የኤም 23 አማጽያን በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሁለተኛ ቁልፍ ከተማ ተቆጣጠሩ
በምሥራቃዊ ኮንጎ ውስጥ ያሉ አማፂዎች ለዓመታት ከዘለቀውን፤ ከመንግስት ሃይሎች ጋር ያደረጉት ውጊያ ተባብሶ ከቀጠለ በኋላ ትላንት አርብ ዕለት ወደ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ ቡካቩ መግባታቸውን የአካባቢው እና የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች አስታውቀዋል።
የኤም 23 አማፂዎች ወደ ከተማዋ ካዚንጉ እና ባጊራ ዞን ገብተው 1.3 ሚሊዮን ህዝብ ወደ የሚኖርበት መሃል ከተማ እየገሰገሱ ነው፤ በማለት በደቡብ ኪቩ የሚገኘው የሲቪል ማኅበረሰብ ምክትል ፕሬዝዳንት ዣን ሳሚ ተናግረዋል። ምክትል ፕሬዝዳንት ዣን ሳሚ በከተማው አንዳንድ አካባቢዎች የተኩስ ልውውጥ መደረጉን አስታውቀዋል።
የተለያዩ በድረገጽ ላይ የተለጠፉ ተንቀሳቃሽ ምስሎች አማፂዎቹ አማ ወደ ባጊራ ወደተሰኙ አካባቢዎች ሲዘምቱ የሚያሳዩ ይመስላል። ከተንቀሳቃሽ ምስሎቹ በአንዱ ላይ፤ ከጀርባ ያለው ድምጽ “እዚያ አሉ... ብዙዎቹ አሉ” እያለ የሚጮህ ድምጽ ይሰማበታል።
ከክስተቱ ሰዓታት በፊት አማፂያኑ በካቩሙ ከተማ የሚገኘውን ሁለተኛውን አውሮፕላን ማረፊያ መቆጣጠራቸውን አስታውቀዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቅርቡ ከመንግስት ሃይሎች ጋር የቀጠለው ጦርነት 350,000 ተፈናቃዮችን ያለ መጠለያ አስቀርቷል በማለት አስጠንቅቋል።
የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መንግስት ሩዋንዳ የኤም 23 አማፂ ቡድንን እየደገፈች ነው በማለት በተደጋጋሚ ቢወንጅለም ሩዋንዳ አስተባብላለች። በአንጻሩ ኪጋሊም በበኩሏ ኪንሻሳ እ.ኤ.አ.1994 በሩዋንዳ የዘር ጭፍጨፋ ያስከተለውን፤ የሩዋንዳ ነፃ አውጪ ዲሞክራሲያዊ ሃይል (ኤፍ.ዲ.ኤል.አር) ጋር በመተባበር የሁቱ ታጣቂ ቡድን ትደግፋለች በማለት የምትከስ ሲሆን ኪንሻሳ ውንጀላውን አትቀበለውም።