በግጭት በተጎዱ የአማራ ክልል አካባቢዎች» በሚል ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር ባዘጋጀው እና ትላንት ይፋ ባደረገው ሰነድ ነው። ሰነዱ አክሎም “ግጭቱን ተከትሎ በድምሩ ከ 15 ሺህ በላይ ሰዎች የሞት፣ የመቁሰል፣ የአዕምሮና ማሕበራዊ ቀውስ እንደዚሁም የፆታዊ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል” በማለት ጠቅሷል። የፎረሙን ዋና ጸሐፊ ዶ/ር ታፈረ መላኩን ዘጋቢያችን አነጋግራለች።

«የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪው፣ በኑሯችን ላይ ጫና ይፈጥራ» የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች

“በአዲስ አበባ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው፣ አዲሱ የትራንስፖርት ክፍያ ጭማሪ፣ ኑሯችንን ያከብደዋል” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ አን
የአሜሪካ ድምፅ

«የትራንስፖርት ታሪፍ ጭማሪው፣ በኑሯችን ላይ ጫና ይፈጥራ» የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች

“በአዲስ አበባ ከተማ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው፣ አዲሱ የትራንስፖርት ክፍያ ጭማሪ፣ ኑሯችንን ያከብደዋል” ሲሉ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡ ስለ ጉዳዩ ለአሜሪካ ድምፅ ማብራሪያ የሰጡ አንድ የኢኮኖሚ ባለሙያ ደግሞ፣ የትራንስፖርት ክፍያን ጨምሮ፣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየጨመሩ ያሉት የአገልግሎት ክፍያዎች፣ በተለይም የታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል ኑሮ እንደሚጎዱ ገልፀዋል፡፡ መንግስት፣ ኑሮን የሚያረጋጉ እና ጫናውን ለመቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድም ባለሙያው ጠይቀዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምላሽና አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለዛሬ አልተሳካም፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ ዛሬ መጀመሩን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አስታወቁ  

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮ ቴሌኮምን 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ  ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል አስጀምረዋል ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአክሲዮን ሽ
የአሜሪካ ድምፅ

የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ ዛሬ መጀመሩን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አስታወቁ  

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮ ቴሌኮምን 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ  ዛሬ በሸራተን አዲስ ሆቴል አስጀምረዋል ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአክሲዮን ሽያጭ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፣ በቀጣይነት ኢትዮቴሌኮምን ጨምሮ የሌሎች ኩባንያዎች የድርሻ ሽያጭ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡ የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ፣ ለህዝብ የሚሸጠው በድምሩ ወደ 30 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያለውን 100 ሚሊዮን አክሲዮን እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ የአንድ አክሲዮን ዋጋ 300 ብር ሲሆን፣ መግዛት የሚቻለው ከ33 እስከ 3 ሺህ 333  እንደሆነም አስታውቀዋል፡፡

በቦንብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ያለፈው የደሴ ፍ/ቤት ዳኛ ቀብር ተፈጸመ

ከትላንት በስቲያ ሰኞ ፣ ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ሲያሽከረክሩት በነበረው መኪና ላይ በፈነዳ ቦንብ ሕይወታቸው ማለፉ በፖሊስ የተገለጸው፣ የደሴ ከተማ አስተዳደር
የአሜሪካ ድምፅ

በቦንብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ያለፈው የደሴ ፍ/ቤት ዳኛ ቀብር ተፈጸመ

ከትላንት በስቲያ ሰኞ ፣ ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ሲያሽከረክሩት በነበረው መኪና ላይ በፈነዳ ቦንብ ሕይወታቸው ማለፉ በፖሊስ የተገለጸው፣ የደሴ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ዳኛ ሙሉጌታ ከበደ ቀብር ሥነ- ሥርዓት ትላንት መፈፀሙን ወዳጆቻቸው ገለፁ። ጥቃቱ በማን እንደተፈፀመ እስካኹን አለመታወቁን ፖሊስ ገለጿል።

VOA60 Africa - Kenya's deputy president pleads not guilty in impeachment process

The house last week voted to charge Rigathi Gachagua on 11 counts, including abuse of power and corruption
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 Africa - Kenya's deputy president pleads not guilty in impeachment process

The house last week voted to charge Rigathi Gachagua on 11 counts, including abuse of power and corruption

VOA60 World - At least 140 people killed in tanker explosion in Nigeria

Nigeria: At least 140 people, including children, were killed and dozens were injured in the in northern Jigawa State after an overturned gasoline tanker truck exploded in flames while they were trying to scoop up fuel pouring from the vehicle, emergency serv
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 World - At least 140 people killed in tanker explosion in Nigeria

Nigeria: At least 140 people, including children, were killed and dozens were injured in the in northern Jigawa State after an overturned gasoline tanker truck exploded in flames while they were trying to scoop up fuel pouring from the vehicle, emergency services said Wednesday.

VOA60 America - US tells Israel to increase humanitarian aid reaching Gaza or risk weapons funding

The Biden administration has warned Israel that it must increase the amount of humanitarian aid reaching Gaza within the next 30 days, or it could risk losing access to U.S. weapons funding.
የአሜሪካ ድምፅ

VOA60 America - US tells Israel to increase humanitarian aid reaching Gaza or risk weapons funding

The Biden administration has warned Israel that it must increase the amount of humanitarian aid reaching Gaza within the next 30 days, or it could risk losing access to U.S. weapons funding.

እስራኤል በሌባኖስ ባደረሰችው የአየር ጥቃት 21 ሞቱ

እስራኤል በሌባኖስ በርካታ ቦታዎች ባደረገችው የአየር ድብደባ ቢያንስ 21 ሰዎች መሞታቸውን የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል። በደቡብ ሌባኖስ በእስራኤል
የአሜሪካ ድምፅ

እስራኤል በሌባኖስ ባደረሰችው የአየር ጥቃት 21 ሞቱ

እስራኤል በሌባኖስ በርካታ ቦታዎች ባደረገችው የአየር ድብደባ ቢያንስ 21 ሰዎች መሞታቸውን የአሶስዬትድ ፕረስ ዘገባ አመልክቷል። በደቡብ ሌባኖስ በእስራኤል ድብደባ ከተገደሉት ውስጥ የከተማዋ ከንቲባ እንደሚገኙበት ታውቋል። ድብደባው የዕርዳታ ሥራዎችን ለማስተባበር የተሰየመ ስብሰባ ላይ የነበሩ ሰዎችን መምታቱን የሌባኖስ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። እስራኤል  በማዘጋጃ ቤቱ ሲካሄድ የበረውንና በዕርዳታ ማስተባበር ላይ ያተኮረውን ስብሰባ “ሆን ብላ ኢላማ አድርጋለች” ሲሉ የሌባኖስ ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ናጂብ ሚካቲ ክስ አሰምተዋል። ትላንት ምሽት ደቡባዊዋን የቃና ከተማ የመታውን የአየር ድብደባ በተመለከተ እስራኤል ያለችው የለም። እ.አ.አ በ1996፣ ከ28 ዓመታት በፊት፣ እስራኤል በቃና ከተማ በሚገኝ የተባበሩት መንግስታት ቅጥር ግቢ ላይ በፈጸመችው የከባድ መሣሪያ ድብደባ የተ መ ድ የሠላም አስከባሪ ኃይሎችን ጨምሮ ቢያንስ 100 የሚሆኑ ሰዎች ተገድለዋል። በርካቶችም ቆስለዋል።

የኬንያ ምክትል ፕሬዝደንት የቀረበባችውን ክስ አስተባበሉ

የኬንያ ምክትል ፕሬዝደንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ ሙስናን ጨምሮ ፈፀሙ በተባለው ወንጀል ዛሬ በሃገሪቱ የሕግ መወሰኛ ም/ቤት ቀርበው ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል።
የአሜሪካ ድምፅ

የኬንያ ምክትል ፕሬዝደንት የቀረበባችውን ክስ አስተባበሉ

የኬንያ ምክትል ፕሬዝደንት ሪጋቲ ጋቻጉዋ ሙስናን ጨምሮ ፈፀሙ በተባለው ወንጀል ዛሬ በሃገሪቱ የሕግ መወሰኛ ም/ቤት ቀርበው ጥፋተኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል። ምክትል ፕሬዝደንቱ “በመንግሥት ላይ ለተደረጉት የተቃውሞ ሰልፎች ድጋፍ ሰጥተዋል፣ ሙስና ፈጽመዋል እንዲሁም በጎሳዎች መካከል ክፍፍል ለመፍጠር ሞክረዋል” የሚል ውንጀላ ቀርቦባቸዋል። ሪጋቲ ጋቻጉዋ ክሱ ፖለቲካዊ መሆኑን አመልክተዋል። በኬንያ በወንጀል ተጠያቂ የሚሆኑ የመጀመሪያው ምክትል ፕሬዚደንት ሊያደርጋቸው ይችላል ተብሏል። ክሱ በተጨማሪም በእርሳቸውና በፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ መካከል ያለውን መልካም ያልሆነ ግንኙነት ያመለከታል ተብሏል። ሩቶ የኡሁሩ ኬንያታ ምክትል በነበሩበት ጊዜ ተመሳሳይ የሆነ አለመግባባት ውስጥ የነበሩ ሲሆን፣ ወደ ፕሬዚደንትንነት ሥልጣን ከመጡ በኋላ ተመሳሳይ ችግር እንደማይፈጠር ቃል ገብተው ነበር። ፓርላማው ክሱን መስማት እንዲቀጥል ፍርድ ቤት በመወሰኑ፣ ፓርላማው በመስማማት ጉዳዩን ወደ ሕግ መወሰኛው ም/ቤት (ሴኔት) አስተላልፏል።

በናይጄሪያ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ በመቃጠሉ በርካቶች ሞቱ

በሰሜን ናይጄሪያ አንድ የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴ ተገልብጦ በመፈንዳቱ አንድ መቶ የሚሆኑ ሰዎች ሲሞቱ 50 የሚሆኑ ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሷል። አብዛኞቹ ሰዎች ሕይወታ
የአሜሪካ ድምፅ

በናይጄሪያ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ በመቃጠሉ በርካቶች ሞቱ

በሰሜን ናይጄሪያ አንድ የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴ ተገልብጦ በመፈንዳቱ አንድ መቶ የሚሆኑ ሰዎች ሲሞቱ 50 የሚሆኑ ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሷል። አብዛኞቹ ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡት ከተገለበጠው ቦቴ ላይ ከሚፈሰው ነዳጅ በመውሰድ ላይ ሳሉ ቦቴው በእሳት ተያይዞ በመፈንዳቱ ነው። የነዳጅ ቦቴው ከሌላ ተሽከርካሪ ጋራ እንዳይጋጭ  ለመራቅ ሲሞክር  መገልበጡን ፖሊስ አመልክቷል።  94 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡንና እንዲሁም 50 የሚሆኑ መጎዳታቸውን ፖሊስ ጨምሮ አስታውቋል። ቦቴው መገልበጡን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ከሚፈሰው ነዳጅ ላይ ለመውሰድ ጥረት ሲያደርጉ ፖሊስ ለመከላከል ቢሞክርም ከአቅም በላይ እንደሆነበት ተመልክቷል። በአስክፊ የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ በምትገኘው ናይጄሪያ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል። በነዳጅ አመላላሽ ቦቴዎች ላይ በተደጋጋሚ አደጋ የሚስተዋል ሲሆን፣ ባለፈው ወር አንድ የነዳጅ አመላላሽ ከሕዝብ ማመላለሻ ጋራ ተጋጭቶ 59 ሰዎች ሞተዋል።

እንግሊዝ በሶማሊያ ለተሰማራው ልዑክ ተጨማሪ ገንዘብ መደበች

እንግሊዝ በሶማሊያ ለተሰማራው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ልዑክ ተጨማሪ 10 ሚሊዮን ዶላር መመደቧን አስታውቃለች፡፡ የእንግሊዝ መንግሥት ዛሬ ባወጣው መግለጫ
የአሜሪካ ድምፅ

እንግሊዝ በሶማሊያ ለተሰማራው ልዑክ ተጨማሪ ገንዘብ መደበች

እንግሊዝ በሶማሊያ ለተሰማራው የአፍሪካ ኅብረት የሽግግር ልዑክ ተጨማሪ 10 ሚሊዮን ዶላር መመደቧን አስታውቃለች፡፡ የእንግሊዝ መንግሥት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ተጨማሪ ድጋፉ ባለፉት ሦስት ዓመታት ለአትሚስ እና አሚሶም የተሰጠውን ገንዘብ መጠን 100 ሚሊዮን ዶላር ያደርሰዋል። “አትሚስ የሶማሊያን ፀጥታ፣ ቁልፍ ሥፍራዎችንና የአቅርቦት ሰንሰለቶችን እንዲሁም መሠረት ልማቶችን በማስጠበቅ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል” ብሏል የእንግሊዝ መንግሥት በመግለጫው። “የሶማሊያ ብሔራዊ ሠራዊት ከሌሎች ጋራ በመተባበር ለሚያካሂደው ዘመቻ፣ የሰብዓዊ ዕርዳታን ለማሳለጥ፣ ምርጫና የፖለቲካ ሂደቶችን በሰላም እንዲከናወኑ ለማስቻል የሚደረገውን ጥረት የእንግሊዝ መንግሥት መደገፉን ይቀጥላል” ሲል አክሏል መግለጫው። ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ጂቡቲ፣ ዩጋንዳ፣ እና ቡሩንዲ በሶማሊያ ለተሰማራው የኅብረቱ ልዑክ ወታደሮቻቸውን አሰማርተዋል። ‘የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍና የማረጋጋት ልዑክ የተሰኘ አዲስ ኃይል በመጪው ጥር ሥራውን ከአትሚስ እንደሚረከብ ይጠበቃል፡፡ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋራ የተፈራረመችውን የመግባቢያ ሥምምነት ተከትሎ በተነሳው ቅሬታ ምክንያት በአዲሱ ልዑክ ውስጥ ኢትዮጵያ እንድትሳተፍ እንደማትፈልግ ሶማሊያ አስታውቃለች፡፡

ኢትዮጵያውያን ታዋቂ እንስቶች የከበሩበት ምሽት

በስፖርት ስነ ጥበብና ስራ ፈጠራ ዘርፎች በሙያቸው ማህበረሰብን የጠቀሙ አፍሪካውያንን የሚሸልመው የዘንድሮው የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ስነ ስርዓት
የአሜሪካ ድምፅ

ኢትዮጵያውያን ታዋቂ እንስቶች የከበሩበት ምሽት

በስፖርት ስነ ጥበብና ስራ ፈጠራ ዘርፎች በሙያቸው ማህበረሰብን የጠቀሙ አፍሪካውያንን የሚሸልመው የዘንድሮው የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ሽልማት ስነ ስርዓት በሜሪላንድ ተካሂዷል:: ታዋቂዋ የዘመናዊ ሙዚቃ አቀንቃኟ አስቴር አወቀና ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩን ጨምሮ አምስት ኢትዮጵያውያትም የዘንድሮው ተሸላሚ ሁነዋል፡፡  ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይመልከቱ፡፡